1ኛ ቆር.12:1-11
በቆርንቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በጉባኤያቸው ብዙ ስሕተቶች ነበሩ። እስከአሁን እንኳ ሁለት ስሕተቶችን ሐዋርያው እንዳረመላቸው አይተናል፤ እነርሱም ስለ ሴቶችና ስለቅዱስ ቁርባን ነበሩ። አሁን በዚህ ምዕራፍ ስለመንፈሳዊ ሥጦታዎች ይፈጽሙ የነበሩትን ስሕተቶች ያርምላቸዋል። ይህ የመንፈሳዊ ሥጦታ ጉዳይ በዘመናችንም አከራካሪ ሆና ስለመጣ የሐዋርያውን መምሪያ በጥንቃቄ በመመልከት የእኛንም ስሕተት በቃሉ መሠረት ማረም ይኖርብናል። ጥያቄ 6. የመንፈሳዊ ሥጦታዎች ዋና ዓላማ ምንድነው? […]