የሕይወት እንጀራ

የሐዋርያት ሥራ

ጴጥሮስ አንድ ሽባ ለማኝ በፈወሰ ጊዜ የተነገሩ ተከታታይ ታሪኮች (የሐዋ. ሥራ 3፡1-5፡42)

«ይምጡና በዓለም የታወቀውን ሰባኪና የፈውስ አገልጋይ ይስሙ። የታመማችሁ ሁሉ ብትመጡ ትፈወሳላችሁ። የታመሙና ዓይነ ስውር ጎረቤቶቻችሁን ሁሉ አምጧቸው። ክርስቶስ በስብሰባው ላይ እንደሚፈውሳቸው ንገሯቸው።» ከተማዪቱን ለመጎብኘት ለሚመጣው ዝነኛ የፈውስ አገልጋይ የሚደረገው ማስታወቂያ እንዲህ እያለ ይቀጥላል። እንደዚህ ዓይነት አሳቦችን በክርስቶስና በሐዋርያት የአገልግሎት ዘመን ከተፈጸሙት ሁኔታዎች ጋር ስናነጻጽር አያሌ ልዩነቶች እንመለከታለን። በመጀመሪያው ክርስቶስም ሆነ ሐዋርያት ተአምራትን በመሥራት ሰዎችን ወደ […]

ጴጥሮስ አንድ ሽባ ለማኝ በፈወሰ ጊዜ የተነገሩ ተከታታይ ታሪኮች (የሐዋ. ሥራ 3፡1-5፡42) Read More »

የጥንት ክርስቲያኖች ሕይወት ጥቅል ማብራሪያ (የሐዋ. 2፡42-47)

የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ምን መምሰል አለበት? ቤተ ክርስቲያን በመንፈሳዊ ሕይወቷ ብርቱና አዳጊ ለመሆን የምትችለው እንዴት ነው? ቤተ ክርስቲያን በፍጥነት በምታድግበት ጊዜ፥ ክርስቶስ እንደሚፈልጋት ብርቱና ሕያው ሆና ለመኖር ምን ማድረግ ይኖርባታል? ዓለም በቤተ ክርስቲያን ላይ ተጽዕኖ በማድረስ እምነቷን እንዳታዳክምና እንዳታጠፋ ምን እናድርግ? ሉቃስ ለማደግ ከፈለግን እንደ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ እንደ ግለሰብ ክርስቲያኖች ልናደርጋቸው የሚገቡንን ነገሮች

የጥንት ክርስቲያኖች ሕይወት ጥቅል ማብራሪያ (የሐዋ. 2፡42-47) Read More »

በበዓለ ኀምሳ ዕለት ጴጥሮስ ያቀረበው ስብከት (የሐዋ. 2፡14-41)

ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ፥ በተመዘገቡት ልዩ ልዩ ስብከቶች አማካይነት ክርስቲያኖችን ለማስተማር ይፈልጋል። የጴጥሮስ፥ የእስጢፋኖስና የጳውሎስ ስብከቶች የሐዋርያት ሥራን ብዙውን ክፍል ሸፍነዋል። እነዚህ የጥንት ሐዋርያት ስለ ክርስቶስ ምን እንዳስተማሩ፥ እንዴት እንደ መሰከሩና ለተለያዩ ሰዎች እንዴት ወንጌሉን እንዳብራሩ የሚያመለክቱ ምሳሌያዊ (ሞዴል) ስብከቶች ናቸው። እነዚህን ስብከቶች በጥንቃቄ በማነጻጸር የሚከተሉትን አሳቦች ልናገኝ እንችላለች። 1) የምስክርነት ዋናው ነገር ስለ

በበዓለ ኀምሳ ዕለት ጴጥሮስ ያቀረበው ስብከት (የሐዋ. 2፡14-41) Read More »

በበዓለ ኀምሳ ቀን የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (የሐዋ. 2፡1-13)

ቤተ ክርስቲያን መደበኛ ሆና የተመሠረተችው መቼ ነበር? የኢየሱስ ወደ ምድር መምጣት፥ የክርስቶስ ንጉሣዊ አገዛዝ በሰዎች ሕይወት ውስጥ መጀመሩን ቢያበስርም፥ የቤተ ክርስቲያን አዲስ ምዕራፍ በመደበኛነት የተከፈተው ግን፥ መንፈስ ቅዱስ በአማኞች ሁሉ ላይ በወረደበት ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። አይሁዶች የበዓለ ኀምሳን (የሳምንታት ወይም የመኸር በዓልም ይባላል) ከፋሲካ በዓል 50 ቀናት በኋላ ያከብሩ ነበር። የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት 12ቱን ጨምሮ፥

በበዓለ ኀምሳ ቀን የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (የሐዋ. 2፡1-13) Read More »

አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ማትያስን ደቀ መዝሙር አድርገው መረጡት (የሐዋ. 1፡12-26)

ለአይሁዶች 12 ቁጥር ትልቅ ትርጉም አለው። በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ በ12 ነገዶች የተከፈለ ሲሆን፥ ክርስቶስም ወደ ምድር ሲመጣ የአዲሱ የእግዚአብሔር ሕዝብ (ቤተ ክርስቲያን) መሪዎች እንዲሆኑ 12 ሰዎችን መርጧል። ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱ በእግዚአብሔር መንግሥት በ12 ዙፋናት ላይ ተቀምጠው እንደሚገዙ ተናግሯል (ማቴ. 19፡28)። ይሁዳ ክርስቶስን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ የራሱን ሕይወት በማጥፋቱ የደቀ መዛሙርቱ ቁጥር ወደ 11 ዝቅ

አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ማትያስን ደቀ መዝሙር አድርገው መረጡት (የሐዋ. 1፡12-26) Read More »

ክርስቶስ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት ለደቀ መዛሙርቱ የተናገራቸው የመጨረሻ ቃላት (ሐዋ. 1፡1-10)

ከበደና ሲሳይ የአንዲት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ናቸው። ቤተ ክርስቲያናቸው የምትገኘው ሙስሊሞችና የክርስትና ሃይማኖትን በልማድ የሚከተሉ ሰዎች በብዛት በሚገኙባት አነስተኛ ከተማ ውስጥ ነበር። ወንጌል ወደዚያች ከተማ የመጣው ከ40 ዓመታት በፊት ሲሆን፥ የምእመናን ቁጥር ቀስ በቀስ ወደ 400 ደርሷል። አንድ ቀን የቤተ ክርስቲያኒቱ ሽማግሌዎች ዓመታዊ የዕቅድ ስብሰባ አካሄዱ። በዚህ ጊዜ ከበደ ብድግ ብሎ፥ «ምእመኖቻችን በቂ የእግዚአብሔር

ክርስቶስ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት ለደቀ መዛሙርቱ የተናገራቸው የመጨረሻ ቃላት (ሐዋ. 1፡1-10) Read More »

የሐዋርያት ሥራ አወቃቀር እና አስተዋጽኦ

የሐዋርያት ሥራ አወቃቀር እና አስተዋጽኦ ፩. የሐዋርያት ሥራ አወቃቀር ከመልክዐ ምድር አቀማመጥ አንጻር የውይትት ጥያቄ:- የሐዋርያት ሥራ 1፡8 እንብብና፥ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱ ወንጌሉን ወደ አራት የተለያዩ መልክዐ ምድራዊ ስፍራዎች እንዲወስዱ ያዘዛቸውን ዘርዝር። ክርስቶስ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት፥ ስለ እርሱ ሲመሰክሩ ወንጌሉን ወደ ኢየሩሳሌም፥ ይሁዳ፥ ለማርያና ወደ ሌሎች የዓለም ክፍሎች እንዲያደርሱ ገልጾላቸዋል፡፡ ሉቃስ እነዚህን ክፍፍሎች ከመጽሐፉ

የሐዋርያት ሥራ አወቃቀር እና አስተዋጽኦ Read More »

የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ልዩ ገጽታዎች

ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ የጴጥሮስና የጳውሎስ ስብከቶች አንድ አምስተኛውን ወይም ሃያ በመቶውን እጅ ይሸፍናሉ። በእነርሱ አማካይነት ስለ ጥንቷ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮና እምነት ጥሩ ማብራሪያዎችን አቅርቧል። በእነዚህ ስብከቶች አማካይነት አይሁዶችና አሕዛብ ክርስቶስ ለምን የተስፋቸው መልስ እንደሆነ ያውቁ ነበር። እንደ ወንጌላቱ ሁሉ የሐዋርያት ሥራም በጥንቃቄ የተመረጡ ታሪኮችን ይዟል። ይህ ግን ዐቢይ የትርጓሜ/ የአፈታት ጥያቄ እንድናነሳ ያደርጋል። በመጽሐፍ

የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ልዩ ገጽታዎች Read More »

የሐዋርያት ሥራ ዓላማ

የሐዋርያት ሥራ ዋነኛ ዓላማ በሉቃስ የተጀመረውን ታሪክ መቀጠል ነው። ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ 1፡1 ላይ እንደሚለው የመጀመሪያ መጽሐፉ ኢየሱስ “ያደርገውና ያስተምረው ዘንድ ስለ ጀመረው” ነገር እንደሚያወሳ ገልጾአል። ይህ መጽሐፍ የክርስትናን ሥራ አጀማመር ያስረዳል። የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ደግሞ በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና በመንፈስ ቅዱስ የክርስቶስ ሥራና ትምህርት እንዴት እንደ ቀጠለ ያስረዳል። ሉቃስ ትንሿ ቤተ ክርስቲያን በፍጥነት አድጋ

የሐዋርያት ሥራ ዓላማ Read More »

የሐዋርያት ሥራ መግቢያ

«እንደ መጀመሪያው ምእተ ዓመት ቤተ ክርስቲያን ብንሆን ኑሮ ደስ ይለኝ ነበር። በዚያን ጊዜ የነበሩት ተአምራት፥ በምእመናን መካከል የነበረው ፍቅርና ኅብረት የተለየ ነበር። ከሁሉም በላይ፥ እንደ ቀድሞዎቹ ሐዋርያት በልሳን ብናገር ትልቅ ነገር ነበር። አሁን የሚያስፈልገን እንደዚያች የቀድሞዋ ቤተ ክርስቲያን እንድንሆን የሚያደርገን መነቃቃት (ሪቫይቫል) ነው።» የውይይት ጥያቄ:- እንደዚህ ዓይነት አባባሎችን የሰማህበትን ሁኔታ ግለጽ። እነዚህ አገላለጾች ትክክል ይመስሉሃል

የሐዋርያት ሥራ መግቢያ Read More »