መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ

1ኛ ነገሥት 17-22

እጅግ የከፋ ነገር ባለበት ዘመን ሁሉ፥ እግዚአብሔር የራሱ የሆኑ ታማኝ ሰዎች አሉት። እነዚህ ሰዎች ብዙ ጊዜ «ቅሬታዎች» የምንላቸው፥ ለሐሰት ትምህርት አንንበረከክም የሚሉ፥ ወይም ከፍተኛ ስደት ባለበት ጊዜ እምነታቸውን በጽናት ይዘው የሚቆዩ ሰዎች ናቸው። ብዙውን ጊዜ በእዚህ የጨለማ ወቅቶች፥ ለእግዚአብሔር ታማኝ የሆኑ ሰዎች ተስፋ ሊቆርጡና በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያለውን እምነታቸውን ለመተው ሊፈተኑ ይችላሉ። ለብቻ ከመቆም ይልቅ፥ […]

1ኛ ነገሥት 17-22 Read More »

1ኛ ነገሥት 12-16

የአንድ መሪ መንፈሳዊ ሕይወት በአጠቃላይ በሰዎች መንፈሳዊ ሕይወት ላይ ታላቅ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ተመልክተናል። ብዙ ጊዜ መሪው ለእግዚአብሔር ታዛዥ በሚሆንበትና ራሱን ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ አሳልፎ በሚሰጥበት ጊዜ፥ ሕዝቡም ለእግዚአብሔር ራሱን አሳልፎ በመስጠት ታዛዥ ይሆናል። መሪው ለእግዚአብሔር በሙላት በማይታዘዝበት ጊዜ፥ ሕዝቡን ከእውነት በቀላሉ ያርቀዋል። 1ኛና 2ኛ ነገሥትን በምናነብበት ጊዜ፥ የእስራኤልና የይሁዳ ነገሥታት የሕዝቡን መንፈሳዊ ሕይወት በከፍተኛ ደረጃ

1ኛ ነገሥት 12-16 Read More »

የሰሎሞን ውድቀት (1ኛ ነገሥት 11)

ሰሎሞን በዓለም ዘንድ ምንም ያህል ጥበበኛ ይሁን፥ በእግዚአብሔር ዓይን ጥበበኛ አልነበረም። ሰሎሞን በወጣትነቱ ዘመን «የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው» (ምሳ. 1፡7) ሲል ጽፎ ነበር። ይህንን ሲል እውነተኛ ጥበብ የሚመጣው ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሆነና የሚገለጠውም ለእግዚአብሔር ወደመታዘዝ በሚያመራው በፈሪሃ እግዚአብሐርነት ነው ማለት ነበር። የሚያሳዝነው ግን ሰሎሞን በሸመገለ ጊዜ ይህንን አልተከተለም። ይልቁንም እግዚአብሔርን ረሳ፤ የእስራኤልን አምልኮ አበላሸ፤ ለእስራኤል

የሰሎሞን ውድቀት (1ኛ ነገሥት 11) Read More »

የ1ኛ ነገሥት አስተዋጽኦ እና ዓላማዎች

የ1ኛ ነገሥት አስተዋጽኦ ሰሎሞን (1-11)  ሮብዓም (12)  የተከፋፈለው የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥት [13-22] (931-853 ዓ.ዓ.)  ሀ. ቀዳማዊ ኢዮርብዓም (12፡22-14፡20)  ለ. ሮብዓም (14፡21-33)  ሐ. አብያ (15፡1-8)  መ. አሳ (15፡9-24)  ሠ. ናዳብ (15፡25-32)  ረ. በአሳ (15፡33-16፡7)  ሰ. ኤላ (16፡8-14)  ሸ. ዘምሪ (16፡15-20) ቀ. ዘንበሪ (16፡21-28)  በ. አክዓብ (16፡29-34)  ኤልያስና ነገሥታት ሀ. ኤልያስና አክዓብ (17፡1-22፡40)  ለ. ኢዮሣፍጥ (22፡41-50) ሐ.

የ1ኛ ነገሥት አስተዋጽኦ እና ዓላማዎች Read More »