ጢሞቴዎስና አፍሮዲጡ፣ ወደር የማይገኝለት ጥንድ (ፊልጵስዩስ 2፡19-30)
በሳን በርናዲኖ ካሊፎርኒያ ውስጥ፥ አንድ ጋዜጠኛ ተዘዋዋሪ በሚበዛበት መንገድ አጠገብ ከሚገኝ ቦይ ውስጥ አንዱን ሰው ሕመምተኛ አስመስሉ እንዲተኛ አደረገ። ታዲያ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች በአጠገቡ ይለፉ እንጂ፥ አንዳቸውም ቆመው ሊረዱት ይቅርና የሐዘን ፊት እንኳን አላሳዩትም ነበር። ከጥቂት ዓመታት በፊት ጋዜጦች አንድ ከዳር እስከዳር የተናኘ ዜና አውጥተው ነበር። ይኸውም አንድ ሰው እያደባ ሴትየዋን ሲቀርባትም ሆነ በመጨረሻም በጩቤ ሲወጋት ሠላሳ ስምንት ተመልካቾች ቢያዩም አንዳቸውም ፖሊስ ለመጥራት ስልክ አለመደወላቸውን የሚገልጽ ነበር። እንደዚሁም ሁለት ወጣቶች በዲትሮይት ውስጥ ሲሄዱ በስልክ መደወያ ጎጆ ውስጥ አንዲት ሴት በልብ ድካም በሽታ ስትሰቃይ ያገኙአታል። እነርሱም ቅርብ ወደሆነው ቤት ተሸክመዋት በመሄድ፥ ባለቤቱ በሩን ሲከፍትላቸው እርዳታ ጠየቁ። ያገኙት መልስ ግን «ከበረንዳዬ ላይ ዘወር በሉ – እርሷንም የምታደርሱበት አድርሷት» የሚል ነበር። አንድ የከንታኪ ሐኪም በሽተኛውን ለመጠየቅ በመኪና በመጓዝ ላይ እንዳለ አንድ አደጋ ሲደርስ አየ። ቆመና ለተጎዳው ሰው እርዳታ ካደረገለት በኋላ ወደ በሽተኛው ቤት አመራ። ሆኖም ያ የረዳው ሰው ከጥቂት ቀናት በኋላ ክስ አቀረበበት። ታዲያ በዛሬው ጊዜ «መልካሙን ሳምራዊ» መሆን ይቻላል? እያንዳንዱስ ሰው ራሱን ለመጠበቅ ሲል ልቡን ማደንደን አለበት ማለት ነው? ምናልባት «መሥዋዕትና አገልግሉት» ጥንታዊ ልማድ ስለሆኑ እኛ ዘመናዊ ሥልጣኔ ብለን ከምንጠራው ጋር ሊስማሙ አይችሉም ይሆናል። እንዳውም እርስ በእርስ መረዳዳት በጳውሎስ ጊዜ እንኳን ያልተለመደ ለመሆኑ አያጠያይቅም። በሮም ያሉ ክርስቲያኖች በፊልጵስዩስ ስላለው ችግር ግድ የላቸውም ነበር። ጳውሎስ ወደ ፊልጵስዩስ ፈቃደኛ ሆኖ የሚሄድለት አንድም ሰው አላገኘም (2፡19-21)። ጊዜው ብዙም አልተለዋወጠም ማለት ነው። ጳውሎስ በዚህም አንቀጽ፥ አሁንም ቢሆን ስለ ትሑት አእምሮ እያስረዳን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን ምሳሌ በማድረግ ለትሑት አእምሮ መግለጫ ሰጥቶናል (2፡1-11)። ከእራሱ ልምምድ በመነሣት የትሑት አእምሮ እንዴት እንደሚሠራ ቀደም ሲል ያሳየን ነው (2፡ 12-18)። አሁን በአገልግሎቱ ጊዜ ከረዱት ሰዎች መሀል ሁለቱን ያስተዋውቀናል፣ ጢሞቴዎስንና አፍሮዲጡን፣ እና ይህንንም ያደረገው ያለ ምክንያት አልነበረም። በእርግጥ አንባቢዎቹ የሚከተለውን ምክንያት እንደሚያቀርቡ ያውቃል፥ «እኛ እንደ ክርስቶስና እንደ ጳውሎስ ይህን መሰሉቹን ምሳሌዎች ለመከተል አይቻለንም። መቼም ኢየሱስም የእግዚአብሔር አንድያ ልጁ ነው ጳውሎስም የተመረጠ ሐዋርያ፥ ትልቅ መንፈሳዊ ልምምድ ያለው ነው! » ሲሉ ምክንያት ይሰጣሉ። ከዚህም የተነሣ ነው ጳውሎስ ሐዋርያ ወይም በጣም የሚያስደንቅ ተአምር የሚሠሩትን ሳይሆን ሁለቱን «ተራ ቅዱሳን» የሚያስተዋውቀን። እንድናውቅ የሚፈልገውም ትሑት አእምሮን ጥቂት የተመረጡ ሰዎች ብቻ የሚታደሉት ስጦታ አለመሆኑን ነው። ይህ ስጦታ ማንኛውም ክርስቲያን ደስታን ያገኝ ዘንድ የሚያስፈልገው ነው። በመሆኑም ዕድሉ ለሁሉም አማኞች ተሰጥቷቸዋል። ጢሞቴዎስ (2፡19-24) ጳውሎስ በመጀመሪያ የወንጌል አገልግሎት ጉዞው ላይ ጢሞቴዎስን በድንገት አገኘው (ሐዋ. 16፡6 ጀምሮ)፥ ምናልባትም በዚያን ጊዜ ወጣቱ ተለውጦ ሊሆን ይችላል (1ኛ ቆሮ. 4፡17)። በመጀመሪያም ክርስትናን የተቀበሉት የጢሞቴዎስ እናትና አያት ነበሩ (2ኛ ጢሞ. 1፡3-5)። እርሱም በእናቱ የአይሁድ በአባቱም የአሕዛብ ልጅ ነበር፥ ነገር ግን ጳውሎስ ሁልጊዜ በእምነት የራሱ «የተወደደ ልጅ» አድርጎ ይቆጥረዋል (2ኛ ጢሞ. 1፡2)። ወጣቱ ጢሞቴዎስ የጳውሎስ ረዳት መሆን የጀመረው ጳውሎስ ወደ ልስጥራንና ደርቤን ለሁለተኛው ጊዜ በተመለሰበት ወቅት ነው(የሐዋ. 16፡1-4)። በአንድ በኩል፥ ጢሞቴዎስ በኋላ ማርቆስ በመባል የሚታወቀውን ዮሐንስን ተክቷል። ይኸውም ጳውሎስ በዚህ በጉዞው ላይ ማርቆስን ይዞ ለመሄድ ባለመፈለጉ ነው። ለዚህም ምክንያቱ ማርቆስ ከዚህ ቀደም ሲል ኃላፊነቱን ለመሸከም ፈቃደኛ ባለመሆኑ ነው (ሐዋ. 13፡13፤15፡36-41)። ከዚህ ከጢሞቴዎስ ልምምድ ውስጥ የምንማረው ትሑት አእምሮ በአንድ አማኝ ሕይወት ውስጥ ከመቅፅበት የሚታይ ወይንም ትኩረት ሳንሰጠው የሚከሰት ነገር አለመሆኑን ነው። ጢሞቴዎስ ለማደግና ለመጎልበት «የክርስቶስን አሳብ» ያዘ። አገልጋይ መሆን የተፈጥሮው አልነበረም። ነገር ግን የጌታን ፈለግ በመከተሉና ከጳውሎስ ጋር በቅርብ በመሥራቱ፥ ጳውሎስ የሚተማመንበትና እግዚአብሔር የሚባርከው ዓይነት አገልጋይ ለመሆን በቃ። የዚህን ወጣት ሰው ባሕርይ ተመልከት። እርሱ የማገልገል አሳብ ነበረው (2፡19-21) መጀመሪያ ነገር፥ ጢሞቴዎስ በተፈጥሮው ለሰዎች ጥንቃቄ የሚያደርግ ስለሚያስፈልጋቸውም ነገር የሚጨነቅ ነበር። እርሱ «ጓደኞቹን በማሸነፍና ሰዎችን በመጫን» አይደሰትም ነበር፤ እርሱ ከልቡ የሚደሰተው በሚያገለግላቸው ሰዎች አካላዊና መንፈሳዊ ደኅንነት ነበር። ጳውሎስ ስለፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን ጭንቀት አድሮበት ነበር። በመሆኑም ጭንቀቱን የሚገልጽለትና በዚያም የሚያየውን ሁሉ ሳይደብቅ የሚነግረው አንድ ሰው መላክ ፈልጎ ነበር። በሮም ውስጥ በመቶ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ነበሩ (በሮሜ ከተማ ውስጥ ጳውሎስ ለ26ቱ በስማቸው ሰላምታ አቅርቧል)፤ ሆኖም አንዳቸውም ይህንን ጉዞ ለማድረግ ፈቃደኞች አልነበሩም። «ሁሉ የራሳቸውን ይፈልጋሉና፥ የክርስቶስ ኢየሱስን አይደለም» (ፊልጵ. 2፡21)። ከዚህ የምንረዳው ሁላችንም ብንሆን በፊልጵ. 1፡21 ወይም በፊልጵ. 2፡21 ውስጥ መኖራችንን ነው! ነገር ግን ጢሞቴዎስ በተፈጥሮው ለሌሎች በጎ ለማድረግ የሚጨነቅ ነበር። ስለዚህ የአገልጋይ አሳብ ያለው ሰው ነበር። በሮም ውስጥ ያሉ አማኞች ግን በራሳቸው ጉዳይ ብቻ የተጠመዱና በውስጣዊ ጭቅጭቃቸው የተያዙ በመሆናቸው (1፡15-16) ለዚህ ዓይነቱ ጠቃሚ ለሆነው የጌታ አገልግሉት ጊዜ አልነበራቸውም። በአሁኑም ጊዜ ቢሆን የቤተ ክርስቲያን ዓቢዩ ችግር አባሎቹ ጊዜያቸውንና ኃይላቸውን አላስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ማዋላቸው ነው። ጢሞቴዎስ አንዱን ወገን የማጠናከር ወይም ሌላውን የመከፋፈል ፍላጎትም ምኞትም አልነበረውም። እርሱ በእግዚአብሔር ሰዎች መንፈሳዊ ሁኔታ ብቻ ደስተኛ ነበር። ይህም በተፈጥሮው የተቀዳጀው ጸጋ ነበር። ሆኖም ይህ ጸጋ እንዴት ነው ሊበለፅግና ለሌሎችም አገልግሎት ሊውል የሚችለው? መልሱን በሚቀጥለው በወጣቱ ሰው ባሕርይ ውስጥ እናገኛለን። ሌሎችን ለማገልገል የሠለጠነ ነበረ (2፡22) ጳውሎስ ጢሞቴዎስን ክርስቶስን እንደተቀበለ ወዲያውኑ የ«ቡድኑ» አባል አላደረገውም። ጳውሎስ እንዲህ ዓይነቱን ስህተት ላለመፈጸም የሚጠነቀቅ ሰው ነበር። መጀመሪያ ላይ በልስጥራንና ደርቤን ውስጥ የቤተ ክርስቲያን ተራ አባል በመሆን እንዲያገለግል ትቶት ሄደ። ከዚያም በዚያ ኅብረት በመንፈሳዊ ነገሮች አደገ፥ ጌታንም እንዴት እንደሚያገለግል ተማረ። ጳውሎስ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ወደዚያ አካባቢ ሲመለስ ስለ ወጣቱ ጢሞቴዎስ «ወንድሞች ሲመሰክሩለት» በመስማቱ ደስ አለው (ሐዋ. 16፡2)። ጳውሎስም ከዓመታት በኋላ ለጢሞቴዎስ ሲጽፍለት፥ አዲስ የተለወጠ ሰው ለአገልግሎት ብቁ ከመሆኑ በፊት ማደግና መሠልጠን እንደሚያሻው ገልጦለታል (1ኛ ጢሞ. 3፡6-7)። አንድ ታዋቂ የምሽት ክበብ ተጫዋች ወደ አንድ መጋቢ በመሄድ መዳኑንና ጌታን ለማገልገል መፈለጉን አስታወቀው «ከዚህ ቀጥዩ ምን ማድረግ ይገባኛል?» በማለትም ጠየቀው። «እኔ የማሳስብህ፥ ከአንድ ጥሩ ቤተ ክርስቲያን ጋር ተገናኝተህ ማደግ እንድትጀምር ነው» ብሉ መጋቢው ከመለሰለት በኋላ፥ ከዚያም «ሚስትህ ክርስቲያን ናት?» ሲል ጠየቀው። «አይደለችም» አለ ሙዚቀኛው፥ «ሆኖም በእኔ አማካይነት እንደምትለወጥ ተስፋ አደርጋለሁ» ካለ በኋላ «ግን እኮ እርሷ ለመለወጥ እፈልጋለሁ እስከምትለኝ መጠበቅ የለብኝም! ማለቴ አሁኑኑ ለእግዚአብሔር አንድ ነገር ማድረግ አለብኝ» አለ። «አዎን፤ ስለ ጌታ ለመመስከር መጠበቅ አያስፈልግህም። የቤተ ክርስቲያን አባል በመሆን ተሰጥዖህን ለክርስቶስ ተጠቀምበት» ሲል መከረው። «ነገር ግን እኔን አላወቅከኝም» ብሉ ሙዚቀኛው ተቃወመ፥ «እኔ እኮ ሁሉም ሰው የሚያውቀኝ ትልቅ ተጫዋች ነኝ። የራሴ የሆነም ድርጅት መጀመር እፈልጋለሁ የሙዚቃ ሸክላዎችን ማሳተም፥ በብዙ ሕዝብ መሀልም መታየት እፈልጋለሁ»። መጋቢው በማስጠንቀቅ፥ «በጣም በርቀትና በፍጥነት ከሄድክ እራስህንና ምስክርነትህን ልትጎዳ ትችላለህ። ሰዎችን መማረክ የሚጀመርበት ቦታ ከቤት ውስጥ ነው። እግዚአብሔር የአገልግሎትን ቦታ የሚከፍትልህ እንደተዘጋጀህ ሲያይ ነው። እስከዚያው ድረስ መጽሓፍ ቅዱስህን አጥና፥ እራስህን ለማሳደግ ዕድል ስጠው» አለው። ሰውየው የመጋቢውን ምክር አልተቀበለም። በእርሱ ምትክ ግን የራሱ የሆነ ድርጅት ከፍቶ በራሱ ኃይል ለማደግ ጀመረ። ሆኖም ሥራው «የተሳካለት። ከዓመት ላነሰ ጊዜ ብቻ ነበር። ከባዱን ኃላፊነቱን ለመወጣት በቂ ጥንካሬ ስላልነበረው ምስክርነቱን ብቻ ሳይሆን፥ በማያቋርጥ ጉዞው የተነሣም ከሚስቱና ከቤተሰቡ ጋር እንደ ባዕድ መተያየት ጀመረ። ከዚያም እንግዳ ከሆነ ቡድን ጋር በመግጠሙ ከሕዝባዊ አገልግሎቱ ላይ ተሰወረ፥ በመጨረሻም የተበላሸና የከሰረ ሰው ሆነ። መጋቢውም ሰለ ሰውየው ሁኔታ ሲተች «የጠለቀ ሥር በመስደድ ምትክ፥ ቅርንጫፎቹን ለማንሰራፋት የፈለገ ሰው ነበር። ይህን የሚያደርግ ሰው መጨረሻው ውድቀት ይሆናል» አለ። ጳውሎስ ይህን መሰሉን ስሕተት በጢሞቴዎስ ላይ አልፈጸመም። ወደታች ሥር እንዲሰድ ጊዜ ሰጥቶት ነበር። ከዚያም ወጣቱን ሰው በወንጌል ሥራ ካስገባው በኋላ አብረው ይሠሩ ነበር። ለጢሞቴዎስ ቃሉን ማስተማር
ጢሞቴዎስና አፍሮዲጡ፣ ወደር የማይገኝለት ጥንድ (ፊልጵስዩስ 2፡19-30) Read More »