የሕይወት እንጀራ

2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች

ድል-ነሺ እምነት (2ኛ ቆሮ. 2፡12-17)

በእስያ የተዘረጉት የጳውሎስ ዕቅዶች ሙሉ ለሙሉ የከሸፉ ይመስል ነበር። ቲቶ የት ነበር? በቆሮንቶስ ያለውስ ሁኔታ ምን ይመስል ነበር? ጳውሎስ በጢሮአዳ ለአገልግሉት የተከፈቱ በሮች ቢኖሩም፥ በእነዚያ በሮች ውስጥ እንደምኞቱ ለመመላለስ የልብ ሰላም አልነበረውም። በሰብዓዊ አባባል፥ ጦርነቱ በሰይጣን ድል-አድራጊነት የተፈጸመ ይመስል ነበር።  የቀረው ነገር ቢኖር የጳውሎስ ድል-አድራጊ እምነት ብቻ ነበር! በእርግጥም የነበረበትን ሁኔታ ተቋቁሞ፥ «ለአምላክ ምስጋና ይሁን!» […]

ድል-ነሺ እምነት (2ኛ ቆሮ. 2፡12-17) Read More »

ንጹሕ ሕሊና (2ኛ ቆሮ. 1፡12-24)

«ፕሮፋይልስ እን ከሬጅ» በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ፥ ጆን ኤፍ ኬኔዲ፥ «ታላላቅ ፈተናዎች ታላላቅ ሰዎችንና ታላላቅ የጀግንነት ሥራዎችን ያስገኛሉ» በማለት ጽፈዋል።  በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ የሚደርሰው ፈተና ሰውየውን እንደሚያንጸው እውነት ቢሆንም፥ በሌላም በኩል ፈተናው የሰውየውን የመንፈስ ጥንካሬ እንደሚያመለክት የታወቀ ነው። ጲላጦስ ታላቅ ፈተና ተጋርጦበት ነበር፤ ዳሩ ግን ፈተናውን ያስተናገደበት መንገድ ጀግንነት ወይም ታላቅነት አላጎናጸፈውም። የሕይወታችን አስቸጋሪ ሁኔታዎች

ንጹሕ ሕሊና (2ኛ ቆሮ. 1፡12-24) Read More »

ብንወድቅም – አልተጣልንም! (2ኛ ቆሮንቶስ 1፡1-11 )

«እናንተ የምትገምቱት፥ በሕይወቴ ውስጥ አንዳችም ውጣ ውረድ እንዳልገጠመኝ፥ በምትኩ የሠመረ መንፈሣዊ ሕይወት እንደ መሪ በትፍስሕት የተሞላ ሰላማዊ ኑሮ እንደ ኖረኝ አድርጋችሁ ነው። ጨርሶ ያላጋጠመኝ ነገር ነው! እኔ ብዙውን ጊዜዬን በጉስቁልና ያሳለፍሁና ነገር ዓለሙ የጨለመብኝ ሰው ነኝ።»  ከላይ የቀረበውን ጽሑፍ ያሰፈሩት በዘመናቸው «በእንግሊዝኛ ተናጋሪ ህብረተሰብ ውስጥ ከሁሉም የላቁ ሰባኪ» የሚል ቅጽል የተቸራቸው ዶክተር ጆን ሄንሪ ጆውት

ብንወድቅም – አልተጣልንም! (2ኛ ቆሮንቶስ 1፡1-11 ) Read More »

ብንወድቅም – አልተጣልንም! (2ኛ ቆሮንቶስ 1፡1-11)

«እናንተ የምትገምቱት፥ በሕይወቴ ውስጥ አንዳችም ውጣ ውረድ እንዳልገጠመኝ፥ በምትኩ የሠመረ መንፈሣዊ ሕይወት እንደ መሪ በትፍስሕት የተሞላ ሰላማዊ ኑሮ እንደ ኖረኝ አድርጋችሁ ነው። ጨርሶ ያላጋጠመኝ ነገር ነው! እኔ ብዙውን ጊዜዬን በጉስቁልና ያሳለፍሁና ነገር ዓለሙ የጨለመብኝ ሰው ነኝ።»  ከላይ የቀረበውን ጽሑፍ ያሰፈሩት በዘመናቸው «በእንግሊዝኛ ተናጋሪ ህብረተሰብ ውስጥ ከሁሉም የላቁ ሰባኪ» የሚል ቅጽል የተቸራቸው ዶክተር ጆን ሄንሪ ጆውት

ብንወድቅም – አልተጣልንም! (2ኛ ቆሮንቶስ 1፡1-11) Read More »

ጳውሎስ እውነተኛ ሐዋርያነቱን በመግለጽ ተከራከረ (2ኛ ቆሮ. 10፡1-13፡14)

ቲቶ በመቄዶንያ ከጳውሎስ ጋር በተገናኘ ጊዜ አብዛኛዎቹ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች እንደሚደግፉት ገለጸለት። ነገር ግን ጳውሎስን አጥብቀው የተቃወሙ ሌሎችም ሰዎች ነበሩ። ስለሆነም፥ በመልእክቱ መጨረሻ አካባቢ ጳውሎስ ሐዋርያነቱን ለተቃወሙት ሰዎች ጠንካራ የመከላከያ ሙግት ያቀርባል። የውይይት ጥያቄ፡– 1ኛ ቆሮ. 10-13 አንብብ። ጳውሎስ እውነተኛ የክርስቶስ ሐዋርያ መሆኑን እንደሚያረጋግጡ የገለጻቸውን የተለያዩ ነገሮች ዘርዝር። ሀ. ጳውሎስ የሚቃወሙትን ሰዎች እንደሚቀጣ ገልጾአል (2ኛ ቆሮ.

ጳውሎስ እውነተኛ ሐዋርያነቱን በመግለጽ ተከራከረ (2ኛ ቆሮ. 10፡1-13፡14) Read More »

ጳውሎስ ለአይሁድ ክርስቲያኖች ስለሚሰጠው የገንዘብ ዕርዳታ ማብራሪያ ሰጠ (2ኛ ቆሮ. 8፡1-9፡15)

አይናለም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረች ጊዜ በገንዘብ እጥረት ትቸገር ነበር። አሥራት መክፈል እንዳለባት ብታውቅም፥ «እኔ በጣም ድሀ ነኝ፤ ለመጻሕፍት መግዣና ለመተዳደሪያ ገንዘብ ያስፈልገኛል፤ ተመርቄ ሥራ ላይ ስሰማራ እከፍላለሁ» ትል ነበር። ከተመረቀች በኋላ በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ ሥራ ተሰጣት። የሚከፈላት ደመወዝ አነስተኛ በመሆኑ አንዳንድ ጊዜ የቤት ኪራይ፥ የምግብና የልብስ ወጪ ለመሸፈን ትቸገር ነበር። ስለሆነም፥ «እስካገባ

ጳውሎስ ለአይሁድ ክርስቲያኖች ስለሚሰጠው የገንዘብ ዕርዳታ ማብራሪያ ሰጠ (2ኛ ቆሮ. 8፡1-9፡15) Read More »

2ኛ ቆሮ. 6፡3-7፡1

መንፈሳዊ መሪ ሰዎች አምነው የሚድኑበትን ዕድል ለመስጠት ሲል በመከራ ይታገሣል (2ኛ ቆሮ. 6፡3-13)። ጳውሎስ በሕይወቱና በአኗኗሩ ምክንያት ማንም ሰው ከወንጌሉ እንዲያፈገፍግ አልፈለገም ነበር። የሚያከናውነው ተግባር ሁሉ ሰዎች ከክርስቶስ ፊታቸውን መልሰው የኋላ ኋላ ለኩነኔ እንዲጋለጡ የሚያደርግ ሳይሆን፥ ለማመን ሁኔታዎችን የሚያመቻችላቸው እንዲሆን ቆርጦ ነበር። ከዚህም የተነሣ፥ ሀ) ጳውሎስ ሰዎች ወንጌልን ይሰሙ ዘንድ አስፈላጊ የሆነውን መከራ ሁሉ በትዕግሥት

2ኛ ቆሮ. 6፡3-7፡1 Read More »

መንፈሳዊ መሪ እግዚአብሔርንና ሰውን ለማስታረቅ የሚሻ የክርስቶስ አምባሳደር ነው (2ኛ ቆሮ. 5፡11-6፡2)።

ጳውሎስ ሰዎችን ለማስደሰት ብሎ ያገለግላል የሚል ወቀሳ ተሰንዝሮበት ነበር። ነገር ግን አንድ ቀን በእግዚአብሔር ፊት ለፍርድ እንደሚቀርብ ከተናገረ በኋላ፥ ጳውሎስ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሚፈራ ገልጾአል። ሰውን መፍራት ወይም ሰውን ለማስደሰት መጣር ዘላለማዊ ፍርድ ያስከትልበት ነበር። ተጨማሪ መከራ ቢያስከትልበትም እንኳ ጳውሎስ ለክርስቶስ የሚያበረክተውን አገልግሎት በቅንዓት የቀጠለው ክርስቶስን ለማስደሰት በመፈለጉ ነበር። አንዳንድ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ጳውሎስ የሚያከናውናቸውን ተግባራት በማየት

መንፈሳዊ መሪ እግዚአብሔርንና ሰውን ለማስታረቅ የሚሻ የክርስቶስ አምባሳደር ነው (2ኛ ቆሮ. 5፡11-6፡2)። Read More »

መንፈሳዊ መሪ ወደፊት ዘላለማዊ ሽልማት እንደሚያገኝ ስለሚተማመን በአገልግሎቱ ይጸናል (2ኛ ቆሮ. 4፡13-5፡10)።

ጳውሎስ መከራ መቀበልን ይወድ ነበር? አይወድም። እንግዲያው ነገሮች አስቸጋሪ ሲሆኑበት፥ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖችና ሌሎችም ሲቃወሙት፥ ስሙን ሲያጎድፉ፥ ዓለም ስታሳድደው ለምን አገልግሎቱን አላቋረጠም? የዚህ ምሥጢሩ ጳውሎስ ዓይኖቹን ከሞት በኋላ በሚሆነው ሁኔታ ላይ ማኖሩ ነው። ሀ. ጳውሎስ ቢሞትም እንኳ እንደሚነሣ ስለሚያውቅ መከራን እየተጋፈጠ ወንጌሉን ሰብኳል (2ኛ ቆሮ. 4፡13-15)። ሞትን ስለማይፈራ ከመሰከርህ ትሞታለህ ቢባል እንኳ አገልግሎቱን አያቋርጥም ነበር። ከዚህም

መንፈሳዊ መሪ ወደፊት ዘላለማዊ ሽልማት እንደሚያገኝ ስለሚተማመን በአገልግሎቱ ይጸናል (2ኛ ቆሮ. 4፡13-5፡10)። Read More »

በሸክላ ውስጥ የተቀመጠ ክቡር ዕቃ (2ኛ ቆሮ. 4፡1-12)

ንጋቱ ከአንድ ከታወቀ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ ተመርቆ የአንዲት ታላቅ ቤተ ክርስቲያን መጋቢ ሆነ። ንጋቱ በትምህርቱ ስለሚኩራራ ኮሌጅ ውስጥ የተማረውን የግሪክና የዕብራይስጥ ቋንቋ ለጉባኤው በማቅረብ ልታይ ባይነትን ያበዛ ነበር። ንጋቱ ይበልጥ እውቅና እያገኘ ሲሄድ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሽማግሌዎች የሚያቀርቡትን አሳብ መቀበሉን አቆመ። ብዙ ገንዘብና ሥልጣን ለማግኘት ሲል የተለያዩ ተግባራትን አከናወነ። አብዛኞቹ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ስሜታዊና ሞቅ ያሉ

በሸክላ ውስጥ የተቀመጠ ክቡር ዕቃ (2ኛ ቆሮ. 4፡1-12) Read More »