ዘኁልቁ 22-36
እግዚአብሔር አንድን ሰው ለመባረክ ከወሰነ፥ ያንን ሰው መርገም አንዳች ፋይዳ ይኖረዋልን? የበለዓምና የሞዓብ ንጉሥ ታሪክ እግዚአብሔር የሚወዳቸውን ሰዎች፥ የእግዚአብሔር ሕዝብ ጠላቶች በምንም ዓይነት ብርታት ሊረግሟቸው ቢሞክሩም፥ እርግማናቸውን እግዚአብሔር እንደሚያከሽፍ ያሳያል፤ ሙከራቸውም ከንቱ ልፋት ብቻ ይሆናል። በተጨማሪ ይህ የበለዓምና የሞዓብ ንጉሥ ታሪክ የሚያስተምረን የእግዚአብሔርን ሕዝብ የሚያጠፋቸው ውጫዊ ስደት ሳይሆን፥ ከዓለም ጋር ጓደኝነት መግጠማቸውና ዓለምን መምሰላቸው እንደሆነ […]