ምዕራፍ 8 – ጸሎት

ስለጸሎት ማወቅ ለምን ያስፈልጋል?

‹‹ጎሽ፣ ይህች ልዩ ሴት መጣችልኝ፡፡ አብራኝ ስትሆን እጅግ ደስተኛ እሆናለሁ!›› ሲል አሰብ ብራየን በውስ፡፡

ብሪየን፣ የአስር አመት ልጅ ሲሆን በከፍተኛ የኦቲዝም በሽታ ይሰቃያል፡፡ ጥቁር ቡኒ ፀጉር፣ ሰማያዊ የአይን ብሌን ያለው መልከ መልካም ልጅ ነው፡፡ በአእምሮው ላይ ያለው ችግር እስረኛ ባየሰደርገው ኖሮ በመልኩ ብቻ በትምህርት ቤቱ ውስጥ ታዋቂ ልጅ ይሆን ነበር፡፡

እናቱ ሞኒካ ብራየንን ልጇን ከወለሉ ላይ አንስታ የእርሱ ብቸኛ አለም ወደ ሆነችው ክፍሉ ውስጥ ወደ ምትገኘው ጠረጴዛው ወሰደችው፡፡ ምሳ አቀረበችለት፡፡ ምሳው ሁል ጊዜ እንደሚበላው የተጠበሰ አይብ ሳንዲዊች፣ በአራት እኩል ቦታ የተቆራረጠ ግማሽ ፓም፣ ሦስት የስኒከር ዱድል ብስኩቶች እና አንድ ብርጭቆ ወተት ነበር፡፡

‹‹እንደገና ሰራችልኝ አይደል! ምርጥ ነው! ልክ እንደምወደው!›› አለ ብራየን ከፊቱ ላይ ማንም ሊያነበው ባይችልም በውስ እጅግ ደስ እየተሰኘ፡፡ “የምትገርም ሴት ናት! ከእሷ ውጭ እንዴት መኖር እንደምችል አላውቅም››፣ አለ በልቡ።

ሞኒካ ልጇ ምግቡን በስርዐት ሲመገብ እየተመለከተች፣ ጮክ ብላ ‹‹እወድሃለው ብራየን›› አለችው፡፡ ‹‹ምኞቴ ምን ያህል እንደማፈቅርህ እንድታውቅልኝ ነው፡፡›› ብላ ማጅራቱን በፍቅር አበስ አበስ አደረገችለት፡፡

ብራየን ስቅጥጥ አለው፡፡ በመደናገጥ ‹‹ምንድን ነው ይሄ? ‹‹በምበላበት ጊዜ በማጅራቴ አካባቢ እንዲህ አይነት ስሜት እንዲሰማኝ አልፈልግም፡፡ ለምንድን ነው እንዲህ እንዲሰማኝ የምታደርገኝ? የማልረዳላት አንድ ነገር ቢኖር ይሄን ብቻ ነው፡፡ ምግቤን ከሰጠችኝ በኋላ በዚህ መንገድ ለምን ታስፈራራኛለች? በሄደች!›› ሲል አሰበ፡፡

‹‹ምን ሆንክ፣ ብራየን?›› ስትል ሞኒካ ጠየቀችው፡፡ ‹‹እባክህ ንገረኝ የኔ ፍቅር፡፡ ምን አለበት ልትነግረኝ ብትችል! በጭንቅላትህ ውስጥ የሚመላለሰውን ሃሳብ መረዳት ብችል ምንኛ በወደድኩ! ማውራት ብንችል ምንኛ ደስ ባለኝ፡፡ ላወራህና ካንተ ልሰማቸው የምፈልጋቸው በርካታ ነገሮች ነበሩኝ!›› ስትል አወራችው፡፡

‹‹የምፈልገውን ነገር ጠንቅቃ ታውቃለች፣ አንዳንድ ጊዜ ግን ቅድም እንዳደረገችው አይነት ነገር ስታደርግ ስለ እኔ ደንታ ያላት አትመስልም፡፡›› አለ ብራየን በውስጡ፡፡ ብራየን ማለዳ በሰውነቱ ላይ በነበረው የመደንዘዝ ስሜት ተበሳጫጭቷል፡፡ ሰውነቱ አንዳች ስሜት እንዲሰማው በመፈለግ የአቲዝም በሽተኞች አንዳንድ ጊዜ እንደሚያደርጉት ራሱን ከግድግዳ ጋር በኋይል ማጋጨት ጀመረ፡፡ ሞኒካ ሮጣ በመምጣት መጋጨት መፈለጉን እስኪተው ድረሰስ እቅፍ አድርጋ ያዘችው፡፡ ‹‹ለምንድን ነው እንዲህ የምታደርገኝ? ደስ የሚያሰኝ ነገር ነበር እኮ፣ ለምንድ ነው እንድተው የምትከለክለኝ? በጣም ነው የሚያስጠላው፡፡›› ሲል በውስጡ ለራሱ ተናገረ፡፡

ሞኒካ ከብራየን አጠገብ በርከክ ብላ አይን አይኑን ለማየት ጥረት ብታደርግም እርሱ ግን በምላሹ ሊመለከታት ፈፅሞ አልፈለገም፡፡ ከእርሷ አይን በተቃራኒው ዘወር በማለት አሻግሮ ማየት ጀመረ፡፡ ሞኒካ በለሆሳስ ‹‹ባንተ ተስፋ አልቆርጥም፡፡›› አለችው፡፡ ‹‹ባታወራኝም፣ እቅፍ ባታደርገኝም፣ ችላ ብትለኝም፣ ሁል ጊዜ ከጎንህ ነኝ››፣ አለችው አይን አይኑን በፍቅር እየተመለከተችው።

አሁን ብራየን በማጅራቱ መነካት የተሰማውን ስሜት ዘንግቷል፡፡ “ለምን እነዚያን ድምፆች ከአንደበቷ እንደምታወጣ ይገርመኛል፡ በጣም እንደምወዳት ግን እርግጠኛ ነኝ! ይህን እንድታውቅልኝ የማደርግበት መንገድ ቢኖር ምንኛ በወደድኩ! እህ —፣ ይሁና፡፡ ያን ማድረግ ብችልም ለእርሷ ምንም ማለት ላይሆን ይችላል”፣ አለ በውስጡ።

ለአንዳንድ ክርስቲያኖች ከእግዘኢብሔር ጋር ማውራት ልክ ብራየን ከእናቱ ጋር የነበረውን አይነት ነው፡፡ እግዚብሔር እንደሞኒካ ሳይሆን የውስጣችንን ሃሳብ ሁሉ ያውቃል፡፡ ያም ሆኖ ግን ሃሳቻችንን እንድንገልጽለትና ለእኛ ያለውን ሃሳብ ደግሞ እንድናደምጥለት በብርቱ ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን በርካታ ክርስቲያኖች በገዛ ፈቃዳቸው በመጣ የመንፈሳዊ ኦቲዝም በሽታ ተጠቅተዋል፡፡ ከኦቲዝም በሽታ የሚያገግሙ ሕፃናት ጥቂቶች ናቸው፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ክርስቲያን ከዚህ መንፈሳዊ ኦቲዝም ፈፅሞ ሊገላገል ወይም ሊያገግም ይችላል፡፡ ጉዳዩ፣ የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡

ጸሎት፡- ‹‹አባት ሆይ ስለ አንተ ማወቁ ብቻ አያረካኝም፣ አንተን ራስህን ማወቅ እፈልጋለሁ! በመስጠትና መቀበል እውነተኛ ልምምድ ውስጥ ልገናኝህ እፈልጋለሁ፡፡ ካንተ ጋር ማውራት፣ አንተን ማምለክ፣ አስተምረኝ፡፡ የቤተኝነት ስሜት እንድለማመድ እና በእውነተኛ የአባት-ልጅ ግንኙነት እንዳድግ እርዳኝ፡፡ አሜን፡፡››

ስለ ጸሎት ማወቅ የሚገባህ አስር እውነታዎች

በመሠረቱ ጸሎት ከእግዚአበሔር ጋር ማውራት ማለት ነው፡፡ ከዚህ ያለፈ እንዲሆን ማድረግም ሆነ መደረግ ያለበት ቢሆንም ይህ አባባለ፤ በበቂ ሁኔታ ጸሎትን ይገልጸዋል፡፡ እግዚአብሔር ከተራ ወዳጅ በእጅጉ የላቀና አእምሮአችን ሊረዳው ከሚችለው በላይ ወዳጃችን ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ከሰው ጋር እንደምናደርገው ሁሉ ከእርሱ ጋር እንድናወራ ይጠይቀናል፡፡

ከእግዚአብሔር ጋር ማውራት ልክ ከሌሎች ሰዎች ጋር እንደምናወራው አይነት አይደለም፡፡ ይህ ግንኙነት-ጥበብ፣ ክህሎት የተጠና ባህሪን እና ስነ ስርአትን የሚጠይቅ ግንኙነት ነው፡፡ በሕይወታቸው ዘመናቸው በሞላ በአይሁድ ስርዕት በማደጋቸው ብዙም ለጸሎት እንግዳ ያልነበሩት እነዚያ 12ቱ የኢሱስ ደቀመዛሙርት ኢየሱስን በሉቃስ 11፡1 ላይ፣ ‹‹—እንጸልይ ዘንድ አስተምረን—›› ካሉት፣ እኔ እና አንተማ እንዴት ስለ ርዕሰ ጉዳዩ እውቀት አያስፈልገን ይሆን!

‹‹እግዚአብሔር ከሰጠን መብቶች ሁሉ ታላቁ በማንኛውም ሰአት ወደ እርሱ እንድትቀርብ ማድረጉ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንድታወራ ብቻ አይደለም መብት የተሰጠህ፣ ተጋብዘሀል፡፡ ፈቃድ ብቻ አይደለም የተሰጠህ፣ እንድታደርገው ይጠብቅሃል፡፡ እግዚአብሔር እስክታወራው በጉጉት ይጠብቅሃል፡፡›› ዌስሊ ኤል. ዱዌል

  1. በማንኛውም ቦታ እና ሰአት በምትፈልገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ መጸለይ ትችላለህ፡፡

ከዚህ በታች ያሉትን ነገሮች አስበህ ታውቃለህ?

  •  እግዚአብሔር በውጥረት ውስጥ ስላለ ለፍላጎቶቼ ትኩረት አይሰጥም፡፡
  •  የእኔ ፍላጎቶች በእግዚአብሔር አይን እዚህ ግባ የማይባሉና ችላ የሚባሉ ናቸው፡፡
  •  ፍላጎቶቼን ለማስታወቅ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ የጽድቅ ድፍረት የለኝም፡፡
  •  በቂ እምነት ስለሌለኝ እግዚአብሔር ጥያቄዎቼን አይቀበላቸውም፡፡
  •  ሌላ አሉታዊ አሳቦች ካሉህ በማስታወሻህ ላይ አስፍራቸው።

እግዚአብሔር መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው፣ በሁሉ ስፍራ የሚገኝ እና ሁሉን ማድረግ የሚችል መሆኑን ማወቅህ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጸሎቶችን እየሰማ ምላሽ በሚሰጥበት ሁኔታ ውስጥ ያንተንም ጸሎት ሰምቶ ለመመለስ ስላለው ችሎታ ምን ያስገነዝብሃል?

ከዚህ በታች በቀረቡት ጥቅሶች ውስጥ ስለምን እንደተጸለየ በመለየት እግዚአብሔር እኛንም በምን ጉዳዮች ላይ እንድንጸልይ እንደሚያበረታታን አመልክት፡፡

  • 1ዜና 4፡10
  • መዝሙር 18፡1
  • መዝሙር 22፡1-2
  • መዝሙር 143፡9
  • ማቴዎስ 6፡11
  • ፊሊጵሲዮስ 4፡6-7
  1. አራት አይነት መሠረታዊ የጸሎት አይነቶች አሉ፡፡

ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ቃላትን ከ‹‹መድገም›› የዘለለ ሊሆን ይገባል፡፡ ልመናችንን ማድመጥ ቢወድም፣ ከዚህም ያለፈ ነገር ከእኛ ይጠብቃል፡፡ የጸሎት ሕይወት ከዚህ በታች ያሉትን አራት መሠረታዊ የጸሎት አይነቶ ማካተቱን ልብ በል፡፡

ውዳሴ – በአምልኮ እና አድናቆት ፍቅርህን ለእግዚአብሔር መግለጥ።

  • ባልና ሚስት ለምን ‹‹አፈቅርሀለው/አፈቅርሻለው›› መባባል ያለባቸው ይመስልሃል?
  • ‹‹ተናገሪው›› ከእዚህ ምን ይጠቀማል?
  • የሚነገረውስ ሰው ከእዚህ ምን ይጠቀማል?

አፈቅርሃለው ብለህ ስትነግረው በታላቁ አምላክ ላይ ተመሳሳይ ነገር እየፈጸምክ መሆንህን ትረዳለህ? ልጆቹ ለእርሱ ያላቸውን ፍቅር ሲገልጹ መስማት እግዚአብሔርን እጅግ ደስ ያሰኘዋል፤ ይባርከዋልም! ካደረገልን በረካታ ነገሮች በኋላ ይህንን በረከት ከእርሱ ማስቀረት ጭካኔ አይሆንም? ሁል ጊዜ እንደምታፈቅረው ንገረው፡፡ ይህን ስታደርግ ግን ስለጠየቀህ ወይም ልታስታውሰው ስለሚገባህ ሳይሆን የሚገባው እንደሆነ በመረዳት ይሁን! ውለታ ካለበትና ከሚያፈቅር ልብ የሚወጣ ጤናማ ምላሽ ይህ ነውና!

ኑዛዜ – ኃጢአት ባደረከው ነገር ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት።

  • መዝሙር 66፡18 አንብብ፡፡ ያልተናዘዝከው ኃጢአት በጸሎትህ ላይ የሚያደርሰው ነገር ምንድን ነው?
  • 1ዮሐንስ 1፡9 አንብብ፡፡ የኑዛዜ ጸሎት ኃጢአትህን ምን ያደርጋል?

‹‹ኑዛዜ›› ለሚለው ቃል የግሪክ አቻ ቃሉ ‹‹homologeo›› ሲሆን የቃል በቃል ትርጓሜው ‹‹ያንኑ መናገር›› ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት እግዚአብሔር በሕይወታችን ላይ ኃጢአትን ሲመለከት ስለ ኃጢአቱ ሃጢአትነት ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት ማለት ነው፡፡ ራሳችንን ከኃጢአት ለማጥራት የምንሰራው ከባድ ነገር የለም፤ የሰራነው ስራ ትክክል ስላለመሆኑ ከእርሱ ጋር እንድንስማማ ይነግረንና ይህን ስናደርግ ራሱ ያነፃዋል፡፡ በአንድ ጊዜ ከኃጢአት የጸዳ ሕይወት እንድንመራ በእያንዳንዱ የሕይወታችን ሽንቁር ውስጥ የተሸሸጉትን “ጥቃቅን” ኃጢአቶቻችንን ጭምር በራሳችን እየመረመርን እንድናገኝና በነሱም ላይ ንስሃ እንድንገባ እግዚአብሔር አይጠብቅብንም። እርሱ ራሱ በመንፈሱ ላለንበት መነፈሳዊ አቅም የሚመጥንና ምላሽ እንድንሰጥባቸው የሚፈልገውን የተወሰኑ ጊዚያዊ ጉዳዮችን በመምረጥ ያመለክተናል፡፡ ይህን የመንፈስ ቅዱስ ወቀሳ ታዘን ትክክለኛ ምልሽ እንድንሰጥም ይጠብቅብናል።

ምስጋና – ስለሰራው ነገር እግዚአብሔርን ማመስገን

ሮሜ 1፡18-32 እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ለምን ለሃሳባቸው ከንቱነት አሳልፎ እንደሰጣቸው ይናገራል፡፡

  • ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚቻለው በእነርሱ ዘንድ ግልጥ ሆኖ ሳለ በሃሳባቸው ከንቱ ሆኑ፣ የሚያስተውለውም ልባቸው ጨለመ፡፡ ይህ የሆነው እግዚአብሔርን ስላላመሰገኑትና ምን ስላላሉት ነው?
  • ከእግዚአብሔር ጋር በሚኖረን ግንኙነት መካከል ምስጋናን ስናስቀር፣ ከአሮጌው ወይስ ከአዲሱ ተፈጥሯችን ጉድጓድ ነው መቅዳት የጀመርነው?

ማስታወሻ፡- የ ‹‹አሮጌው ጉድጓድ/አዲሱ ጉድጓድ  ማብራሪያ በምዕራፍ 4 ላይ ቀርቧል። አሮጌው ተፈጥሮህን እንቢ በማለት ለእግዚአብሔር ያልተቋረጠ ምስጋና አምጣ!

ልመና – እግዚአብሔርን መጠየቅ

እግዚአብሔር ልመናህን ወደ እርሱ ማምጣት እንደምትችል ብቻ ሳይሆን እንድታመጣ እንደሚፈልግም ጭምር እንድታውቅ ይፈልጋል! ልጅ በመሆንህ ለአንተ የሰጠው መብት ነው!

  1. እግዚአብሔር በእርግጥ ጸሎትህን ያደምጣል፡፡

ጸሎት ስነልቦናዊ ልምምድ ወይም ስነስርአት አይደለም፡፡ ለራሳችን ጥቅም ለማግኘት ስንል የምንመስጥበት የተመሰጦ አይነትም አይደለም፡፡ ጸሎት እውነተኛ ውይይት ነው፡፡ አንተ ታወራለህ፣ እግዚአብሔር ደግሞ ያደምጥሃል፡፡ ከዛም እርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ በኩል፣ ወይም በሁኔታዎች ወይም በቀጥታ በልብህ ይናገርሃል፡፡

መዝሙር 94፡9 አንብብ፡፡ ይህ ጥቅስ ምን ጭብጭ ይዟል?

  1. በጸሎት ውስጥ እምነት ወሳኝ ነገር ነው፡፡

በርካታ ክርስቲያኖች ወደ እግዚአብሔር እምነት በሌለው ዝንባሌ ይቀርባሉ፡፡ እግዚአብሔር ጸሎታቸውን ለመመለስ ያለውን ፈቃድና ችሎታ ይጠራጠራሉ፡፡ እና እግዚአብሔር ለጸሎታቸው ምላሽን ባይሰጥ የሚያስገርም ነው? ‹‹በአንተ ውስጥ እንድሰራ እኔ ላደርገው እንደምችል እመን፣›› ሲል እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ዳር እስከ ዳር ይጠይቅሃል፡፡ ለጸሎትህ አስደናቂ ምላሽ ይሰጥ ዘንድ እምነት፣ እግዚአብሔር በአንተ ውስ ሊያሳድገው ከሚፈልጋቸው ነገሮች መካከል ዋነናው ነው!

ማቴዎስ 13፡54-58 አንብብ፡፡ ለምንድን ነው ኢየሱስ በገዛ አጋሩ ሊያደርግ ከነበረው አስደናቂ ተአምራት የተስተጓጎለው?

  1. እግዚአብሔር በአራት መንገዶች ጸሎትን ይመልሳል፡፡

እግዚአብሔርን በጸሎት አንድን ነገር መጠየቃችን በራሱ አፋጣኝ ምላሽ ለመቀበል ዋስትና አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ጠቢብ ነው፡፡ ከምንጠይቃቸው ነገሮች ከፊሎቹ ለእኛ መልካም ነገሮች እንደሆኑ፣ ከፊሎቹ ደግሞ እንደሚጎዱን፣ ከፊሎቹ ደግሞ ዘግይተው ወደ ሕይወታችን ቢመጡ የተሸለ እንደሆነ፣ ከፊሎቹ ደግሞ የተወሰኑ ቅድመ ሁኑታዎች ከተሟሉ በኋላ ወደ ሕይወታችን ቢመጡ የተሻሉ መሆናቸውን ያውቃል፡፡ ለዚህም ነው ወደ እርሱ የምንጸልያቸውን ጸሎቶች “እሺ”፣ “አይሆንም”፣ “ጠብቅ”፣ “አስቅድሞ ይህ ይሁንና” ብሎ የሚመልሰው፡፡ እንደ ልጆቹ፣ እግዚአብሔር በጸሎታችን ላይ ባደረገው ውሳኔ ስምምነታችንን ያለማንጎራጎር ልንገልጽ ይገባል፡፡ በታላቅ ጥበቡ እንታመናለንና፡፡

ድክ ድክ የምትል ልጄ በቆንጆ አንጸባራቂ ቢላ ለመጫወት ብትጠይቀኝ እና ብፈቅድላት በጣም ክፉ አባት ነኝ፡፡ በዚህ ወቅት ስለነገሩ ጎጂነት የፈለኩትን ያህል ላብራራላት ብሞክርም ላትረዳኝ ትችላለች፡፡ በማልቀስና በመለማመጥ ሃሳቤን እንድቀይር ልትሞግተኝ ትሞክር ይሆናል፡፡ ነገር ግን ስለምወዳት በአቋሜ ጸንቼ እቆያለሁ፡፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በኃላ፣ ማለትም ቢላን በአግባቡ ለመጠቀም በምትደርስበት እድሜ ግን ቢላውን ልሰጣት እችላለሁ፡፡

የ እሺ፣ አይሆንም፣ ጠብቅ፣ ይህ ይሁንና ምሳሌዎች

ከዚህ በታች ያሉትን ጥቅሶች ካነበብክ በኋላ እሺ፣ አይሆንም፣ ጠብቅ፣ ይህ ይሁንና ከሚሉት አማራጪች ተስማሚውን በመምረጥ ከጥቅሶቹ ፊት ጻፍ፡፡ (ለእያንዳንዱ አማራጭ ሁለት ሁለት ጥቅሶች ቀርበዋል፡፡)

  • 1ሳሙኤል 1፡11፣19-20 __________________
  • ማቴዎስ 26፡36-45 __________________
  • ዘፍጥረት 15፡2-6፤21፡1-7 __________________
  • [በቤተ መቅደሱ ምረቃ ወቅት የሰሎሞን ጸሎት፡፡] 2ዜና 6፡36-39 እና 7፡14 __________________
  • 2 ነገሥት 6፡15-20 __________________
  • 2 ቆሮንቶስ 12፡7-10 __________________
  • ዘጸአት 2፡23-25 እና መዝሙር 105፡26-38 __________________
  • ዘኁልቁ 21፡4-9 __________________

ምናባዊ ሃሳብ፡- አንድ ሰው ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡- ‹‹ጌታ ሆይ ግራ በመጋባት ውስጥ ነን! አዲስ ለተወለደው ልጃችን፣ ለቤት ኪራይ እና ለመኪና እዳ ክፍያ የሚሆን ተጨማሪ ገቢ ያስፈልገናል፡፡ በመስራ ቤቴ ያለውን አዲስ የሰራ ማስታወቂያ ከተጨማሪ የደመወዝ ክፍያ ጋር እንዳገኘው እርዳኝ?›› እግዚአብሔር ለዚህ ጥያቄ ‹‹አይሆንም›› ወይም ‹‹ጠብቅ›› ሊል የሚችልበትን ሃሳባዊ ምክንያቶች ፃፍ፡፡

አይሆንም፡፡ —————-

ጠብቅ፡፡ ——————–

  1. ‹‹እሺ›› የሚሉ ምላሾች ቅድመ ሁኔታዎች አሏቸው፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ሳይንስ መሠረት ከአንድ ጥቅስ ተነስተህ ዶክትሪን መስራት አትችልም፡፡ ርዕስ ጉዳዩን አስመልክቶ መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን ጠቅላላ ሃሳብ ማጤን ይኖርብሃል፡፡ አለበለዚህ የዝሆንን የተወሰነ የሰውነት ክፍል ከዳሰሱ በኃላ ስለዝሆን መግለጫ ለመስጠት እንደሞከሩ ሦስት ማየት የተሳናቸው ሰዎችን መምሰልህ ነው፡፡ አንዱ የዝሆኑን ሰፋ ያለ የሰውነት ክፍል ከነካ በኃላ እንደ መኖሪያ ቤት ትልቅና ጠፍጣፋ ይመስላል አለ፡፡ አንዱ ደግሞ ኩንቢውን ከነካ በኃላ እባብ ይመስላል አለ፡፡ ሌላው ደግሞ እግሮቹን ከነካ በኃላ ዛፍ ይመስላል አለ፡፡ ምሳሌው ለጸሎታችን ‹‹እሺ›› የሚል ምላሽን ለማግኘት ከምናደርገው ምርመራ ጋር የሚመሳሰልበት ነገር አለው፡፡ ይህም፣ ከእሺታ ምላሾች ጋር አብረው የሚመጡትን ቅድመ ሁኔታዎች ከአጠቃላዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ሃሳብ አንጻር  መፈተሽ ይኖርብናልን እና ነው። እዚህ ማጠቃለያ ላይ ለመድረስ ይረዳን ዘንድ እስቲ ከዚህ በታች ያሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚያስተላልፉትን ቅድመ ሁኔታዎች እናጢን።

ከዚህ በታች አስር የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ቀርበዋል፡፡ እያንዳንዱ ለጸሎቶቻችን አወንታዊ ምላሽ ለማግኘት መሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ያሳያሉ፡፡ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች በክፍት ቦታው ላይ ፃፍ፡፡

  • ቴዎስ 17፡20 ________________
  • ማርቆስ 11፡24 ________________
  • ማርቆስ 11፡25 ________________
  • ሉቃስ 18፡1-8 አንብብ ________________
  • ሉቃስ 18፡9-14 አንብብ ________________
  • ዮሐንስ 14፡13 [በዚህ ጥቅስ ውስጥ 2 ቅድመ ሁኔታዎች አሉ] ________________
  • ዮሐንስ 15፡7 ________________
  • ያዕቆብ 4፡2 ________________
  • ያዕቆብ 4፡3 ________________
  • 1ዮሐንስ 5፡14-15 ________________
  1. በ ‹‹ኢየሱስ ስም›› በሚድረግ ጸሎት ውስጥ ታላቅ ስልጣን አለ

በማሕበር በሚደረጉ ጸሎቶች ላይ በጸሎቱ ማብቂያ ላይ ‹‹በኢየሱስ ስም፣ አሜን›› ሲባል ሰምተህ ይሆናል፡፡ ይህን ማድረግ ተገቢ ቢሆንም በኢየሱስ ስም መጸለይ የጸሎታችን መደምደሚያ በማድረግ የእግዚአብሔርን የማረጋገጫ ማህተም ከመጠባበቅ የላቀ ነው፡፡

‹‹በኢየሱስ ስም›› መጸለይ ምን ማለት ነው? ይህ ማለት የኢየሱስ ክርስቶስን ሕጋዊ ውክልና ይዘህ በክርስቶስ ፍጽምና በአብ ፊት በመታየት ጸሎትህን ማቅረብ ማለት ነው፡፡ ይህ ሁኔታ፣ በር ካንኳኳ በኃላ የሕግ ማዘዣ በማሳየት ‹‹በሩን ይክፈቱልኝ!›› የሚልን ፖሊስ ይመስላል፡፡ ይህ ሰው በሩን ክፈቱልኝ ስላለ ብቻ ይከፈትልኛል ብ አይጠብቅም፤ በሩ እንደሚከፈትለት የሚጠብቀው በሕግ ስም ሕጉን ወክሎ መምጣቱ ብቻ ነው፡፡

‹‹ሰይጣን በጥረታችን ላይ ሊሳለቅ ይችል ይሆናል፣ በጥበባችን ላይም ሊዘባበት ይችላል፣ ነገር ግን፣ ደካማ አማኝ እንኳን ሳይቀር በጉልበቱ ሲንበረከክ ሲያይ ይርበደበዳል፡፡›› – ያልታወቀ ምንጭ

ከኢየሱስ ትንሳኤ በኋላ ኢየሱስ ለተከታዮቹ ጸሎታቸውን በቀጥታ ወደ አብ ማድረስ እንደሚችሉ ነግሯቸዋል፡፡ ምክንያቱም አሁን በራሳቸው ሳይሆን በእርሱ ስም ወደ አብ ይቀርባሉና፡፡ ኢየሱስ ስልጣኑንና ፍፅምናውን ለእኛ ሰጥቷል በመሆኑም ለልመና በአብ ፊት ስንሆን ፈጣሪያችን እኛን ሳይሆን በእርሱ ደስ የሚሰኝበትንና ጸሎቱን ሊሰማ የሚወደውን ኢየሱስን ይመለከታል!

በስካር ሆኜ ከነጉድፌ በመሆን እና ልቤ በሃሰት ተሞልቶ በፊቱ ብቀርብና ‹‹እርሱን በመወከል በልጁህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በፊትህ መጥቻለሁ፣›› ብል አብ እንዴት የሚመልስልኝ ይመስልሃል?

አብ ልባችንን ያውቃል፡፡ እኛም ሆንን እርሱ ከእኛ ኃጢአት የለሽ ፍፁም ሕይወት የማይጠበቅ ቢሆንም፣ ለመንፈስ ቅዱስ የእርምት ጥረት ተገቢ ምላሽ መስጠት አለመስጠታችንን ያውቃል፡፡ ‹‹በኢየሱስ ስም›› የሚጸልይ ሰው አንዳንድ ባህሪያት ምን ሊመስል ይገባል ትላለህ?

  1. ለ እሺ መልስ፣ በፅናት መቆም

በእግዚአብሔር ፊት ልመናን አንዴ ካስታወቁ በኋላ በድጋሜ ጉዳዩን ሳያስቡ ወይም ሳያሳስቡ ምላሹ እስኪመጣ በትዕግስት መጠባበቅ የምክንያታዊነት፣ የትህትና እና የታላቅ እምነት መገለጫ እንደሆነ ይታሰብ ይሆናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የእግዚአብሔር ልጅ ያለውን መመልከት ጠቃሚ ነው፡፡

ሉቃስ 11፡5-13 አውጥተህ አንብብ፡፡ በቁጥር 9 እና 10 ላይ ያለው መልዕክት የግሪኩ ሃሳብ የተሻለ ትርጓሜ፣ ‹‹ሳታቋርጡ ለምኑ — ሳታቋርጡ ፈልጉ — ሳታቋርጡ አንኳኩ —›› የሚለው ነው፡፡ ኪዚህ ጥቅስ በጸሎታችን በፅናት ስለመሆን ምን ትማራለህ?

ሳታቋርጥ እንድንለምን፣ ሳናቋርጥ እንድንፈልግ፣ ሳናቋርጥ እንድናንኳኳ የሚፈልገው ለምን ይመስልሃል?

  1. ችላ ያልናቸው ኃጢአቶች የ‹‹እሺ›› መልሶቻችን እንቅፋቶች ናቸው፡፡

ለምንድን ነው እግዚአብሔር ኃጢአትህን ችላ የማይለው?

ዴኒስ የጓደኛውን የቤት እቃ ለማጓጓዝ መኪናውን እንዲያውሰው ለመጠየቅ ወደ ማይክ ሄደ፡፡ ስለ ጉዳዩ በሚያወሩበት ጊዜ ማይክ የዴኒስ እጅጌ ላይ ደም ተመለከተ፡፡

‹‹ዴኒስ እየደማህ መሆኑ ተመልክተሀል?››

‹‹አዎ፣ ምንም ችግር የለውም፡፡ ይቆማል፡፡ አሁን ስለመኪናህ እናውራ፡፡ ልዋስው እችላለሁ? ነዳጁን ሞልቼ እመልስልሃለው፡፡››

ደሙ እየበዛ ሄደ ወለሉ ላይ መንጠባጠብ ጀመረ፡፡

‹‹ፈጥነን ወደ ሆስፒታል መሄድ ይኖርብናል፣ ዴኒስ፡፡ አርተሪህ ሳይቆረጥ አይቀርም!››

ዴኒስ በመታወክ፣ ‹‹ማይክ፣ ስለደሜ ጉዳይ ልታልፈው ትችላለህ? አሁን የማወራው ስለ መኪናህ ነው! የማወራው ነገር ግድ አይልህም? ርዕሱን እቀያየርክ ትቀጥላለህ ወይስ የመኪናውን ቁልፍ ሄደህ ታመጣልኛለህ?››

ማይክም እንደዛው በመታወክ፣ ‹‹ወደ ሆስፒታል ሄደን ይህን ቁስልህን እስካላሰፋነው ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ ስለመኪናው አዲት ቃል አልተነፍስም – አለበለዚያ መኪናዬን ለመጠቀም በሕይወት የምትቆይ አይመስለኝም!››

ዴኒስ ጓደኛው ቤት ለመቀየር የሚያደርገውን ስራ ለማገዝ ያደረገው ተነሳሽነት አስደናቂ ነው፡፡ ማይክ ግን ከዚህ ይልቅ አስቸኳይ ነገር በዴንስ ሕይወት ላይ ተመልክቷል፡፡ እኛም ወደ እግዚአብሔር በርካታ አስደናቂ ጥያቄዎችን ይዘን ልንመጣ እንችላለን ነገር ግን ኃጢአት ሕይወታችንን በስለት ሲቆራርጥ እየተመለከተ እነዚሕን ጥያቄዎች ከቁብ ሊቆጥራቸው አይችልም፡፡

  1. ማድመጥ መዘንጋት የለብህም፡፡

እስካከሁን ስለ ጸሎት በጣም ጠቃሚ ነጥቦን ተገንዝበሃል፡፡ ሮዝላንድ ሪንኮር እንዳለው፣ ‹‹ጸሎት በሁለት ወዳጆች መካከል የሚደረግ ውይይት፣›› ከሆነ እግዚአብሔር ሊናገርህ የሚፈልገውን ነገር ለማድመጥ የተወሰነ ጊዜ ልትሰጥ ይገባሃል፡፡

ይህን ለማድረግ መጽሐፍ ቅዱስህን ከፍተህ በዝምታ ልትጠብቅ ትችላለህ፣ አልያም የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ እያሰላሰልክ ከእግዚአብሔር አንዳች ነገር በመጠባበቅ መቆየት ትችላለህ፡፡ ሊናገር የሚፈልገው ነገር ካለ እንዲናገርህ ጠይቀው፡፡ ከዛም ጠብቅና ስማ፡፡

በ 1ሳሙኤል 3፡10 ላይ ሳሙኤል እንዲህ አለ፣ ‹‹ባሪያህ ይሰማልና ተናገር፡፡›› ነገር ግን ብዙውን ጊዜ ጸሎቶቻችን ከዚህ በተቃራኒው፣ ‹‹ባሪያህ ይናገራልና አድምጥ!›› የሚሉ ናቸው፡፡ ኢሳይያስ 55፡2 እና 3 አንብብና እግዚአብሔር ምን እንድናደርግ እንደሚፈልግ ጻፍ፡፡

‹‹ጸሎት በመጀመሪያ ደረጃ እግዚአብሔርን ማድመጥ ነው፡፡ እግዚብሔር ሁልጊዜ ይገራል፤ ሁል ጊዜ አንድ ነገር ያደርጋል፡፡ ጸሎት ወደዚህ ተግባር መግባት ማለት ነው፡፡›› – ሄነሪ ኖወን

‹‹መንፈሳዊ ጦርነቶች በድል የሚጠናቀቁት ከመንፈስ ቅዱስ የሚሰጡትን መገለጦች በመከተል ነው፡፡ ልጅ በአባቱ ላይ እንዳለው አይነት ጥገኝነት በእግዚአብሔር ላይ ጥገኛ ሆነን ብንሰማው፣ በድል ጎዳና ይመራናል፡፡›› – ጆን ዳውሰን

ለማን ልጸልይ?

ከዚህ በታች በጸሎት ጊዜህ ሊረዳህ የሚችል ምቹ የምስል ማብራሪያ ቀርቦልሃል፡፡ ለማን መጸለይ እንዳለብህ ለማስታወስ እጅህን ማየት ብቻ ነው፡፡

  • አውራ ጣትህ ላንተ ቅርብህ ነው፣ ስለዚህ ጸሎትህን ላንተ ያቅርብ ከሆኑ ሰዎች ጀምር፡- ለባለቤትህ፣ ለልጆችህ፣ ለወላጆችህ፣ ለወንድሞችህና እህቶችህ፣ ለሌሎች ዘመዶችህ፣ ጓደኞችህ እና ጎረቤቶችህ፡፡
  • አመልካች ጣትህ የሚያስተምሩ ሰዎችን ማለትም መጋቢዎችን፣ ሚሽነሪዎችን እና መምህሮችን ያስታውስሃል፡፡ ሌሎችን በትክክለኛ አቅጣጫ እንዲመሩ ድጋፍና ጥበብ ያሻቸዋል፡፡
  • የመሃል ጣትህ ትልቁ ጣትህ ነው በመሆኑም ለመሪዎች እንድትጸልይ ያስታውስሃል፡- ለፕሬዝደንቶች፣ በንግዱ አለም ላሉ ዎኖች፣ ለትምህርት ቤት አስተዳዳሪዎች፣ ለአለቃህ፣ ወዘተ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከተሞቻችንን፣ ክልሎቻችንን እና አገራችንን የሚቀርጹ ስለሆኑ የእግዚአብሔር ምሪት ያሻቸዋል፡፡
  • የቀለበት ጣትህ ደካማው ጣትህ ነው ይህም ለደካሞች በችግር ውስጥ ላሉትና በህመም ላሉ እንድትጸልይ ያስታውስሃል፡፡ እነዚህ ሰዎች ቀንና ለሊት ጸሎትህን ይሻሉ፡፡
  • ትንሿ ጣትህ ከጣቶችህ ሁሉ ትንሿ ናት። ይህም ከእግዚአብሔርና ከሌሎች አንጻር ራስህን ዝቅ አድርገህ እንድትመለከት ያስታውስሃል፡፡ ስለ ፍላጎቶህ፣ ስለደስታህ፣ ስለ ችግሮችህ፣ ስለ እቅድህና ህልሞችህ ጸልይ፡

የጸሎት ማስታወሻ

ከዚህ ቀጥሎ የጸሎት ሕይወትህን የሚያነቃቃና እምነትህን የሚያሳድግ ሃሳብ ቀርቦልሃል፡፡ ሦስት ቀለሞች ያሉት በርካታ ወረቀት አዘጋጅ፡፡ የቀለሞቹንም ርዕስ ‹‹ቀን›› ፣ ‹‹ልመና›› ፣ እና ‹‹መልስ›› ብለህ ሰይም፡፡ ስለ አንድ ጉዳይ እንድትጸልይ በተሰማህ ጊዜ ሁሉ፣ የልመናውን ርዕሰ ጉዳይ ፅፈህ ቀኑን አኑር፡፡ ከዛም እግዚአብሔር ከአራቱ የመልስ አይነቶች በአንዱ ምላሽ ሲሰጥህ፣ ምላሹን በሦስተኛው ኮለም ላይ ፃፍ፡፡ ከቆይታ በኃላ ይህን የጸሎት ማስታወሻ ስትመለከት እግዚአብሔር ለጸሎትህ በሰጠህ ምላሾች ትደነቃለህ!

ከሕይወትህ ጋር ማዛመድ

በሚከተሉት ሦስት ጉዳዮች (የግል ወይም ለሌሎች ሊሆን ይችላል) ላይ አሁኑኑ መጸለይ እጀምራለሁ፡፡ ተጨባጭ ምላሽ ከእግዚአብሔር እስካገኝ ድረስ ጸሎቴን አላቋርጥም፡፡ ጸንቼ እጸልያለሁ!

  1. _________________________________
  2. _________________________________
  3. _________________________________

የቃል ጥናት ጥቅስ፡-

እስከ አሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም፤ ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ለምኑ ትቀበሉማላችሁ።-ዮሐንስ 16፡24

ማጠቃለያ

‹‹ልታወራኝ፣ ወደ እኔ ልትመጣ ትወዳለህ? ሲል ኢየሱስ ጥያቄ ያቀርብልሃል

ምዕራፍ 9ን ያጥኑ

Leave a Reply

%d bloggers like this: