የማርቆስ ወንጌል

ኢየሱስ ከሞት ተነሣ (ማር. 16:1-20)

ማርቆስ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ያቀረበው ዘገባ ከሁሉም ወንጌላት አጠር ያለ ነው። ይህም በተለይ ብዙ ምሑራን እንደሚሉት፥ ምዕራፍ 16 ቁጥር 8 ላይ የሚያበቃ ከሆነ እውነት ነው ማለት ይቻላል። የክርስቶስን መቀበር የተመለከቱት ሦስት ሴቶች ወደ መቃብሩ ተመለሱ። በዚህ ጊዜ የተመለከቷቸው መላእክት ክርስቶስ ከሞት እንደ ተነሣና ወደ ገሊላ እንደ ሄደ ነገሯቸው። ደቀ መዛሙርቱ በዚያ ከእርሱ ጋር ተገኝተዋል። ማርቆስ […]

ኢየሱስ ከሞት ተነሣ (ማር. 16:1-20) Read More »

የኢየሱስ መሰቀል፥ መሞትና መቀበር (ማር. 15፡21-47)

ክርስቶስ በደረሰበት ከፍተኛ ድብደባ ምክንያት በመድከሙ፥ ሮማውያን ስምዖን መስቀሉን ተሸክሞ ክርስቶስ ከሁለት ወንበዴዎች ጋር ወደሚሰቀልበት ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ እንዲያደርስ አስገደዱት። ብዙውን ጊዜ ወንጀለኞች ወንጀላቸው የተዘረዘረበት ጨርቅ ከአንገታቸው ላይ ይደረግና መስቀሉን ተሸክመው ወደሚሰቀሉበት ስፍራ እንዲወሰዱ ይገደዱ ነበር። ማርቆስ መስቀሉን የተሸከመው ስምዖን፥ የአሌክለንድሮስና የሩፎስ አባት እንደነበር ገልጾአል። ጳውሎስም በሮሜ 18፡13 ሩፎስን ስለሚጠቅስ፥ እነዚህ ሰዎች ምናልባትም በሮም

የኢየሱስ መሰቀል፥ መሞትና መቀበር (ማር. 15፡21-47) Read More »

ማርቆስ 14፡1-15:20

ኢየሱስ ለመስቀሉ ተዘጋጀ (ማር. 14፡1-42) ሀ. ኢየሱስ ለሞቱ በመዘጋጀት ሽቶ ተቀባ (ማር. 14፡1-11)። የክርስቶስ ሞት ድንገተኛ ነበር? አልነበረም። ክርስቶስ ላለፉት አያሌ ወራት ወደ ተወዳጇ ኢየሩሳሌም ሲደርስ፥ እንደሚገደልና ከሞት ግን እንደሚነሣ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። ከመስቀሉ ሁለት ቀናት ቀደም ብላ አንዲት ሴት ውድ ሽቶ ቀባችው። ክርስቶስ ይህ ለቀብሩ መታሰቢያ እንደሚሆን ገለጸ። በወንጌላት አማካኝነት ከዚያም የዚህች ሴት ታላቅ

ማርቆስ 14፡1-15:20 Read More »

ማር. 12፡41-13:37

ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ስለ እውነተኛ አሰጣጥ አስተማረ (ማር. 12፡41-44)። በተፈጥሯዊ መንገድ የአንድን ለጦታ ታላቅነት ከምንለካባቸው መንገዶች አንዱ የስጦታውን መጠን መመልከት ነው። አንድ መቶ ብር ወይም ከዚያ የበለጠ ገንዘብ የሚከፍሉትን ሰዎች እያደነቅን፥ ዐሥር ሣንቲም ብቻ የሚሰጡትን ቸል እንላለን። ብዙ የሚሰጡትን እያከበርን፥ ጥቂት ብቻ የሚሰጡንን እንንቃለን። ክርስቶስ ግን እግዚአብሔር አንድን ስጦታ የሚለካው፥ ሰጭውን ምን ያህል እንደሚጎዳው በማገናዘብ

ማር. 12፡41-13:37 Read More »

በኢየሱስና የሃይማኖት መሪዎች መካከል የተካሄደ ክርክር (ማር. 11፡27-12፡40)

ማርቆስ፥ «ክርስቶስ በአይሁድ የሃይማኖት መሪዎች ለምን ተገደለ?» የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ የክርስቶስን ሕይወት የመጨረሻ ቀናትና ክርስቶስ ከሃይማኖት መሪዎች ጋር ያካሄዳቸውን ክርክሮች ገልጾአል። ልማዳቸውንና ሰንበትን ባለመጠበቁ ምክንያት፥ የተጠነሰሰው ጥላቻ እያደገ ሄዶ ወደ መስቀል ሞት አድርሶታል። ሀ. በካህናት አለቆችና በሸንጎው አባላት የቀረበ ጥያቄ (ማር. 11፡27-12፡12)። የአይሁድ አለቆች ክርስቶስ በድል አድራጊነት ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱና ከቤተ መቅደስ ውስጥ ነጋዴዎችን ማባረሩ

በኢየሱስና የሃይማኖት መሪዎች መካከል የተካሄደ ክርክር (ማር. 11፡27-12፡40) Read More »

ማርቆስ 11፡1-26

ኢየሱስ እንደ ሰላም ንጉሥ ወደ ኢየሩሳሌም በድል ገባ (ማር.11፡1-11)። አሁን ማርቆስ የክርስቶስን ታሪክ የሚናገርበት መንገድ ተቀይሯል። በፊት ማርቆስ የጊዜ ቅደም ተከተልን ጠቅሶ የዕለት ተዕለት ሁኔታዎችን ካስረዳ በኋላ፥ «ወዲያውኑ» በሚሉ ዓይነት ቃላት ታሪኩን በፍጥነት ይተርክ ነበር፡ አሁን ማርቆስ የዕለት ተዕለት ክስተቶችን ይዘረዝራል። አሁን ቀስበቀስ የታሪኩን ፍጻሜ (የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ) ይገልጻል። በተለይም በስቅለት ዕለት ማርቆስ ክስተቶችን ከሰዓት

ማርቆስ 11፡1-26 Read More »

ማርቆስ 10፡1-52

1. ኢየሱስ ስለ ጋብቻና ፍች አስተማረ (ማር. 10፡1-12)። ፈሪሳውያን ክርስቶስን ለመፈተን በመፈለግ ስለ ፍች ጠየቁት። በዚህ ጊዜ እርሱም በፍች ላይ ያለውን የእግዚአብሔርን አመለካከት ገልጾላቸዋል። ፍች ሁልጊዜም የኀጢአትና በእግዚአብሔር ዓላማ ላይ የማመፅ ምልክት ነው። እግዚአብሔር ጋብቻን የወጠነው ባልና ሚስት በጣም በመቀራረብ በአሳብና በተግባር እንዲጣመሩ ነው። ፍችን ማበረታታት በእግዚአብሔር ፍላጎት ላይ ማመፅ ነው። ፍች የሚፈቀድበት ብቸኛው ጊዜ

ማርቆስ 10፡1-52 Read More »

ማርቆስ 9፡1-50

ኢየሱስ ሰማያዊ ክብሩን ገለጸ (ማር. 9፡1-3)። ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ አንዳንዶቹ ከመሞታቸው በፊት ክብሩን እንደሚያዩ ከተናገረ በኋላ፥ ጴጥሮስን፥ ዮሐንስንና ያዕቆብን ይዞ ወደ ተራራ ወጣ። በዚያም መለኮታዊ ክብሩን ገለጸ። በዚያም ሕግን የወከለው ሙሴና ነቢያትን የወከለው ኤልያስ ቀርበው ከኢየሱስ ጋር ተነጋገሩ። ለሁለተኛ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር የሚወደው ልዩ ልጁ እንደሆነ ሰሙ። ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ምን ያህል እንደ

ማርቆስ 9፡1-50 Read More »

ማርቆስ 8፡1-38

ኢየሱስ አራት ሺህ ሕዝብን መገበ (ማር. 8፡1-21) ክርስቶስ ምንም ያህል ሥራ ቢበዛበትም ስለ ሰዎች ጥቅም የሚያስብ ሲሆን፤ ጉዳታቸው ልቡን ይሰማውና ይራራላቸው ነበር። በዚያን ጊዜ ለሰዎች መጎዳት የራራው ክርስቶስ፥ ዛሬም የሚያስፈልገንን ሁሉ በሚመለከትበት ጊዜ ይራራልናል። ክርስቶስ አሁን አራት ሺህ ሕዝብ ለመመገብ ያነሣሣውን የርኅራኄ ምክንያት ቀደም ሲል አምስት ሺህ ሕዝብ በመገበበት ወቅት፥ ለደቀ መዛሙርቱ አስተምሮ የነበረውን ትምህርት

ማርቆስ 8፡1-38 Read More »

ማርቆስ 7፡1-37

ክርስቶስ ሰውን ስለሚያረክስ ነገር አስተማረ (ማር. 7፡1-23) በማርቆስ ወንጌል ውስጥ ከቀረቡት ረዣዥም ታሪኮች አንዱ፥ ሰውን ስለሚያረከሱና ስለሚያነጹ ነገሮች የሚያስረዳው ነው። ይህ ቤተ ክርስቲያን ልትረዳው የሚገባት ጠቃሚ እውነት ነው። በቀድሞይቱ ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያኖች ይጠይቋቸው ከነበሩት ዐበይት ጥያቄዎች አንዱ፥ «ሃይማኖታዊ ንጽሕናችንን ለማሳየት ልንጠብቃቸው የሚገቡ ትውፊቶች አሉ ወይ?» የሚል ነበር። ለብዙ ምእተ ዓመታት አይሁዶች የተወሰኑ ነገሮችን በማድረግ ውስጣዊ

ማርቆስ 7፡1-37 Read More »