በትንቢተ ዘካርያስ ውስጥ የሚገኙ ዐበይት ትምህርቶች

1. የመጨረሻዎቹ ዘመን 

ከሥነ መለኮት ትምህርት ዐበይት ክፍሎች አንዱ «ኤስካቶሎጂ በመባል የሚታወቅ ሲሆን፥ ይህም በመጨረሻው ዘመን ስለሚሆኑት ነገሮች የሚመለከት ጥናት ነው። እስካሁን ድረስ የተመለከትናቸውን የነቢያትን መጻሕፍት ስናጠና ሁሉም በአንድ ወይም በሌላ መንገድ በመጨረሻው ዘመን ስለሚሆኑ ነገሮች እንደሚናገሩ አስተውለናል። በሩቁ መጪ ጊዜ ስለሚፈጸሙት ተናጠል ክስተቶች ለመናገር «የጌታ ቀን» ወይም «በዚያ ቀን» የሚሉ ሐረጎችን ይጠቀማሉ። ዳሩ ግን በመጨረሻው ዘመን ስለሚሆነው ነገር በጊዜ ቅደም ተከተል የሰፈረ ዝርዝር መግለጫ ያቀረበ አንድም ነቢይ የለም። የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን በዘመን መጨረሻ በሚሆኑ ነገሮች የአፈጻጸም ቅደም ተከተል ላይ የማይስማሙበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው። ስለዚህ በተለያዩ ስፍራዎች የተሰጡትን መረጃዎች ማጠናቀርና ስለ መጨረሻው ዘመን ወደ አንድ አሳብ መድረስ የራሳችን ኃላፊነት ነው።

በብሉይ ኪዳን ከሚገኙት መጻሕፍት ሁሉ በተሻለ ሁኔታ በመጨረሻው ዘመን ስለሚፈጸሙት ነገሮች ግልጽ መረጃ የሚሰጡን ሁለት የትንቢት መጻሕፍት አሉ። እነርሱም ትንቢተ ዳንኤልና ዘካርያስ ናቸው። ትንቢተ ዳንኤል የሚያተኩረው በመጨረሻ ዘመን በአሕዛብ መንግሥታት ዘንድ ምን እንደሚሆን በመናገር ላይ ነው። ዳንኤል ስለ አይሁድ ቢናገርም እንኳ፥ ታሪካቸውን አስቀድሞ የሚናገረው ከአሕዛብ መንግሥታት ጋር ካላቸው ግንኙነት አንጻር ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ዘካርያስ የሚያተኩረው የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ሕዝብ የሆኑትን የእስራኤልን ሕዝብ በሚመለከት ጉዳይ ላይ ነው። ዘካርያስ በተጨማሪ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት በግልጽ ከተነገሩ መረጃዎች አንዳንዶቹን ይሰጠናል።

ቀጥሎ ዘካርያስ የጠቀሳቸውን የመጨረሻውን ዘመን ክስተቶች ልብ ብለህ ተመልከት፡-

ሀ. እስራኤል በመጨረሻው ዘመን እንደገና ትሰበሰባለች፣ ትታደላለችም (ዘካርያስ 10፡9-12) 

ለ. ኢየሩሳሌም በመጨረሻው ዘመን ትከበባለች (ዘካርያስ 12፡1-3፤ 14፡1-2)፣ 

ሐ. በመጀመሪያ አሕዛብ እስራኤልን ያሸንፋሉ (ዘካርያስ 14፡2)፤

መ. እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን ይታደጋል (ዘካርያስ 14፡3-4)፤ 

ሠ. እግዚአብሔር በአሕዛብ ላይ ይፈርዳል (ዘካርያስ 12፡9)፤ 

ረ. ይሁዳና እስራኤል እንደገና አንድ ሕዝብ ይሆናሉ (ዘካርያስ 10፡9-12) 

ሰ. አይሁድ የገደሉትን መሢሑን በሚያዩበት ጊዜ ይለወጣሉ፤ ከኃጢአትም ይነጻሉ (ዘካርያስ 12፡10-13፡9)፤ 

ሸ. የደብረ ዘይት ተራራ ለሁለት ይሰነጠቃል። ከኢየሩሳሌም የሚፈስስ ወንዝ ይወጣል (ዘካርያስ 14፡4-6) 

ቀ. አዲስ ፍጥረት፥ አዲሲቷ ኢየሩሳሌም፥ እንዲሁም አዲስ ቤተ መቅደስ ይሠራል፥ እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ ይገዛል (ዘካርያስ 14፡6-2) 

በ. አሕዛብ በኢየሩሳሌም ያመልካሉ (ዘካርያስ 14፡16)። 

2. መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ

ትንቢተ ዘካርያስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ አስደናቂ ትንቢቶችን የያዘ መጽሐፍ ነው። ትንቢቶቹ ዛሬ የኢየሱስን ታሪክ ለምናውቅ ለእኛ አስደናቂ ላይሆኑ ይችላሉ። ይሁን እንጂ እነዚህ ትንቢቶች ከመፈጸማቸው ከአራት መቶ ዓመታት በፊት መሰጠታቸውንና ያለ አንዳች ስሕተት በትክክል መፈጸማቸውን ስናስብ እንደነቃለን። ከአራት መቶ ዓመታት በኋላ የሚፈጸመውን ነገር ቀርቶ ከአሥር ዓመት በኋላ የሚሆኑትን ነገሮች እንኳ ማን አስቀድሞ ሊናገር ይችላል? ዳሩ ግን እግዚአብሔር ያለፈውን እንደሚያውቅ ሁሉ የወደፊቱንም ያውቃል። ለእርሱ በመቶ ወይም ከሺህ ከሚጠሩ ዓመታት በፊት እንኳ የሚሆኑትን ነገሮች አስቀድሞ መናገር እጅግ ቀላል ነው። ቀጥሎ የቀረበው ሰንጠረዥ ስለ መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰጡ ትንቢቶች እንዴት እንደተፈጸሙና የወደፊቶቹ ደግሞ እንዴት እንደሚፈጸሙ ያሳየናል።

ትንቢት

ኢየሱስ ትሁት ይሆናል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 6፡12፤ 13:7

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ማቴዎስ 26፡31 56

ትንቢት

ኢየሱስ ሰው ይሆናል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 6፡12፤ 13፡7

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ሉቃስ 2

ትንቢት

ኢየሱስ ተቀባይነት አይኖረውም፤ በሠላሳ ብርም ይሸጣል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 11፡12-13

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ማቴዎስ 26፡15፤ 27፡9-10

ትንቢት

ኢየሱስ በጦር ይወጋል፤ ይገደላል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 12፡10፣ 13፡7

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ማቴዎስ 26፡31፣ ዮሐ. 19:37 

ትንቢት

ኢየሱስ ካህን ይሆናል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 6፡13

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ዕብራውያን 6፡20 

ትንቢት

ኢየሱስ የሰላምና የጽድቅ ንጉሥ በመሆን በኢየሩሳሌም ይነግሣል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 6፡13፤ 9፡9፤ 14፡9፡16

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ማቴዎስ 21፡5፤ ራዕይ 11፡15፤ ራእይ 19፡6 

ትንቢት

ኢየሱስ በክብር በመመለስ ሕዝቡን እስራኤልን ነጻ ያወጣል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 14፡1-6

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ማቴዎስ 25፡31

ትንቢት

ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ይሠራል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 6፡12-13

ትንቢት

ኢየሱስ አዲስ የዓለም ሥርዓት ይመሠርታል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ14፡6-19

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ራእይ 21፡22-27፡ 22:1፣ 5

ትንቢት

ኢየሱስ በቃል ኪዳኑ ደም እስራኤልን ያድሳል

የተነገረበት ክፍል 

ዘካርያስ 9፡11

የትንቢቱ ፍጻሜ 

ማርቆስ 14፡24

ትንቢት

ኢየሱስ ለተበተኑና እንደ በጎች ለሚቅበዘበዙት ሕዝቡ እረኛ ይሆናል

የተነገረበት ክፍል 

 ዘካርያስ 10፡2

የትንቢቱ ፍጻሜ 

 ማቴዎስ 9፡36

** የትንቢት መጻሕፍት የኢየሱስን የመጀመሪያና ዳግመኛ ምጽአት በግልጽ ለይተው እንደማያመለክቱ ልብ በል። አንድ ጊዜ ተቀባይነት ስለማይኖረውና ተሰቅሎ ስለሚገደለው ስለ ትሑቱ ኢየሱስ ይናገራሉ። በሚቀጥለው ቁጥር ደግሞ አይሁዳውያን ስለሚቀበሉት እንዲሁም በጽድቅና በሰላም ስለሚገዛው ንጉሥ ይናገራሉ። በሸለቆ ሥር ቆሞ አሻግሮ የሚመለከት አንድ ሰው እጅግ የተቀራረቡ በሚመስሉ ተራሮች መካከል ያለውን ርቀት በትክክል መናገር እንደማይችል፥ የወደፊቱን ብዙ መቶ ዓመታት አሻግረው የተመለከቱት ነቢያት በኢየሱስ የመጀመሪያና ዳግም ምጽአት መካከል ያለውን ልዩነት ለመመልከት አልቻሉም። ነቢያቱ የሚናገሩት ስለ ሁለት የተለያዩ ጊዜያት መሆኑ የታወቀው ከኢየሱስ የመጀመሪያ አመጣጥ በኋላ ነው።

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) በዘመን መጨረሻ የሚፈጸመውን ነገር ማወቅ ዛሬ በክርስቲያናዊ ጉዞአችን የሚያበረታታን እንዴት ነው? ለ) የዘካርያስ ትንቢቶች የሚያበረታቱን እንዴት ነው?

(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)

የመመዘኛ ጥያቄዎችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ (መስፈንጠሪያ) ይጫኑ፡፡

https://forms.gle/FBWrMQw5En7Kkc7w8

Leave a Reply

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading