የሕይወት እንጀራ

2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ

የጳውሎስ የማጠቃለያ ማበረታቻ እና የስንብት ሰላምታ (2ኛ ጢሞ. 4፡1-22)

ጳውሎስ ጢሞቴዎስ የእግዚአብሔር ታማኝ አገልጋይ ሆኖ ሊኖር ስለሚችልበት መንገድ የማጠቃለያ ማበረታቻ ይሰጠዋል (2ኛ ጢሞ. 4፡1-5)። ጳውሎስ የቤተ ክርስቲያን መሪ ተግባር ምን መሆን እንዳለበት ጠቅለል አድርጎ በመግለጽ ለጢሞቴዎስ ያቀረበውን ምክር ይደመድማል። ጢሞቴዎስ እግዚአብሔር ሕይወቱን እየተመለከተ መሆኑን ማስታወስ ያስፈልገው ነበር። አንድ ቀን ደግሞ በሕያዋንና በሙታን ላይ በሚፈርድ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ይቀርባል። አንድ መሪ ምን ማድረግ እንዳለበት፥ እንዴት […]

የጳውሎስ የማጠቃለያ ማበረታቻ እና የስንብት ሰላምታ (2ኛ ጢሞ. 4፡1-22) Read More »

በመጨረሻዎቹ ቀናት የሚኖረው ክሕደት እና ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ የሰጠው ዐደራ (2ኛ ጢሞ. 3፡1-17)

ጳውሎስ በመጨረሻው ዘመን የሰዎች ባሕሪ ምን እንደሚመስል ይገልጻል (2ኛ ጢሞ. 3፡1-9) ብዙውን ጊዜ ነገሮች ከዓመት ዓመት እየተሻሻሉ ይሄዳሉ ብለን እናስባለን። ብዙ ሰዎች ትምህርት የተከታተሉ አዳዲስ ሥራዎችን በመፍጠር ብዙ ገንዘብ ያገኛሉ፥ ከግብርና ቦታቸው ራቅ ባሉ አካባቢዎች የተሻሉ ቤቶችን ይሠራሉ፥ የራሳቸውን ቴሌቪዥን፥ መኪና ወዘተ… ይገዛሉ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን በመሳሰሉ ተቋማት አማካኝነት በዓለም ላይ ብዙ ገንዘብና ብዙ ሥራም

በመጨረሻዎቹ ቀናት የሚኖረው ክሕደት እና ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ የሰጠው ዐደራ (2ኛ ጢሞ. 3፡1-17) Read More »

ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ቆራጥ ወታደር ሆኖ ለክርስቶስ እንዲሠራ ያደፋፍረዋል (2ኛ ጢሞ. 2፡1-26)

ስደት ሲጠናከርና አማኞች ለእምነታቸው የመሞታቸው ጉዳይ ቁርጥ ሲሆን፥ አማኞች በተለይም የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሊያስታውሷቸው የሚገቧቸው ወሳኝ ነገሮች ምን ምንድን ናቸው? እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ ስለመመላለስ የሚያስተምሩ ቁልፍ እውነቶች ምን ምንድን ናቸው? እምነታችን ለቀጣዩ ትውልድ በጥንቃቄ መተላለፉን እንዴት ልናረጋግጥ እንችላለን? ጳውሎስ የእግዚአብሔር ሕዝብ ታማኝ መሪ መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ ለጢሞቴዎስ ያብራራል። ሀ) ታማኝ የቤተ ክርስቲያን መሪ

ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ቆራጥ ወታደር ሆኖ ለክርስቶስ እንዲሠራ ያደፋፍረዋል (2ኛ ጢሞ. 2፡1-26) Read More »

ታማኝ ስለ መሆን የተሰጠ ማበረታቻ (2ኛ ጢሞ 1፡1-18)

ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ለወንጌሉ በቆራጥነት እንዲቆም ያበረታታዋል (2ኛ ጢሞ 1፡1-14) ከአርባ ለሚበልጡ ዓመታት ገብረ እግዚአብሔር እግዚአብሔርን በታማኝነት ሲከተል ቆይቷል። በግል ሕይወቱ፥ እግዚአብሔርን በሙሉ ልቡ ለመውደድና በመንፈሳዊ ሕይወቱ ለማደግ ሲሻ ቆይቷል። በአደባባይ ሕይወቱም እንዲሁ፥ ገብረ እግዚአብሔር በምስክርነትና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተለያዩ እርዳታዎችን በማድረግ እግዚአብሔርን ለማገልገል ጥሯል። ምንም እንኳን የቤተ ክርስቲያኒቱ ሽማግሌ ሆኖ ባይመረጥም፥ በየሳምንቱ በማለዳ ወደ ቤተ

ታማኝ ስለ መሆን የተሰጠ ማበረታቻ (2ኛ ጢሞ 1፡1-18) Read More »

የ2ኛ ጢሞቴዎስ መዋቅር እና አስተዋጽኦ

የ2ኛ ጢሞቴዎስ መዋቅር 2ኛ ጢሞቴዎስ እንደ መጽሐፍ ሳይሆን ጳውሎስ ከመሞቱ በፊት የእምነት ልጁ ለሆነው ጢሞቴዎስ የሰጠውን ግላዊ ምክር የሚያስተላልፍ ሆኖ ስለቀረበ፥ ይህንንም መልእክት በአስተዋጽኦ መልክ ማቅረቡ አስቸጋሪ ነው። ጳውሎስ ጢሞቴዎስ በስደት ውስጥ እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ እንዴት መመላለስ እንዳለበት አስተዋይነት የተሞላበትን ምክር ይለግሰዋል። ይህ መጽሐፍ በአራት ክፍሎች ሊከፈል ይችላል። ጳውሎስ ጢሞቴዎስ እንዴት እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ ለመመላለስ

የ2ኛ ጢሞቴዎስ መዋቅር እና አስተዋጽኦ Read More »

የ2ኛ ጢሞቴዎስ ዓላማ እና ልዩ ባሕሪያት

የ2ኛ ጢሞቴዎስ ዓላማ የመጀመሪያው ዓላማ፡- ጢሞቴዎስ ከሚጋፈጠው ስደት ባሻገር በእምነቱ እንዲበረታ ለማሳሰብ። በመጨረሻዎቹ ጥቂት ወራት ጳውሎስ ብቸኝነት ተጫጭኖት ነበር። ከጽሑፎቹ እንደምንመለከተው፥ ጳውሎስም እንደኛ ሰው በመሆኑ በአንዳንድ አማኞች ተግባራት ጥልቅ ስሜት ጉዳት ደርሶበት ነበር። ስደትን ከመፍራታቸው የተነሣ ይመስላል ብዙዎቹ የጳውሎስ የግል ጓደኞችና የአገልግሎት ተባባሪዎች ብቻውን ጥለውት ወደየቤቶቻቸው ገቡ። ጳውሎስ ከእስያ አውራጃ ሁሉም ሰው እንደ ተወው ይናገራል።

የ2ኛ ጢሞቴዎስ ዓላማ እና ልዩ ባሕሪያት Read More »

የ2ኛ ጢሞቴዎስ በማን ተጻፈ፣ ለማን ተጻፈ፣ መቼና የት ተጻፈ

የ2ኛ ጢሞቴዎስ ጸሐፊ የውይይት ጥያቄ፡– 2ኛ ጢሞ. 1፡1 አንብብ። ሀ) የመጽሐፉ ጸሐፊ ማን ነው? ለ) መጽሐፉ የተጻፈው ለማን ነው? ሐ) 2ኛ ጢሞቴዎስን በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገብ ቃላት ውስጥ በመመልከት ስለ ጸሐፊው፥ መልእክቱን ስለሚቀበሉት ሰዎችና ስለ መጽሐፉ የተገለጸውን ጠቅለል አድርገህ ጻፍ። ጳውሎስ የ2ኛ ጢሞቴዎስ መልእክቱን የጀመረው እንደተለመደው ራሱን፥ «በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነው ጳውሎስ» በማለት ነበር።

የ2ኛ ጢሞቴዎስ በማን ተጻፈ፣ ለማን ተጻፈ፣ መቼና የት ተጻፈ Read More »

የሁለተኛ ጢሞቴዎስ መግቢያ

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ወደሚካሄደው የቀብር ሥነ ሥርዓት እየሄድክ ነው እንበል፥ ወደ ቤተ ክርስቲያኒቱ ገብተህ ስትቀመጥ፥ ከቤተ ክርስቲያኒቱ መድረክ ላይ የተኛው አስከሬን ያንተው መሆኑን ትገነዘባለህ። የራስህን የቀብር ሥነ ሥርዓት እየተመለከትህ ነው እንበል። ፕሮግራሙን እየተከታተልህ እያለ፥ ከልጆችህ ታላቁ ብድግ ብሎ በልጅነቱ ከአንተ ጋር ስለነበረው ግንኙነትና ስለ አንተ የሚያስታውሳቸውን ነገሮች ለማኅበረ ምእመናኑ ይናገራል። ሁለተኛ፥ ባለቤትህም በበኩሏ ባሏ እንደ

የሁለተኛ ጢሞቴዎስ መግቢያ Read More »