መላእክት

ሀ. የመላእክት አፈጣጠር 

መጽሐፍ እንደሚናገረው፥ እግዚአብሔር ሰውን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ለቁጥር የሚያዳግቱ ሠራዊተ መላእክት ፈጥሯል። መላእክት ልክ እንደ ሰው ሕልውና ያላቸው ከመሆናቸውም በላይ፥ ታላቅ እውቀትና የግብረ ገብ ኃላፊነት ችሎታ አላቸው። “መልአክ” ማለት ልዩ በሆነ አገባሱና አገላለጡ መልእክተኛ ማለት ነው። ቃሉ አንዳንዴ ለሌሎች መልእክተኞች ማለት በራእይ 2-3 የተጠቀሱትን የሰባት የእስያ አብያተ ክርስቲያን መልእክተኞች ላመሳሰሉት መጠሪያ ሊሆንም ይችላል (ራእይ 1፣ 20፤ 2፡1፥ 8፥ 12፥ 18፤ 3፡1፥ 7፥ 14)። አንዳንዴም ለሰብአዊ መልእክተኞች መጠሪያነት አገልግሏል (ሉቃስ 7፡24፤ ያዕ. 2፡25)። የሞቱ ሰዎችን መንፈስ ላመጥቀሻም ውሏል (ማቴ. 18፡10፤ ሐዋ. 12፡15)። እዚህ ላይ ከፍተኛ ግንዛቤኝ የሚሻው ዐቢይ ጉዳይ፥ ሰዎች ሲሞቱ ወደ መላእክትነት ይለወጣሉ ወይም ከሰዎች የተለየ መንፈስ ይሆናሉ ማለት አለመሆኑ ነው። “መልእክተኛ” የሚለው ቃል በጣም ሰፊ አሳብ ይዟል። በዚህ ሁኔታ “መላእክትን የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን መልአክ ለማመልከትም፥ ማለት ክርስቶስ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሰመላእክት መልክ ከእግዚአብሔር ወደ ሰው የተላከ መሆኑን ለመግለጫነት አገልግሷል (ዘፍጥ. 16፡1-13፤ 21፡17-19፤ 22፡11-16)። 

ቃሉ ሰውን ወይም እግዚአብሔርን በግልጥ ለማመልከቻነት በማይውልበት ጊዜ፥ ግብረ ገባዊ ኃላፊነት ላሰባቸውና፥ በዚህም አኳያ እግዚአብሔርን ለሚያገለግሉ ማለት ልዩ ሁኔታ ላላቸው ሰዎች መጠሪያነት ያገለግላል። መላእክት እንደ ሰው ሁሉ ለዘላለም የሚኖሩና ከሌሎች ፍጡራን የሚሰዩ ናቸው። እግዚአብሔር በዘመናት ባለው ዕቅድ ውስጥ ጎላ ያለ ስፍራ የሚይዙ ሲሆኑ፥ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከመቶ ጊዜ በላይ፥ አዲስ ኪዳን ውስጥ ደግሞ ይበልጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሰዋል። 

መላእክት እጅግ ከቁጥር በላይ ሆነው በአንድ ጊዜ የተፈጠሩ ናቸው (ዕብ. 2፡22፤ ራእይ 5፡11)። ጥበብ፥ ፈቃድና ስሜት ያለው አንድ ፍጡር የሚኖሩት ባሕርያት ሁሉ አሏቸው። ከዚህም የተነሣ ለእግዚአብሔር አምልኮ የማቅረብ ችሎታ አላቸው (መዝ. 148 ፡2)። ስላ አገልግሎታቸውና ሥነ- ምግባራዊ ምርጫቸውም ኃላፊነት አለባቸው። 

2204 በመንፈሳዊ ሥርዓት የተፈጠሩ እንጂ፥ ሰብአዊ አካል ያላቸው አይደሉም (1ኛ ቆሮ. 15፡44)። አንዳንዴ ግን በአካል ሊገለጡና እንደ ሰው ሊታዩ ይችላሉ (ማቴ. 28፡3፤ ራእይ 15፡6፤ 18፡1)። በመዋለድ አይባዙም፥ አካላዊ ሞትም አይሞቱም። ከሰው ጋር የሚመሳሰሉበት ነገር ቢኖርም፥ ዓበይት በሆኑ ነገሮች የተለዩ ናቸው። 

ለ. ያልወደቁት መላእክት 

በአጠቃላይ መላእክት፥(1) ያልወደቁ መላእክት፥ (2) የወደቁ መላእክት ተብለው በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ይመደባሉ። ያልወደቁት መላእክት በዘመናቸው ሁሉ የተቀደሱ ስለሆኑ ቅዱሳን መላእክት” ተብለው ይጠራሉ (ማቴ. 25፡31)። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአጠቃላይ ስለ መላእክት ሲጠቀስ በዓይነ ሕሊና የሚታዩት ያልወደቁ መላእክት ናቸው። የወደቁ መላእክት የሚባሉት ደግሞ ቅድስናቸውን ያልጠበቁት ናቸው። 

ያልወደቁ መላእክት በሚከተለው አኳኋን በልዩ ክፍል የሚመደቡ ሲሆን፥ ከእነርሱም አንዳንዶቹ በስም ተጠቅሰዋል። 

1. የቅዱሳን መላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሲሆን፥ የስሙም ትርጉም ንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ነው (ዳን. 10፡21፤ 12፡1፤ 1ኛ ተሰ. 4፡16፤ ይሁዳ 9፤ ራእይ 12፡7-10)። 

2. ከዋና ዋናዎቹ የእግዚአብሔር መልእክተኞች አንዱ ቅዱስ ገብርኤል ሲሆን፥ የስም ትርጉም ተግዚአብሔር ጀግና” ቀሚል አው። ለዳንኤል የተላኩ ታላላቅ መልእክትን (ዳን. 8፡16፤ 9፡21)፥ ለዘካርያስ (ሉቃስ 1፡18-19)፤ እና ለቅድስት ድንግል ማርያም (ሉቃስ 1፡26-38) የተላለፉትን ጭምር በታማኝነት አድርሷል። 

3. ተስዙዎቹ መላእክት የየራሳቸው ስም ባይሰጣቸውም፥ የተመረጡ ተብለው ይጠራሉ (1ኛ ጢሞ. 5፡21)። ይህ አሳብ የሚገርም ነጥብ አለው። ይህም መላእክት በመለኮታዊ አጠራር የተመረጡ መባላቸው፥ ዳግም ተወልደው የዳኑ ሰዎችም የተመረጡ ተብለው ከተጠሩበት አጠራር ጋር መመሳሰሉ አስደናቂ ነው። 

4 . “ኃይላትና ሥልጣናት” የሚለው መጠሪያ የወደቁትንም ሆኝ ያልወደቁን መላእክት ለመጥሪያነት የሚያገለግል ይመስላል (ሉቃስ 21፡26፤ ሮሜ 8፡38፤ ኤፌ. 1፡21፤ 3፡10፤ ቈላ. 1፡16፤ 2፡10፥ 15፤ 1ኛ ጴጥ. 3፡22)። ይህም በመሆኑ ሰዎችን ለመቆጣጠር ወይም ለመያዝ በቅዱሳኑና በወደቁት መላእክት መካከል የማያቋርጥ ጦርነት ይካሄዳል። 

5 . አንዳንድ መላእክት ኪሩቤል በመባል የሚታወቁ ሊሆኝ፥እነርሱም የእግዚአብሔርን ቅድስና ከማንኛውም ዓይነት የኃጢአት ርኩሰት የሚከላከሉ ሕያው ፍጡራን ናቸው(ዘፍጥ. 3፡24፤ ዘጸ. 25፡18፥ 20፤ ሕዝ. 1፡1-18)። የወደቁት መላእክት አለቃ ሰይጣንም በመጀመሪያ ቅዱስ ሆኖ ለዚህ ዓላማ ነበር የተፈጠረው (ሕዝ. 28፡14)። በብሉይ ኪዳን፥ መገናኛው ድንኳን እንዲሁም ቤተ መቅደስ ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ የታቦቱን የሥርየት መክደኛ የሚጠብቁት የኪሩቤል ምስሎች ከወርቅ የተሠሩ ነበሩ። 

6. ሱራፌል በመባል የሚጠሩት መላእክት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱት አንዴ ብቻ፥ ኢሳይያስ 6፡2-7 ውስጥ ነው። እነርሱም ስድስት ክንፎች ያሏቸው፥ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ፥ በእግዚአብሔር ወደ ምድር የሚላኩና በተለይ የእርሱን ክብር የሚጠብቁ ናቸው። 

7. “የእግዚአብሔር መልአክ” የሚለው ቃል የክርስቶስን በመልከ መልክ መለጥ ለማመልከት ብሉይ ኪዳን ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። ስሙም የሚገባው ለእግዚአብሔር ብቻ ሲሆን፥ ያገለገለውም ከመለኮት ስምድር መገለጥ ጋር ነው። በመሆኑም በምንም ሁኔታ የሠራዊተ መላእክት መጠሪያ ሊሆን አይገባም (ዘፍጥ. 18፡1-19፡29፤ 22፡11፥ 12፤ 31፡11-13፤ 32፡24-32፤ 48፡15፥ 16፤ ኢያሱ 5፡13-15፤ መሳ. 13፡19-22፤ 2ኛ ነገሥት 19፡35፤ 1ኛ ዜና 21፡12-30፤ መዝ. 34፡7)። የእግዚአብሔር መልአክ በሆነው ክርስቶስና በሌሉች መላእክት መካከል ያለው እጅግ ከፍተኛ ልዩነት፥ ጳውሎስ ወደ ዕብራውያን ባስተላለፈው መልእክት ውስጥ ተገልጧል(ዕብ. 1፡4-14)። 

ሐ. የወደቁ መላእክት 

ያልወደቁ መላእክት እንዳሉ ሁሉ፥ ስፍር ቁጥር የሌላቸውና የመጀመሪያ ክብራቸውን ትተው የወደቁ መላእክት መኖራቸውም ተገልጧል። ሲፈጠር ቅዱስ በነበረውና በኋላ ግን በትዕቢቱ ከከፍታ ቦታ በወደቀው መልአክ፥ በሰይጣን የተመሩት እነዚህ ለቁጥር የሚያዳግቱ መላእክት ከዳተኞች፥ በእግዚአብሔር ላይ ያመፁ፥ እንዲሁም በተፈጥሯቸውም ሆነ በስፍራቸው ኃጢአተኞች ሆኑ። 

የወደቁ መላእክት በሁለት ይመደባሉ። እነርሱም፦ (1) ነጻ የሆኑና (2) በእስራት ያሉ ናቸው። ከወደቁት መላእክት ሰይጣን ብቻ ነው በተለይ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚጠቀሰው። ሰይጣን በወደቀ ጊዜ ብዙ ከእርሱ ያነሱ ታናናሽ መላእክትን አስከትሎ እንደነበር ለመገመት ይቻላል (ዮሐ. 8፡44)። ከእነርሱም አንዳንዶቻቸው እስከ ታላቁ የፍርድ ቀን ድረስ ታስረው ለፍርድ ተጠብቀዋል (1ኛ ቆሮ. 6፡3፤ 2ኛ ጴጥ. 2:4፤ ይሁዳ 6)። ሌሎቹ ደግሞ ለጊዘው ነጻ የሆኑና አጋንንት ወይም መናፍስት እየተባሉ በአዲስ ኪዳን በተደጋጋሚ የሚጠቀሱት ናቸው (ማር. 5፡9 15፤ ሉቃስ 8፡30፤ 1ኛ ጢሞ. 4፡1)። በድርጊቱ ሁሉ ተሳታፊ ሆነው ሰይጣንን ስለሚያገለግሉት፥ የመጨረሻ ዕጣውም ተሳታፊዎች ይሆናሉ (ማቴ. 25፡41፤ ራእይ 20፡10)። 

መ. የቅዱሳን መላእክት አገልግሎት 

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ መላእክት በሰፊው የተጠቀሰው አገልግሎታቸው ነው። ቀዳሚው አገልግሎታቸው እግዚአብሔርን ማምለክ ሲሆን፥ ራእይ 4፡8 ውስጥ የአንዳንዶቹ አገልግሎት፥ “ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም” ተብሏል። ይህ በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ተጠቅሷል (መዝ. 103፡20፤ ኢሳ. 6፡3)። በአጠቃላይ ቅዱሳን መላእክት በተለያዩ ብዙ መንገዶች እግዚአብሔርን የሚያገለግሉ መሆናቸው ቀጥሎ ባሉት ተግባራታቸው በመጠኑ ተገልጧል። 

1. በፍጥረት መጀመሪያ(ኢዮብ. 38፡7)፥ ሕግ በሚሰጥበት ጊዜ(ሐዋ. 7፡53፤ ገላ. 3፡19፤ ዕብ. 2፡2፤ ራእይ 22፡16)፥ ክርስቶስ ሲወለድ (ሉቃስ 2፡13)፥ ሲፈተን (ማቴ. 4፡11)፥ በአትክልቱ ስፍራ(ሉቃስ 22:43)፥ በትንሣኤ (ማቴ. 28፡2)፥ በዕርገት ጊዜ(ሐዋ. 1፡10) የነበሩ ሲሆን፥ በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ጊዜም አብረውት ይገለጣሉ (ማቴ. 24፡31፤ 25፡31፤ 2ኛ ተሰ. 1፡7)። 

2. ቅዱሳን መላእክት የድነት ወራሾች የሆኑትን የሚያገለግሉ መናፍስት ናቸው (ዕብ. 1፡14፤ መዝ. 34፡7፤ 91፡11)። ከመላእክት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ወይም ኅብረት እንዲኖረን ባይነገረንም፥ የሁልጊዜ በጎ አገልግሎታቸውን ልንረዳ ይገባል። 

3. መላእክት በምድር ላይ ያሉ ነገሮችን የሚመለከቱና ምስክሮች ናቸው (መዝ. 103፡20፤ ሉቃስ 12፡8፥ 9፤ 15፡10፤ 1ኛ ቆሮ. 11፡10፤ 1ኛ ጢሞ. 3፡16፤ 1ኛ ጴጥ. 1፡12፤ ራእይ 14፡10)። 

4. አልዓዛር ሲምት ወደ አብርሃም እቅፍ የተወሰደው በመላእክት ነበር(ሉቃስ 16፡22)። 

5. መልእክት በታሪክ አተረዘሩት እገልግሎቶቻቸው በተጨማሪ፥ ጌታችን ወደ ምድር ሲመለስ አብረውት ይመጣሉ፥ በአዲሲቷ ኢየሩሳሌምም ለዘለም ይታያሉ(ዕብ. 12፡22-24፤ ራእይ 19፡14፤ 21፡12)። ቅዱሳን መላእክት በሺህ ዓመቱ መንግሥት መጨረሻ፥ ማለት በአዲሱ ዘላለማዊ መንግሥት መጀመሪያ፥ ፍርድና ሽልማት ሳይጠብቃቸው አይቀርም። የወደቁት መላእክት ደግሞ በዚሁ ጊዜ ከመሪያቸው ጋር በአንድነት ይፈረድባቸውና ወደ እሳት ባሕር ይጣላሉ። 

6. በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተገለጠው የቅዱሳን መላእክት አገልግሎት ትምህርት እጅግ ጠቃሚ ነው። በታሪክ የተገለጠውንና እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ያለውን ሰጎ ፈቃድና ልዑላዊ ምሪትን ለመረዳትም በዋናነት ያገለግላል።

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Leave a Reply

%d bloggers like this: