የሕይወት እንጀራ

2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች

የመለየት ልመና (2ኛ ቆሮ. 6፡11-7፡1)

ምንም እንኳን ቤተ ክርስቲያኗ በጳውሎስ ላይ የተለያዩ ችግሮችና ልብን የሚሰብሩ ሐዘኖች ብታደርስበትም፥ እርሱ ግን በቆሮንቶስ ውስጥ የሚገኙትን አማኞች በጣም ይወዳቸው ነበር። አስቀድሞ በታማኝነትና በፍቅር ተናግሮአቸው ነበር፤ አሁን ደግሞ ልባቸውን ይከፍቱለት ዘንድ በፍቅር ይጠይቃቸዋል። ጳውሎስ የወለዳቸው ልጆቹ የሚገባውን ፍቅር እንደ ነፈጉት አባት ያህል ሐዘኔታ ተሰምቶት ነበር (1ኛ ቆሮ. 4፡15 ተመልከት)።  ፍቅራቸውን የሚነፍጉት ለምን ነበር? ምክንያቱም የተከፋፈለ […]

የመለየት ልመና (2ኛ ቆሮ. 6፡11-7፡1) Read More »

ለምስጋና የቀረበ ልመና (2ኛ ቆሮ. 6፡ 1-10)

እነዚህ ሁለት ምዕራፎች ጳውሎስ ስለ አገልግሉቱ ለሚሰጠው ማብራሪያ እውነተኛ ማጠቃለያ ያቀርባሉ። ባለፍንባቸው ምዕራፎች ውስጥ ለአንባቢዎቹ፥ ከመከራዎቹ ባሻገር አገልግሎቱ ድል-ነሺ (ምዕ. 1-2) እና የከሰረ (ምዕ. 3) መሆኑን በመግለጽ፥ ከመታከት የተነሣ ከዓላማው ከቶውንም ዝንፍ እንደማይል ተናግሯል። ባላንጣዎቹ አገልግሎቱን ለግል ጥቅም ማግኛ እንዳዋለ አድርገው የከሰሱት ቢሆንም፥ ዳሩ ግን አገልግሎቱ እውነተኛ (ምዕ. 4) እና በእግዚአብሔር ላይ በተጣለ እምነት የተመሠረተ

ለምስጋና የቀረበ ልመና (2ኛ ቆሮ. 6፡ 1-10) Read More »

የክርስቶስ ተልዕኮ (2ኛ ቆሮ.5፡18-21)

በዚህ አንቀጽ ውስጥ ቁልፉ አሳብ ዕርቅ ነው። ሰው ከዓመፁ የተነሣ፥ የእግዚአብሔር ጠላትና ከእርሱ ጋር ከሚኖረው ኅብረት የራቀ ነበር። ከመስቀሉ ሥራ የተነሣ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ሰውንና እግዚአብሔርን ወደ አንድነት አመጣ። እግዚአብሔርም ከሰው ጋር በመታረቅ፥ ፊቱን በፍቅር ወደ ጠፋው ዓለም መለሰ። የዕርቅ መሠረታዊ ትርጉም «ሙሉ ለሙሉ መለወጥ» የሚል ሲሆን፥ በእግዚአብሔርና በጠፋው ዓለም መካከል የተደረገውን የግንኙነት ለውጥ ያመለክታል። 

የክርስቶስ ተልዕኮ (2ኛ ቆሮ.5፡18-21) Read More »

የአገልግሎት መንስዔዎች (2ኛ ቆሮንቶስ 5፡9-21)

ምን ጊዜም ቢሆን እምነታችንና አካሄዳችን ጎን ለጎን ሊሄዱ ይገባል። እግዚአብሔር ያደረገልንን በጎ ነገር ለእርሱም በአፀፋው መልካምን እንድናደርግ ሊያነቃቃን ስለሚገባ፥ ጳውሎስ ተግባርንና የእምነት ትምህርትን አይነጣጥላቸውም ነበር። ፊልፕስ ብሩክስ፥ «ክርስትና የፍቅር ልጅና የተግባር ወላጅ ያልሆነውን እውነት አይቀበልም» ብለዋል።  አንዲት ሴት ለሰባኪው፥ «በስብከትህ መጨረሻ ላይ «ስለዚህ በሚለው ቃል ደጋግመህ ባትጠቀም ኖሮ ግሩም ሰባኪ በወጣህ ነበር» ስትል ተናግራዋለች።  ጳውሎስ

የአገልግሎት መንስዔዎች (2ኛ ቆሮንቶስ 5፡9-21) Read More »

አስተማማኝ እምነት አለን (2ኛ ቆሮ. 4፡13-18)

የእምነት መንፈስ የሚለው ሐረግ «የእምነት እይታ ወይም አመለካከት» ማለት ነው። ጳውሎስ ወደ ልዩ የእምነት ስጦታ ሳይሆን (1ኛ ቆሮ. 12፡9)፥ ዳሩ ግን አማኝ ሁሉ ሊኖረው ወደሚገባ የእምነት አመለካከት እያመለከተ ነበር። ጳውሎስ ራሱን፥ «አመንሁ፤ ስለዚህም ተናገርሁ» የሚለውን የመዝሙር (116)፡10 መልእክት ከጻፈው ሰው ጋር ይመሳሰላል። ለእግዚአብሔር የሚሰጠው እውነተኛ ምስክርነት በእግዚአብሔር በማመን ላይ የተመሠረተ ሲሆን፥ ይህም እምነት የሚመጣው ከእግዚአብሔር

አስተማማኝ እምነት አለን (2ኛ ቆሮ. 4፡13-18) Read More »

የከበረ አገልግሎት አለን (2ኛ ቆሮ. 4፡1-6)

የዚህ ክፍል ዋናው መልእክት በቁጥር 1 እና 16 ውስጥ የተደጋገመ ሲሆን፥ ይኸውም «አንታክትም!» ወይም ጳውሎስ በቀጥታ እንዳሰፈረው፥ «ተስፋ አንቆርጥም» የሚል ነው። እርግጥ በጳውሎስ ሁኔታ ውስጥ ተስፋ ለመቁረጥ የሚያበቁ በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም፥ ዳሩ ግን ታላቁ ሐዋርያ ከተልዕኮው አላፈገፈገም ነበር። ይህን በመሰለው የሕይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ዝሎ እንዳይወድቅ ያበረታው ምን ነበር? ጳውሎስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ምን እንዳገኘ ያውቅ

የከበረ አገልግሎት አለን (2ኛ ቆሮ. 4፡1-6) Read More »

ስውርነት – ግልጽነት (2ኛ ቆሮ. 3፡12-18)

መጽሐፍ ቅዱስ መልእክቱን ለማስተላለፍ በተምሳሌቶች፥ በዘይቤዎችና በሌሉችም ሥነ ጽሑፋዊ ዘዴዎች ስለሚጠቀም፥ በመሠረቱ «(ሥዕላዊ) ገላጭ መጽሐፍ» ነው። ጳውሎስ በዚህ አንቀጽ ውስጥ፥ ክብር የሞላበትን ነጻነትና ግልጽነት ተጎናጽፎ ከጸጋ ሥር የሚገኘውን የክርስትና ሕይወት ለማብራራት፥ በሙሴና በፊት መጋረጃው ዓይነ-ርግብ ታሪክ ይጠቀማል። ጳውሎስ ከሙሴ ልምምድ ውስጥ ያገኘው ግንዛቤ፥ እኔና አንተ በዘጸአት 34፡29-25 ያለውን ክፍል በማንበብ ልናገኝ ከምንችለው በላይ የጠለቀ መንፈሳዊ

ስውርነት – ግልጽነት (2ኛ ቆሮ. 3፡12-18) Read More »

የሚደበዝዝ ክብር – የሚበዛ ክብር (2ኛ ቆሮ. 3፡7-11)

ይህ አንቀጽ የምዕራፉ እምብርት ስለ ሆነ፥ ከዘጸአት 34፡29-35 ጋር ተያይዞ መጠናት አለበት። የሕግ መሰጠት፥ የድንኳንና የቤተ መቅደስ አገልግሎት ውስጥ በትክክል ክብር ያልተለየው ስለ ነበረ፥ ጳውሎስም ቢሆን ይህን የአሮጌውን ኪዳን ክብር አልካደም። ዳሩ ግን እርሱ ለማጠናከር የፈለገው የአዲሱ ኪዳን የጸጋ ኪዳን ክብር እጅግ የሚበልጥ መሆኑንና ለዚሁም በርካታ ምክንያቶች እንዳሉት ነበር።  1. የአዲሱ ኪዳን ክብር ማለት መንፈሳዊ

የሚደበዝዝ ክብር – የሚበዛ ክብር (2ኛ ቆሮ. 3፡7-11) Read More »

ሞት – ሕይወት (2ኛ ቆሮ. 3፡4-6)

ጳውሎስ ምን ጊዜም ቢሆን ክብሩን ለራሱ ሳይሆን፥ ለእግዚአብሔር ላመስጠት የፈጠነ ነበር። መተማመኛው እግዚአብሔር እንደ መሆኑ፥ ብቃቱም የሚመጣለት ከእግዚአብሔር ነበር። ጳውሎስ ንቁና በሚገባ የተማረ ሰው ቢሆንም፥ በጌታ እንጂ በራሱ ብቃት ላይ አልተደገፈም።  በርግጥ የሕግ መምህራን፥ ማንኛውም ሰው ሕግን በመጠበቅ መንፈሳዊ ሊሆን እንደሚችል አስተምረዋል። ዳሩ ግን የሕግ ትምህርት የሰዎችን ራስ-ወዳድነት አዝማሚያ የሚያጎላብት ነው። በእግዚአብሔር ጸጋ ላይ የምናተኩር

ሞት – ሕይወት (2ኛ ቆሮ. 3፡4-6) Read More »

የድንጋይ ጽላት – የሰው ልብ ጽላት (2ኛ ቆሮ. 3፡1-3)

እውነተኛ ነገር በሚኖርበት ጊዜ ሁሉ፥ ሰዎች የማስመሰል ተግባር ሲፈጽሙ ይታያል። ሌላው ቀርቶ የኪነ-ጥበብ ሃያሲያን እንኳ «ምርጥ ሥራዎች» ተብለው በቀረቡ አስመሳይ የሥዕላ ሥዕል ቅቦች ተሞኝተዋል፤ እንደዚሁም እውነተኛ አሳታሚዎችም «ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸው መዛግብት» እንደ ሆኑ በመቁጠር የገዙዋቸው ንብረቶች በማስመሰል የተሠሩ መሆናቸውን ዘግይተው ይረዳሉ። ይህን የመሳሰለውን ማጭበርበር ስንመለከት፥ ሄነሪ ዎርድ ቢቸር የተባሉት ሰው «ለውሸት ምንጊዜም ምርኩዙ እውነት ነው»

የድንጋይ ጽላት – የሰው ልብ ጽላት (2ኛ ቆሮ. 3፡1-3) Read More »