የሕይወት እንጀራ

ወደ ሮሜ ሰዎች

ሮሜ 5፡1-21

ኃጢአተኛው በእግዚአብሔር ከጸደቀ በኋላ የሚቀበላቸው በረከቶች (ሮሜ 5፡1-11) የውይይት ጥያቄ፡– ሮሜ 5፡1-11 አንብብ። እግዚአብሔር በክርስቶስ ለሚያምኑ ሰዎች የሚሰጣቸውን የተለያዩ በረከቶች ዘርዝር። አብርሃም በእምነቱ ምክንያት ተስፋ የተገባለትን ልጅ አግኝቷል። እኛስ ክርስቶስን ብቸኛ የድነት (የደኅንነት) መንገድ እንደሆነ ስናምን ምን እናገኛለን? ጳውሎስ ብዙ ልንደርስባቸው የምንችልባቸውን በረከቶችን ዘርዝሯል። ሀ. ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ይኖረናል። ከእንግዲህ ከእግዚአብሔር ጋር እየተዋጋን ከፍርዱ ሥር […]

ሮሜ 5፡1-21 Read More »

እምነት እንጂ ሥራችን እንደማያድነን የሚያሳዩ የብሉይ ኪዳን ምሳሌዎች (4:1-25)

የውይይት ጥያቄ፡- እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያጸድቀው በእምነት እንጂ በሥራ እንዳልሆነ ጳውሎስ ያረጋገጠበትን ሁኔታ በአጭሩ አብራራ። የጳውሎስን መልእክት የሚያነቡ አይሁዶች አዲስ የድነት (የደኅንነት) መንገድ እያቀረበልን ነው የሚል ስጋት አድሮባቸው ነበር። በተለይም እግዚአብሔር ሕግጋቱን የሚታዘዙትን እንደሚቀበል ያስተምራል ብለው ከሚያስቡት የብሉይ ኪዳን ትምህርት ተቃራኒ ስለመሰላቸው ተጨንቀው ነበር። «በእምነት መዳን በብሉይ ኪዳን የተገለጠውን እውነት አይሽረውም ወይ?» ሲሉ ጠየቁ። ጳውሎስ ግን

እምነት እንጂ ሥራችን እንደማያድነን የሚያሳዩ የብሉይ ኪዳን ምሳሌዎች (4:1-25) Read More »

የድነት (ደኅንነት) መሠረቱ የክርስቶስ ስለ ኃጢአተኞች መሞት ነው (ሮሜ 3፡21-31)

ጳውሎስ የወንጌል ገለጻውን ከክርስቶስ ሳይሆን ከሰዎች ኃጢአተኝነት እንደሚጀምር ከዚህ በፊት በነበረው ትምሕርታችን ተመልክተናል። ጳውሎስ መንፈሳዊና መልካም ሥነ ምግባራዊ ሕይወት ያላቸው የሚመስሉትን ጨምሮ ሰዎች ሁሉ ምን ያህል ልባቸው በክፋት እንደተሞላ እንዲያውቁ ይፈልጋል። ይህንንም ያደረገው ተስፋ እንዲቆርጡ ለማድረግ ሳይሆን፥ «እድን ዘንድ ምን ላድርግ?» የሚል ጥያቄ እንዲያነሡና ለድነት (ለደኅንነት) ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ ነው። ጳውሎስ ስለ ድነት (ደኅንነት) ባቀረበው

የድነት (ደኅንነት) መሠረቱ የክርስቶስ ስለ ኃጢአተኞች መሞት ነው (ሮሜ 3፡21-31) Read More »

ሁሉም ሰው ኃጢአተኛ ስለሆነ ደኅንነትን ማግኘት ይኖርበታል (ሮሜ 3፡9-20)

የውይይት ጥያቄ፡– ሮሜ 3፡9-20 አንብብ። ሀ) ጳውሎስ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች ስለመሆናቸው የሚሰጠው መደምደሚያ ምንድን ነው? ለ) ሰዎች ሁሉ በክርስቶስ ከማመናቸው በፊት ይህን እውነት ማወቅ ያለባቸው ለምን ይመስልሃል? ጳውሎስ ስለ ሰዎች ኃጢአተኝነት ያቀረበውን የመጀመሪያውን ክፍል ትምህርት በግልጽ አሳብ አጠቃሎታል። ይህም ሰዎች ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአተኞች ናቸው የሚል ነው። የተጻፈ የእግዚአብሔር ሕግ ባይኖራቸውም እንኳን፥ አሕዛብ ሁሉ ኃጢአተኞች

ሁሉም ሰው ኃጢአተኛ ስለሆነ ደኅንነትን ማግኘት ይኖርበታል (ሮሜ 3፡9-20) Read More »

ሃይማኖተኛ የሆኑ አይሁዶችም ኃጢአተኞች ናቸው (ሮሜ 2፡1-3፡8)

የውይይት ጥያቄ፡- ሮሜ 2፡1-3፡8 አንብብ። አይሁዶች (እና የትኛውም ሃይማኖተኛ ጥሩ ሰው) በቅዱስ አምላክ ፊት ኃጢአተኞች መሆናቸውን በራስህ ቃል በአጭሩ አስረዳ። አይሁዶችና ሌሎች ጥሩ ሃይማኖተኛ ሰዎች ስለ አሕዛብ ኃጢአተኝነት በሚያነቡበት ጊዜ ኩራት ሳይሰማቸው አይቀርም። ጥቂት ሰዎች፥ «እኛ እንደ እነርሱ ክፉዎች አይደለንም። የእግዚአብሔርን ሕግጋት እናከብራለን። የወሲብ ኃጢአት አንፈጽምም። ማንንም አልገደልንም። ጣዖታትን እናመልክም። ስለዚህ እግዚአብሔር ሊቀበልን ይገባል» ብለው

ሃይማኖተኛ የሆኑ አይሁዶችም ኃጢአተኞች ናቸው (ሮሜ 2፡1-3፡8) Read More »

አሕዛብ ኃጢአትን ሠርተዋል (ሮሜ 1፡18-32)

ወንጌል የሚለው ቃል መልካም የምሥራች ማለት ነው። ይህ እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ሁሉ ይቅር ብሎ በነፃ እንደሚያሰናብተን የሚያረጋግጥ አዋጅ ነው። በቤተሰቡ ውስጥ ተቀባይነትን አግኝተን ለዘላለም ልንድን እንችላለን። ሌላኛው የወንጌሉ ገጽታ «የእግዚአብሔር ቁጣ» ነው። ይህ ቁጣ ባልዳኑት ሰዎች ላይ እግዚአብሔር የሚያሳየው የጥላቻ ስሜት እይደለም። እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ እንደሚወድ እናውቃለን (ዮሐ. 3፡16)። ነገር ግን ይህ ቁጣ እግዚአብሔር ዐመፃን በሚያደርጉት

አሕዛብ ኃጢአትን ሠርተዋል (ሮሜ 1፡18-32) Read More »

ጳውሎስ ለሮሜ ክርስቲያኖች ያቀረበው ሰላምታና የመልእክቱ ዓላማ (ሮሜ 1፡1-17)

፩. ጳውሎስ ለሮሜ ክርስቲያኖች ያቀረበው ሰላምታ (ሮሜ 1፡1-7) ምንም እንኳ የሮሜ መልእክት ከደብዳቤነቱ ይልቅ ወደ ትምህርታዊ ሐተታነቱ የሚያደላ በመሆኑ ለየት ያለ ቢሆንም፥ ጳውሎስ በመግቢያው ጥንታዊ የደብዳቤ አጻጻፍን ይከተላል። ሁሉም የጳውሎስ መልእክቶች መግቢያ ቢኖራቸውም፥ የሮሜ መልእክት መግቢያ ረዘም ያለና ከሌሎቹ ሁሉ ያነሰ ግላዊ ጉዳዮች ያሉበት ነው። የጥንት ሰዎች መጀመሪያ የሚያነሡት ጥያቄ፥ «የዚህ መልእክት ጸሐፊ ማን ነው?»

ጳውሎስ ለሮሜ ክርስቲያኖች ያቀረበው ሰላምታና የመልእክቱ ዓላማ (ሮሜ 1፡1-17) Read More »

የሮሜ መልእክት መዋቅርና እና አስተዋጽኦ

፩. የሮሜ መልእክት መዋቅር የውይይት ጥያቄ፡– ይህን የሮሜ መልእክት እቀራረፅ በጥንቃቄ ካጠናህ፥ በሮሜ ውስጥ የጳውሎስን ትምህርት ፍሰት በሚገባ ልትገነዘብ ትችላለህ። ከዚህ በታች የቀረቡት ሰባት ነጥቦች ወንጌል ለሚያካትታቸው ነገሮች መልካም ማጠቃለያ የሚሆኑት እንዴት ነው? ጳውሎስ ስለ ወንጌልና እግዚአብሔር ሰዎችን ስለሚያጸድቅበት ሁኔታ የጻፈውን አሳብ ጠቅለል ባለ መልክ (ርዕሰ-ጉዳይ) ማስቀመጡ የሮሜን መልእክት ለመረዳት ይረዳናል። ከሮሜ ውስጥ አንድ ክፍል

የሮሜ መልእክት መዋቅርና እና አስተዋጽኦ Read More »

የሮሜ መልእክት ልዩ ገጽታዎች

ከቆላስይስ በስተቀር አብዛኞቹ የጳውሎስ ደብዳቤዎች በተወሰኑ ጉዳዮችና የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎቶች ላይ ሲያተኩሩ፥ የሮሜ መልእክት በአብዛኛው አጠቃላይ የሆኑና ነገረ መለኮታዊ ጉዳዮችንም ያነሣል። አንዳንድ ምሁራን ጳውሎስ የሮምን ቤተ ክርስቲያን ስላልጎበኘ፥ ስለ ሮም ቤተ ክርስቲያን ዝርዝር ጉዳዮች የሚያውቀው እንዳልነበረው ይገምታሉ። ስለሆነም፥ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ክርስቲያኖች በሚጋፈጧቸው አጠቃላይ ጉዳዮች ላይ አተኮረ። በተጨማሪም፥ አማኞች ሊያውቋቸው ስለሚገቧቸው መሠረታዊ አስተምህሮዎች

የሮሜ መልእክት ልዩ ገጽታዎች Read More »

የሮሜ መልእክት ዓላማ

የውይይት ጥያቄ፡- ሮሜ 1፡1-17 አንብብ። «ወንጌል» የሚለው ቃል ስንት ጊዜ እንደተጠቀሰ ቁጠር። ይህ ጳውሎስን ስላሳሰበው ዋንኛ ጉዳይ ምን ይነግረናል? የሮሜን መልእክት በጥንቃቄ በምናጠናበት ጊዜ ጳውሎስ ይህን መልእክት ለመጻፍ ያነሣውት አያሌ ዓላማዎች እንደነበሩት እንረዳለን። በታሪክ ሁሉ ክርስቲያኖች፥ የሮሜ መልእክት የእግዚአብሔርን የድነት (የድኅንነት) መንገድ የሚያሳይና እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ድነትን (ደኅንነትን) ለመስጠት በወጠነው ዕቅድ ውስጥ ክርስቶስ ምን ዓይነት

የሮሜ መልእክት ዓላማ Read More »