የሕይወት እንጀራ

2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች

መንፈሳዊ መሪ ለአዲሱ ኪዳንና ለእግዚአብሔር የማስቻል ኃይል አጽንኦት ይሰጣል (2ኛ ቆሮ. 2፡14-3፡18)።

ጳውሎስ ወደ በኋላ ቲቶን አግኝቶ ስለ ቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ንስሐና የአመለካከት ለውጥ ስለመስማቱ ይናገራል። ይህ የልብ ለውጥ የጳውሎስን ልብ በደስታ ሞላው (2ኛ ቆሮ. 7፡5-16)። ከቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ጋር ስለነበረው ግንኙነት ማሰብ ሲጀምር አእምሮው እግዚአብሔርን ስለማገልገሉ አስደናቂ ምሥጢር ያስብ ጀመር። ስለሆነም፥ ከ2ኛ ቆሮ. 2፡14 እስከ 2ኛ ቆሮ. 7፡1 ድረስ ጳውሎስ ስለ አገልግሎቱና እግዚአብሔር በመሪዎች ሕይወት ውስጥ ስለሚያከናውናቸው ተግባራት […]

መንፈሳዊ መሪ ለአዲሱ ኪዳንና ለእግዚአብሔር የማስቻል ኃይል አጽንኦት ይሰጣል (2ኛ ቆሮ. 2፡14-3፡18)። Read More »

ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ስለ ራሱ ሁኔታ እብራራላቸው (2ኛ ቆሮ. 1፡12-2፡13)

ጳውሎስ በዕቅዱ መሠረት ለምን እንዳልጎበኛቸው ገለጸላቸው (2ኛ ቆሮ. 1፡12-2፡4) የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ለሌሎች የገባኸውን ቃል መጠበቅ አስፈላጊ የሚሆነው ለምን ይመስልሃል? ለ) መሪዎች ለምእመናን የገቧቸውን የተስፋ ቃሎች በማይፈጽሙባቸው ጊዜያት ምን ይከሰታል? ሐ) ለመሪዎች በሚያክናውኗቸው ተግባራት ሁሉ በንጹሕ ሕሊና መመላለስ አስፈላጊ የሚሆነው ለምንድን ነው? መ) ስለ ራስህ ሕይወት አስብ። ሰዎች ቢያውቋቸው የሚያሳፍሩህ አንዳንድ ነገሮች ምን ምንድን ናቸው?

ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ስለ ራሱ ሁኔታ እብራራላቸው (2ኛ ቆሮ. 1፡12-2፡13) Read More »

እግዚአብሔር የመጽናናት አምላክ (2ኛ ቆሮ. 1፡1-11)

ጌታሁን ከቦታ ቦታ እየተጓጓዘ ስለ ክርስቶስ የሚመሰክር ፍሬያማ ወንጌላዊ ነበር። በአገልግሎቱ ውጤታማ ነበር። አንድ ቀን ተሳፍሮ የሚጓዝበት አውቶቡስ ተገልብጦ ገደል በመግባቱ ጌታሁን ለሽባነት ተዳረገ። እየተጓዘ የሚያገለግለው አገልግሎቱ ተቋረጠ። ብዙ ክርስቲያኖች ወደ እርሱ መጥተው እንዲፈወስ ጸለዩለት። ምንም እንኳን በእግዚአብሔር ላይ ጠንካራ እምነት ቢኖረውም ሊፈወስ አልቻለም። ስለሆነም፥ «እግዚአብሔር ይህ በእኔ ላይ እንዲደርስ ለምን ፈቀደ? አንዳንድ ክርስቲያኖች በከፍተኛ

እግዚአብሔር የመጽናናት አምላክ (2ኛ ቆሮ. 1፡1-11) Read More »

የ2ኛ ቆሮንቶስ መዋቅር እና አስተዋጽኦ

የ2ኛ ቆሮንቶስ መዋቅር የ2ኛ ቆሮንቶስ መልእክት ከአንዱ ወደ ሌላው ርእሰ ጉዳይ ቢያመራም፥ በሦስት ክፍሎች ሊከፈል ይችላል። ጳውሎስ የሚደግፉትን አብዛኛዎቹን የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ያመሰግናቸዋል (2ኛ ቆሮ. 1-7)። ጳውሎስ በዕቅዱ መሠረት ለምን ወደ ቆሮንቶስ እንዳልመጣ ያብራራል። የክስተቶችን ቅደም ተከተል በመስጠት ቆሮንቶስን በቁጣ ለመጎብኘት ወይም በተቃወሙት ጊዜ ሐዋርያዊ ሥልጣኑን ለመጠቀም እንዳልፈለገ ያስረዳል። ንስሐ ገብተው የእርሱን ሐዋርያነት መቀበላቸው እንዳስደሰተውም ይገልጻል።

የ2ኛ ቆሮንቶስ መዋቅር እና አስተዋጽኦ Read More »

የ2ኛ ቆሮንቶስ ዓላማ እና ልዩ ባሕሪያት

የ2ኛ ቆሮንቶስ ዓላማ እንደዛሬው ሁሉ የቀድሞዋ ቤተ ክርስቲያንም ከሐሰተኛ አስተማሪዎች ጋር ታግላለች። ጳውሎስ አብያተ ክርስቲያናትን በተከለበት ስፍራ ሁሉ የሐሰት አስተማሪዎች ወንጌሉን ለመበረዝ ይጥሩ ነበር። ይህንን ያደርጉ የነበረው በሁለት ዐቢይ መንገዶች ነበር። አንደኛ፥ ሰዎች የእግዚአብሔርን መልእክተኛ እንዲጠራጠሩ ለማድረግ ይጥሩ ነበር። በዚህ መሠረት የሐሰት አስተማሪዎቹ የጳውሎስን እውነተኛነት በማጣጣል ሰዎች የጳውሎስን ትምህርት እንዲጠራጠሩ ያደርጉ ነበር። ሁለተኛ፥ የወንጌሉን መልእክት

የ2ኛ ቆሮንቶስ ዓላማ እና ልዩ ባሕሪያት Read More »

የ2ኛ ቆሮንቶስ መግቢያ

ስንታየሁ ከመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ በቅርቡ ተመርቆ አባል በነበረበት የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መጋቢ በመሆን ያገለግል ጀመር። መጀመሪያ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ ይከናወኑ ጀመረ። እምነቱን ለዓለማውያን ከማካፈሉም በላይ፥ በየእሑዱ የእግዚአብሔርን ቃል ማጥናትና መስበክ ያስደስተው ነበር። ብዙም ሳይቆይ ግን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ችግሮች መኖራቸውን ተገነዘበ። ሁለት ሽማግሌዎች ተጣልተው መነጋገር አቁመዋል። ሁለት የኳዬር መዘምራን ወሲባዊ ኃጢአት እየፈጸሙ ይመላለሱ ነበር። እነዚህ

የ2ኛ ቆሮንቶስ መግቢያ Read More »