የሕይወት እንጀራ

የዮሐንስ ወንጌል

ማርያም ኢየሱስን ሽቶ መቀባቷ እና ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም በድል መግባቱ (ዮሐ. 12፡1-19)

ማርያም ኢየሱስን ሽቶ ቀባችው (ዮሐ. 12፡1-11) ኢየሱስ የሚሞትበት ጊዜ ደርሷል፤ የቀረው ስድስት ቀናት ብቻ ነው። ክርስቶስ ቢታንያ በሚገኘው የማርያም፥ የማርታና የአልዓዛር ቤት ተቀምጧል። ይህ ቤተሰብ ለክርስቶስ ያለው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ፥ ለክብሩ ትልቅ ግብዣ አዘጋጁለት። ሦስቱ የቤተሰቡ አባላት ፍቅራቸውን ለክርስቶስ ገለጹ። ምናልባትም ታላቅ እኅታቸው የነበረችው ማርታ ክርስቶስን ታስተናግድ ነበር። አልዓዛር ከክርስቶስ ጋር በማዕድ ተቀምጦ ይበላ ነበር። […]

ማርያም ኢየሱስን ሽቶ መቀባቷ እና ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም በድል መግባቱ (ዮሐ. 12፡1-19) Read More »

ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣው (ዮሐ. 11:1-57)

ሞት የሰው ልጆች ሁሉ ዋነኛ ጠላት ነው። አዳምና ሔዋን ኃጢአት ከሠሩበት ጊዜ አንሥቶ ሥጋዊ ሞት የሰው ልጆች ሁሉ የመጨረሻው ጠላት ሆነ፡፡ ሁላችንም በሞት ተሸንፈናል። ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ ችግሮች መልስ ይሆን ዘንድ፥ ለዚህ ዋነኛ ጠላት መፍትሔ ሰጥቷል። ይህ አልዓዛር ከሞት የተነሣበት ሰባተኛው «ምልክት» ክርስቶስ በሞት ላይ ፍጹም ሥልጣን እንዳለው ከማሳየቱም በላይ፥ ለሁላችንም ተስፋ የሚሰጥ ምልክት

ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣው (ዮሐ. 11:1-57) Read More »

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለመሆኑ ከአይሁድ መሪዎች ጋር ተከራከረ (ዮሐ. 10፡22-42)

ከብዙ ጊዜ በኋላ የመታደስ በዓል ሲከበር ክርስቶስ አሁንም በቤተ መቅደስ ተገኝቶ ነበር። ይህ የመታደስ በዓል የሚከበረው በታኅሣሥ 165 ዓ.ዓ ሲሆን፥ በአንቲኮስ ኤጲፋነስ የረከሰውን ቤተ መቅደስ ይሁጻ መቃብያን መልሶ አደሰው። በዓሉ አይሁዶች ለመጨረሻ ጊዜ የተቀዳጁትን ድል ያመለከታል። ክርስቶስ በሃይማኖት መሪዎች ለሚመሩ አይሁዶች መሢሕነቱን ደጋግሞ ገልጾአል። የፈጸማቸው ተአምሮችና «ምልክቶች» መሢሕ መሆኑን ይመሰክራሉ። ይሁንና አይሁዶች እስከ አሁን ድረስ

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለመሆኑ ከአይሁድ መሪዎች ጋር ተከራከረ (ዮሐ. 10፡22-42) Read More »

ክርስቶስ የእግዚአብሔር መንጋ መልካም እረኛ ነው (ዮሐ. 10፡1-21)

የውይይት ጥያቄ፡- መዝሙር 23 እና ሕዝቅኤል 34ን አንብብ። ሀ) ከእነዚህ ምንባቦች ስለ እግዚአብሔር ምን እንማራለን? ለ) ከእነዚህ ምንባቦች እግዚአብሔር ፍጹም እረኛን ስለመላኩ ምን እንማራለን? ሐ) ስለ እረኛ አንዳንድ አሳቦችን ለማግኘት የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት እንብብ። የአይሁድ እረኞች ምን እንደሚመስሉና በኢትዮጵያ ከሚገኙ እረኞቹ እንዴት እንደሚለዩ ጠቅለል ያለ ማብራሪያ ጻፍ። ውብ ከሆኑት ምሳሌዎች መካከል አንዱ፥ እግዚአብሔር እንደ

ክርስቶስ የእግዚአብሔር መንጋ መልካም እረኛ ነው (ዮሐ. 10፡1-21) Read More »

ከመወለዱ ጀምሮ ዓይነ ስውር የነበረ ሰው መፈወስ (ዮሐ. 9:1-41)

ጌታሁንና ጽጌ ከተጋቡ ብዙ ዓመታት ቢሆናቸውም ልጆች ግን አልወለዱም። ጽጌ ብዙ ጊዜ ብታረግዝም፥ ልጁ ከመወለዱ በፊት ይሞታል። እንዲህ የመሰለውን ገጠመኝ ስናይ «ኃጢአት» የሠራው ማን ነው? ጌታሁን ወይስ ጽጌ?» በማለት እንጨነቃለን። ወርቅነሽ መንፈሳዊ ሴት ናት። አንድ ቀን ግን በጠና ታመመችና ለ10 ዓመት ያህል የአልጋ ቁራኛ ሆነች። አሁንም ታዲያ «ኃጢአት የሠራው ማን ነው?» ብለን እናስባለን። አንድ ክፉ

ከመወለዱ ጀምሮ ዓይነ ስውር የነበረ ሰው መፈወስ (ዮሐ. 9:1-41) Read More »

ኢየሱስ በዳስ በዓል ላይ ያስተማረው ትምህርት (ዮሐ. 8፡12-59)

በዮሐንስ 7 እና 8 በክርስቶስና በአይሁድ መካከል የተፈጠረው ትግል ተጠናክሮ ቀጥሏል። እነዚህ ሁለቱ ምዕራፎች ያካተቷቸው አሳቦች የተፈጸሙት ክርስቶስ የዳስ በዓልን ለማክበር በኢየሩሳሌም በነበረበት ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። ሀ. ክርስቶስ የዓለም ብርሃን ነው (ዮሐ 8፡12)። የዳስ በዓሉ አከባበር በተምሳሌታዊ ተግባራት የተሞላ መሆኑን ቀደም ብለን ተመልክተናል። ክርስቶስ ሕያው ወንዝ መሆኑን የገለጸው በመሠዊያው ላይ ውኃ ሲፈስ በመመልከቱ ላይሆን አይቀርም።

ኢየሱስ በዳስ በዓል ላይ ያስተማረው ትምህርት (ዮሐ. 8፡12-59) Read More »

ክርስቶስና በዝሙት የተያዘች ሴት (ዮሐ. 8፡1-11)

ተመስገን የአንድ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መጋቢ ነው። አንድ ቀን አንዲት የኳየር ዘማሪ የሆነች ወጣት ወደ እርሱ መጥታ ማርገዟን ገለጸችለት። ተመስገን በነገሩ በጣም ተናደደ። «የቤተ ክርስቲያናችንን ስም ያጠፋሽ ኃጢአተኛ ሴት ነሽ። እኛ እንዳንቺ ዓይነቷን ሴት አንፈልግም» አላት። ልጅትዋ በኃፍረት ተሸማቅቃ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ወጥታ ሄደች። ክርስቲያን የነበሩት ወላጆቿም በእርግዝናዋ ስላፈሩ ከቤታቸው ለቅቃ እንድትሄድ አስገደዷት። መሄጃ ስፍራ ስላጣች

ክርስቶስና በዝሙት የተያዘች ሴት (ዮሐ. 8፡1-11) Read More »

ክርስቶስ በዳስ በዓል ላይ ተገኘ (ዮሐ. 7፡1-53)

ዮሐንስ ከሚናገራቸው ነገሮች አንዱ የክርስቶስ ሕይወት በእግዚአብሔር አብ እጅ ውስጥ ባለው «ጊዜ» የተገዛ ነው። ቀደም ሲል ለክርስቶስ ተአምራትን ለማድረግ «ጊዜው» እንዳልነበር ተመልክተናል (ዮሐ 2፡4)። አሁን ኢየሱስ ሰዎችን ስለ መሢሕነቱ ለማሳመን ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ጊዜው እንዳልሆነ ተናግሯል። የክርስቶስ መንገድና ጊዜ ከሌሎች ሰዎች የተለየ ነው። ዮሐንስ እንደሚናገረው የኢየሱስ «ወንድሞች» ማለትም የዮሴፍና የማርያም ልጆች ኢየሱስ መሢሕ መሆኑን አልተቀበሉም።

ክርስቶስ በዳስ በዓል ላይ ተገኘ (ዮሐ. 7፡1-53) Read More »

ክርስቶስ የሕይወት እንጀራ ነው (ዮሐ. 6፡25-71)

የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ሰዎች ለሕይወት ወሳኝ ናቸው የሚሏቸውን ነገሮች ዘርዝር። ለ) እነዚህን ነገሮች ባለማግኘትህ ምክንያት የምታጣቸውን ነገሮች ዝርዝር። ሐ) የምንፈልጋቸው ወይም የምናጣቸው ነገሮች ለእኛ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች መሆናቸውን የሚያሳዩት እንዴት ነው? የምንፈልጋቸው ነገሮች ልባችን የት እንዳለና ለምንስ ነገር ትልቅ ዋጋ እንደምንሰጥ ያመለክታሉ። ቤተሰብ አስፈላጊ በመሆኑ፥ ለጋብቻና ለልጆች ትልቅ ግምት እንሰጣለን። ገንዘብ ጠቃሚ በመሆኑ ለጥሩ ሥራ

ክርስቶስ የሕይወት እንጀራ ነው (ዮሐ. 6፡25-71) Read More »

ክርስቶስ አምስት ሺህ ሰዎችን መመገቡ እና በውኃ ላይ መራመዱ (ዮሐ. 6፡1-24)

፩. ክርስቶስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ (ዮሐ 6፡1-15) ዮሐንስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ለማረጋገጥ የጠቀሰው አራተኛው ምልክት፥ ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መመገቡን ነው። ይህ በአራቱም ወንጌላት ውስጥ ከተጠቀሱት ጥቂት ተአምራት መካከል አንዱ ነው። ይህም ተአምሩ ደቀ መዛሙርቱን በጣም እንዳስደነቃቸው የሚያመለክት ነው። ይህ «ምልክት» ስለ ክርስቶስ ምን ያስተምራል? እራት መልእክቶች ያሉት ይመስላል፡- አንደኛው፥ ክርስቶስ የሥነ ፍጥረት

ክርስቶስ አምስት ሺህ ሰዎችን መመገቡ እና በውኃ ላይ መራመዱ (ዮሐ. 6፡1-24) Read More »