1ኛ ቆሮ.16፡5-24
ጥያቄ 16. በዚህ ክፍል ላይ ስንት ነጥቦችን እንደሚጠቅስ በአጭሩ ዝርዝር። የደብዳቤው መደደሚያ ላይ በሆነው በዚህ ክፍል ሐዋርያው የተለያዩ ነጥቦችን ይጠቅሳል፤ በአጭሩ እንዘርዝራቸው። 1ኛ/ ከቁጥር 5-6፡- «በጉዞዬ እንድትረዱኝ» ሲል ገንዘብ መጠየቁ እንዳልነበረ ከ9፡15 እንረዳለን። ምናልባት አንዳንድ ለጉዞው የሚያስፈልገው ስንቅና ሸኚዎች የመሳሰሉ ነገሮች ይሆናሉ። 2ኛ/ ከቁጥር 7-9፡- በኤፌሶን ለአገልገሎት አንደሚሰነብት ይነግራቸዋል። «ሥራ የሞላበት ትልቅ በር ተከፍቶልኛልና» እግዚአብሔር […]