የሕይወት እንጀራ

ትንቢተ ዳንኤል

ዳንኤል 7-12

የትንቢተ ዳንኤል የመጀመሪያ ክፍል የሆነው ምዕራፍ 1-6፥ በዳንኤል የሕይወት ዘመን በተፈጸሙ ታሪካዊ ድርጊቶች ላይ ያተኩራል። ራእዮቹም ስለ አሕዛብ ነገሥታት እንጂ ስለ ዳንኤል አልነበሩም። ከምዕራፍ 7-12 ያለው የመጽሐፉ ሁለተኛ ክፍል እግዚአብሔር የአሕዛብ መንግሥታትንና የእስራኤልን ሕዝብ የወደፊት ሁኔታ ለዳንኤል በገለጣቸው ልዩ ራእዮች ላይ ያተኩራል። የመጀመሪያዎቹ ስድስት ምዕራፎች በቅድሚያ አሕዛብን የሚመለከቱ ከመሆናቸው የተነሣ የተጻፉት በአራማይክ ቋንቋ ሲሆን፥ የመጨረሻዎቹ […]

ዳንኤል 7-12 Read More »

ዳንኤል 1-6

የውይይት ጥያቄ፥ ምሳሌ 22፡6ና መክብብ 12፡1 አንብብ። ሀ) እግዚአብሔር ልጆቻቸውን በጌታ መንገድ ለሚያሳድጉ ወላጆች የገባው የተስፋ ቃል ምንድን ነው? ለ) ሰሎሞን እግዚአብሔርን ማክበር አለብን ያለው መቼ ነው? በወጣትነት ዘመናችን የምንማረው ትምህርት በቀሪው የሕይወት ዘመናችን ምን ዓይነት ሰዎች እንደምንሆን ተጽዕኖ ከሚያሳድሩብን ነገሮች መካከል ከፍተኛው ነው። እንዲሁም በወጣትነት ዘመናችን የምንወስናቸው ውሳኔዎች በቀሪው የሕይወት ዘመናችን በምናደርጋቸው ነገሮች ላይ

ዳንኤል 1-6 Read More »

የትንቢተ ዳንኤል ዓላማና መልእክት

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ዳንኤል 2፡21፤ 4፡34-35 አንብብ። እነዚህ ቍጥሮች እግዚአብሔር የዓለምን መንግሥታት ጨምሮ የነገሮች ሁሉ ተቈጣጣሪ መሆኑን እንዴት ያስተምሩናል? ክርስቲያኖች ይህንን እውነት ማወቅ የሚያስፈልጋቸው ለምንድን ነው? አይሁድ ከ1400 ዓ.ዓ. እስከ 586 ዓ.ዓ. እግዚአብሔር ለአብርሃም በገባው በቃል ኪዳን ምድር ላይ ኖረዋል። በ586 ዓ.ዓ. ግን በድንገት አይሁድ ከተስፋይቱ ምድር ተማርከው ተወሰዱ። በአሕዛብ ምድር ሆነው በአሕዛብ ቁጥጥር ሥር

የትንቢተ ዳንኤል ዓላማና መልእክት Read More »

የትንቢተ ዳንኤል ታሪካዊ ሥረ-መሠረት

ዳንኤል በተወለደበት ወቅት የነበሩት ሁኔታዎች ለይሁዳ ሕዝብ እጅግ መልካም የሚመስሉ ነበሩ። እግዚአብሔርን የሚፈራው ንጉሥ ኢዮስያስ በዙፋን ላይ ነበር። ቤተ መቅደሱ ነጽቶ ነበር። ቢያንስ ቢያንስ ለይስሙላ ሰዎች እግዚአብሔርን እንደሚያከብሩና እንደሚያመልኩ ይናገሩ ነበር፤ ነገር ግን አይሁድ የለወጡት ባሕርያቸውን እንጂ ልባቸውን አልነበረም። በይሁዳ ሰላም የነበረ ቢመስልም እንኳ በሰሜን ምዕራብ ራቅ ብሎ ጦርነት ይካሄድ ነበር። በአሦራውያን ቊጥጥር ሥር የነበረው

የትንቢተ ዳንኤል ታሪካዊ ሥረ-መሠረት Read More »

የትንቢተ ዳንኤል ሙግቢያ

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ለክርስቲያኖች እግዚአብሔር በሕይወታቸው ውስጥ ማንኛውንም ነገር እንደሚቆጣጠር ማወቃቸው አስፈላጊ የሚሆነው ለምንድን ነው? ለ) በሕይወትህ ውስጥ በተፈጸመ ድርጊት እግዚአብሔር ተቆጣጣሪ መሆኑን የረሳህበትን ሁኔታ ግለጥ። ውጤቱ ምን ነበር? መ) በችግር ውስጥ ሆነህ በእግዚአብሔር ሉዓላዊነት የተጽናናህበትን ሁኔታ ግለጽ። ለክርስቲያን እግዚአብሔር በነገሮች ሁሉ ላይ ሉዓላዊ መሆኑን ከማወቅ ጋር የሚስተካከሉ እውነቶች ቢኖሩ ከቊጥር የማይገቡ ናቸው። እግዚአብሔር የበላይ

የትንቢተ ዳንኤል ሙግቢያ Read More »