የሕይወት እንጀራ

ትምሕርቶች

ቅድስና 

ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ በደኅንነታችን ውስጥ ስለምናገኛቸው በረከተች ስናጠና ነበርን። በዳንንበት ጊዜ ስላገኘናቸው ብዙ የደኅንነት በረከቶች አጥንተናል። ዳግም በዳንንበት ወቅት፣ እግዚአብሔር በዳግም ልደት አዲስ ሕይወትን ሰጥቶናል። በደኅንነታችን ወቅት በውስጣችን ሊኖር ካመጣው ከክርስቶስ ጋር ኅብረት በምናደርግበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እኛን ከክርስቶስ ጋር አንድ አድርጎ ያየናል። እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር በማለት ደኅንነትን ባገኘንበት ወቅት፣ ወዲያው መጽደቃችንን አስታውቆልናል። እንደ ልጆቹ […]

ቅድስና  Read More »

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

በደኅንነታችን ውስጥ ካገኘናቸው በረከቶች መካከል በጣም የሚያስደስተንና የሚያጽናናን የእግዚአብሔር ጎልማሳ ልጆች ከመሆናችን የተነሣ ያለን የተትረፈረፈ የርስት ዋስትና ነው። በዚህ ረገድ እግዚአብሔር አዲስ ሕይወትን፥ ከክርስቶስ ጋር ኅብረትን እንዲሁም ከበደላችን ነፃ መውጣትን የሰጠን ብቻ ሳይሆን በተጨማሪም የራሱ ልጆችና የሰማያዊ ክብር ወራሾችም እንድንሆን መብት ሰጥቶናል። የእግዚአብሔር አዋቂ (ጎልማሳ) ልጆች የመሆን በረከት የ«ጉዲፈቻ የማደጎ ልጅ» መሆን ማለት ነው።  ጥያቄ፡-

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ)  Read More »

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

የደኅንነት በረከተች – ክፍል 2  በትምህርት 11ና 12 ውስጥ ከኃጢአታቸው የተነሣ በሰዎች ስለሚደርሰው አላከሪ ሁኔታ ተመልክተናል። በመጀመሪያ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች ሆነው በመወለዳቸው፥ እንደዚሁም በዮላቸው ኃጢአት ከመሥራታቸው ሁሉም በመንስ ሞተዋል! ደሞ በሥጋ ይሞታሉ። ሁለተኛ፤ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኛነትን ባሕርይ ይዘው ስለ ተወለዱና በየግላቸውም ኃጢአትን በመሥራታቸው፥ ሁሉም በእግዚአብሔር ፊት ከኃጢአታቸው የተነሣ በደለኞች ናቸው። ነገር ን እግዚአብሔር እነዚህን የኃጢአት

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ  Read More »

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

በትናንትናው ዕለት ከክርስቶስ ጋር መተባበር ምን ማለት እንደሆነ ማጥናት ጀምረን ነበር። በጥናታችን ወቅትም ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ከክርስቶስ ጋር ሞተን የተነሣን፥ እግዚአብሔር ክርስቶስን በሚመለከትበት ዓይኑ እንደሚያየን፥ ክርስቶስ በውስጣችን እንደሚኖርና እኛም በምድር ላይ የሚታየው የክርስቶስ አካል መሆናችንን አስተውለናል። ይህ ከክርስቶስ ጋር የምንተባበርበት እያንዳንዱ ሁኔታ አስደናቂ በረከት ነው። ሆኖም አማኞች ከክርስቶስ ጋር ባላቸው ኅብረት የተነሣ የሚመጡ ብዙ

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው?  Read More »

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ክርስቲያኖች ሊደሰቱበት ከሚገባቸው እጅግ በጣም ጥልቅና ምሥጢራዊ የሆኑ የደኅንነት በረከቶች አንዱ ከክርስቶስ ጋር የሚኖራቸው ኅብረት ነው። በአንድ አኳኋኑ ሲታይ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ሲባል፥ የደኅንነትን በረከቶች ሁሉ የሚሸፍን አሳብ ነው። በብዙ ክፍለ ምንባቦች ላይ «በክርስቶስ» መሆን ወይም «ከክርስቶስ ጋር መተባበር» ሲባል፥ ሐረጉ ክርስቲያን ወይም በክርስቶስ አማኝ መሆን ማለት ይሆናል። ይህን የተላመደ ማዕከላዊ ሃሳብ በተለየ ርእስ በመውሰድ

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው?  Read More »

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

በትናንትናው ዕለት ስለ ዳግም መወለድ ማጥናት ጀምረናል። ስለ ዳግም መወለድም እንደ ቁልፍ የሆነ ጥቅስ ያጠናን ሲሆን፥ እርሱም ዮሐ 3፡1-8 ነበር። በዚህ ጥቅስ ላይም ዳግም መወለድ ሊባል የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ሊሰጠን የሚፈጽመው ሉዓላዊ የማንጻት ተግባር እንደሆነ ተምረናል። ዛሬ ደግሞ በተቀሩት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ስለ ጳም መወለድ ወይም ልደት የሚነግሩንን ቁልፍ የሆኑ ጥቅሶችን

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2  Read More »

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

የደኅንነት በረከቶች – ክፍል አንድ  በዛሬው ትምህርታችን እግዚአብሔር ስለሚሰጠን የደኅንነት በረከተች እናጠናለን። እንደሚታወቀው እኛ በኃጢአት የተወለድን ከመሆናችንም በላይ እያንዳንዳችን ብዙ የኃጢአት ተግባራትን ስለምንፈጽም በኃጢአታችን ሙታን ነን። ስለዚህ እግዚአብሔር በሕይወታችን ውስጥ ጣልቃ ገብቶ ከኃጢአታችንና ከሚያስከትልብን ክፉ መዘዝ ሁሉ ሊያድነን ይገባል። ትዝ እንደሚላችሁ ደኅንነት እንደሚያስፈልገን በትምህርት 11ና 12 ላይ አጥንተናል። እግዚአብሔር እኛን መርጦ ወደ ራሱ ሊያቀርበን በማለት

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1  Read More »

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

1. መርሆ፡- ታዛዥነትና መልካም ሥራ የሚያድን እምነት ማረጋገጫዎች ናቸው።  ባለፉት ሦስት ቀናት ወደ ደኅንነት ስለሚያደርሱ መንገዶች ስናጠና ነበር። አዲስ ኪዳን ግልጽ እንደሚያደርገው ሰዎች የክርስቶስን ደኅንነት ለመቀበል እንዲችሉ አንድ ነገር ማድረግ አለባቸው፡- በራሳቸው መታመንን ትተው ወደ ክርስቶስ መመለስ አለባቸው። ይህም ስለ ደኅንነታቸው በበጎ ሥራቸው ላይ ማተኮርን በመተው በኢየሱስና እርሱ በሞቱና በትንሣኤው ባከናወናቸው ድርጊቶች ላይ መመርኮዝ ይጠበቅባቸዋል።

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል?  Read More »

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ለደኅንነት አስፈላጊ ስለሆኑ ነገሮች ተምረናል። በዚህን ጊዜ ለደኅንነት አንድ ነገር ብቻ እንደሚያስፈልግ ተመልክተናል። ነገር ግን ይህ አንድ ነገር ደግሞ በሦስት ልዩ ልዩ መንገዶች እንደሚገለጽ አስተውለናል። አንዳንድ ጊዜ ይህ ነገር «ንስሐ» ተብሎ ይገለጻል። ስለዚህ ለመዳን ከራሳችን ይልቅ ወደ ክርስቶስ ብቻ መመለስ አለብን። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ይህ የደኅንነት አንድ ነገር «እምነት» ይባላል። ስለዚህ

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ»  Read More »

እምነት 

ትናንትና ለደኅንነት አስፈላጊ ስለሆኑት ነገርች ጥናታችንን ጀምረን ነበር። በመሠረቱ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ደኅንነት አንድ አስፈላጊ የሆነ ነገር ብቻ ይሰጠናል። ይህንንም አንድ አስፈላጊ የሆነ ነገር በሦስት የተለያዩ መንገዶች ይገልጻቸዋል። አንዳንድ ጊዜም መጽሐፍ ቅዱስ ለደኅንነት አስፈላጊ የሆነውን ነገር እንደ «ንስሐ» አድርጎ ያቀርበዋል። በሌላ ጊዜም መጽሐፍ ቅዱስ ለደኅንነት ተፈላጊውን ነገር ሲጠቅስ፥ «እምነት» መሆኑን ይናገራል። እንደዚሁም መጽሐፍ ቅዱስ ለደኅንነት

እምነት  Read More »