የሕይወት እንጀራ

የዮሐንስ ወንጌል

ኢየሱስ በሽተኞችን መፈወሱና ስለ ሥልጣኑ ከአይሁድ መሪዎች ጋር መከራከሩ (ዮሐ. 4፡43-5፡47)

፩. ሁለተኛው ምልክት፡ ኢየሱስ የሹሙን ልጅ ፈወሰ (ዮሐ 4:43-54) አንዳንድ ጊዜ የፈውስ ስጦታ ያለው ሰው በመካከላችን ከሌለ እግዚአብሔር ሰዎችን የሚፈውስ አይመስለንም። ወይም ደግሞ ታማሚውን ሰው የፈውስ አገልግሎት ወደሚካሄድበት ቤተ ክርስቲያን እንወስዳለን። ልጁ እንዲፈወስለት ወደ ኢየሱስ የመጣው ሹምም እንዲህ ዓይነት አመለካከት ነበረው። ኢየሱስ ወደ ቤቱ መጥቶ ልጁን እንዲዳስስለት ፈለገ። ኢየሱስ ግን የሹሙን ሰው እምነት በአንድ ደረጃ […]

ኢየሱስ በሽተኞችን መፈወሱና ስለ ሥልጣኑ ከአይሁድ መሪዎች ጋር መከራከሩ (ዮሐ. 4፡43-5፡47) Read More »

ኢየሱስ ድነትን (ደኅንነትን) ለሳምራዊቷ ሴት አብራራ (ዮሐ. 4፡1-42)

የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ የጾታ፥ የጎሣና የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ በሚገኙ ሰዎች መካከል የምታያቸውን የመናናቅ ሁኔታ ዘርዝር። እነዚህ አሉታዊ የመናናቅ ሁኔታዎች አንዳንድ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚንጸባረቁት እንዴት ነው? ለ) እነዚህ የመናናቅ ሁኔታዎች አንዳንድ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚከሰቱት እንዴት ነው? ሐ) ክርስቶስ በእነዚህ ሁለት የተለያዩ ቡድኖች መካከል ያለው ግንኙነት ምን ዓይነት መልክ እንዲኖረው

ኢየሱስ ድነትን (ደኅንነትን) ለሳምራዊቷ ሴት አብራራ (ዮሐ. 4፡1-42) Read More »

መጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን ወደ ኢየሱስ አመለከታቸው (ዮሐ. 3፡22-36)

ራስ ወዳድነት የምእመናን ብቻ ሳይሆን የመሪዎችም ሁሉ ትልቁ ችግር ነው። ሕይወታችንን የገዛው ራስ ወዳድነት ካልተወገደ በቀር ኢየሱስ የሚፈልገውን ዓይነት አመራር ተግባራዊ ልናደርግ አንችልም። ይህ ራስ ወዳድነት የተለያዩ ገጽታዎች አሉት። አንደኛው፥ አንድ መሪ የግል ጥቅሙን (ገንዘብ፥ ክብር) በሚፈልግበት ጊዜ፥ ራስ ወዳድነት ግላዊ ሊሆን ይችላል። ሁለተኛው፥ አንድ መሪ ከጠቅላላው የእግዚአብሔር ቤተሰብ ይልቅ የራሱን ቤተሰብ ወይም ጎሳ ለመጥቀም

መጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን ወደ ኢየሱስ አመለከታቸው (ዮሐ. 3፡22-36) Read More »

ኢየሱስ አዲስ ልደት ምን እንደሆነ ለኒቆዲሞስ ገለጸለት (ዮሐ. 3፡1-21)

በወንጌላት ውስጥ ፈሪሳውያን በቡድን ሆነው ኢየሱስንና አገልግሎቱን እንደ ተቃወሙ በሰፊው ተጠቅሷል። ኢየሱስ የመጣው እነርሱ ከጠበቁት በተለየ መንገድ ስለነበረ፥ የሃይማኖት መሪዎቹ መሲሕ መሆኑን ሊቀበሉ አልቻሉም፡፡ ደግሞም ኢየሱስ ሃይማኖታዊ ሕጎቻቸውን ባለመከተሉ፥ መንፈሳዊነቱንም ሊገነዘቡ ተስኖአቸው ነበር። ነገር ግን ኢየሱስ ከሃይማኖታዊነታቸው ባሻገር፥ ወደ ልባቸው ዘልቆ በመመልከት፥ በግብዝነታቸው ገስጾአቸዋል። ይህ በኢየሱስና በፈሪሳውያን መካከል የነበረው ግንኙነት ፍጥጫና ውጥረት የበዛበት ነበር። ይህም

ኢየሱስ አዲስ ልደት ምን እንደሆነ ለኒቆዲሞስ ገለጸለት (ዮሐ. 3፡1-21) Read More »

ኢየሱስ ነጋዴዎችን ከቤተ መቅደስ አባረረ (ዮሐ. 2፡12-25)

ኢየሱስ ሦስት አስፈላጊ ሃይማኖታዊ በዓሎች ላይ ለመገኘት ወደ ኢየሩሳሌም የሄደ ይመስላል። ዮሐንስ የሚያቀርባቸው ቀጣዮቹ ታሪኮችም በእነዚያ በዓላት ሰሞን የተካሄዱ ነበሩ። የመጀመሪያው በዓል ፋሲካ ነው። ከሦስት ዓመት በኋላ ኢየሱስ በዚህ ዕለት ይሞታል። ኢየሱስ በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ውስጥ የነበረውን አምልኮ በተመለከተ ጊዜ ስግብግብ ነጋዴዎች አምላኪዎቹን ይበዘብዙና የአምልኮውም መንፈስ በእንስሳት ግዢውና በገንዘብ ልውውጡ ምክንያት በተፈጠረው ጩኸት ታውኮ

ኢየሱስ ነጋዴዎችን ከቤተ መቅደስ አባረረ (ዮሐ. 2፡12-25) Read More »

የኢየሱስ የመጀመሪያው ምልክት፡- ውኃን ወደ ወይን ጠጅ ለወጠ (ዮሐ. 2፡1-11)

የኢየሱስ አገልግሎት ከይሁዳ ወደ ገሊላ ተሸጋገረ። ዮሐንስ ኢየሱስ በገሊላ ሳለ ስላጋጠመው ሁኔታ ብዙም የነገረን ነገር የለም። ሌሎች ተመሳሳይ ወንጌላት በገሊላ ላይ ሲያተኩሩ፣ ዮሐንስ ግን በይሁዳ ላይ ትኩረት አድርጓል። ኢየሱስ በገሊላ ሳለ ቤተሰቡና ደቀ መዛሙርቱ ለሰርግ ታድመው ነበር። እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ በአይሁዳውያንም ዘንድ ጋብቻ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶ ለአያሌ ቀናት የሚሰነብት ሥርዐት ነበር። ለእንግዳው ሁሉ የሚበቃ ምግብና

የኢየሱስ የመጀመሪያው ምልክት፡- ውኃን ወደ ወይን ጠጅ ለወጠ (ዮሐ. 2፡1-11) Read More »

መጥምቁ ዮሐንስ ኢየሱስን ለመግለጥ ያደረገው አገልግሎት (ዮሐ 1፡19-51)

የውይይት ጥያቄ፡- ዮሐ 1፡19-2፡25 አንብብ ሀ) ይህ ክፍል ስለ ኢየሱስ ምን ይነግረናል? ለ) በኢየሱስ ስለ ማመንና እርሱን ስለ መከተል ምን እንማራለን? ሌሎች ወንጌላት ቀደም ብለው ይህንኑ እንዳደረጉ ስለሚያውቅ ሐዋርያው ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ መጠመቅ አልጻፈም። ከዚህ ይልቅ መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ በሰጠው ምስክርነት ላይ አትኩሯል። ዮሐንስ ስለ ራሱና ስለ ኢየሱስ ማንነት ግልጽ ግንዛቤ ነበረው። ሀ. መጥምቁ

መጥምቁ ዮሐንስ ኢየሱስን ለመግለጥ ያደረገው አገልግሎት (ዮሐ 1፡19-51) Read More »

የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ (ዮሐ. 1-18)

አንድ ጊዜ፣ «ኢየሱስ ክርስቶስ መኖር የጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው? የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው መቼ ነው?» የሚል ጥያቄ ለቤተ ክርስቲያናችን መሪ አቀረብሁለት። ይህ የቤተ ክርስቲያን መሪ ወዲያው በማቴዎስና ሉቃስ ወንጌል ውስጥ ስለተጠቀሰው የኢየሱስ ታሪክ አስታወሰ። «መኖር የጀመረው ከማርያም ከተወለደበት ጊዜ አንሥቶ ነው። እግዚአብሔር በማርያም ማኅፀን ውስጥ ሳለ ሕይወትን ስለ ሰጠው እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው» ሲል መለሰልኝ። ብዙ

የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ (ዮሐ. 1-18) Read More »

የዮሐንስ ወንጌል መዋቅር እና አስተዋጽኦ

፩. የዮሐንስ ወንጌል መዋቅር በትምህርት ቤት ጥሩ ጽሑፍ ለማዘጋጀት መግቢያውን፥ ፍሬ ነገሩንና መደምደሚያውን በሚገባ ማዋቀር እንዳለብን አስተማሪዎቻችን ይነግሩናል። የዮሐንስ ወንጌልም በዚህ መንገድ የተዘጋጀ ነው። መግቢያ (ዮሐ 1፡1-18)። የነገረ መለኮት ምሑር የሆነው ዮሐንስ፥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እያስተማረ ነበር። በመሆኑም በመግቢያው ላይ ቃል የተባለው ኢየሱስ ከዘላለም ዘመናት በፊት ከእግዚአብሔር አብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ወደ ነበረበት ጊዜ

የዮሐንስ ወንጌል መዋቅር እና አስተዋጽኦ Read More »

የዮሐንስ ወንጌል ልዩ ገጽታዎች

፩. ዮሐንስ ከመጽሐፉ አብዛኛውን ክፍል ያዋቀረው፥ ሰባት ሰባት ነገሮችን ባካተቱ ሁለት ምድቦች ከፋፍሎ ነው። ሀ. ሰባት ምልክቶች፡- ማርቆስ ኢየሱስ የፈጸማቸውን ተአምራት (ለምሳሌ፣ ፈውስ) የኃይል መግለጫዎች ወይም ተአምራት ብሎ ሲጠራ፣ ዮሐንስ ግን «ምልክቶች» ማለትን መርጧል። ምልክት ወደ ሌላ ነገር የሚያመላክት ክስተት ነው። ኢየሱስ የፈጸማቸው ተአምራት ሁሉ መለኮታዊነቱንና መሢሕነቱን የሚያሳዩ ነበሩ። ብዙዎቹ ምልክቶች ደግሞ የማስተማሪያ አጋጣሚዎች ነበሩ።

የዮሐንስ ወንጌል ልዩ ገጽታዎች Read More »