የሕይወት እንጀራ

ወደ ሮሜ ሰዎች

የጳውሎስ የግል ምስክርነት፣ ዕቅዶችና ሰላምታ (ሮሜ 15፡14-16፡27)

፩. የጳውሎስ የግል ምስክርነትና ዕቅዶች (ሮሜ 15፡14-33) የውይይት ጥያቄ፡- ሮሜ 15፡14-33 አንብብ። ሀ) ጳውሎስ ስለ ራሱ የሰጠው መግለጫ ለሮሜ ሰዎች መልእክት የጻፈበትን ሁኔታ የሚያስረዳው እንዴት ነው? ለ) ጳውሎስ ስለ ወደፊት አገልግሎቱ ምን አለ? ሰዎችንና አሳባቸውን በተሳሳተ መንገድ መረዳቱ ቀላል ነው። ብዙዎቻችን ከሰዎች ቃላት በስተጀርባ የተደበቁትን ፍላጎቶችን እየፈለግን በተሳሳተ መንገድ እንተረጉማለን። ከዚህም የተነሣ በማያስፈልግ መቀያየም ውስጥ […]

የጳውሎስ የግል ምስክርነት፣ ዕቅዶችና ሰላምታ (ሮሜ 15፡14-16፡27) Read More »

ክርስቲያኖች የተለየ አመለካከት ያላቸውን ክርስቲያኖች የሚያስቀይም ነገር ባለማድረግ ፍቅራቸውን ያሳያሉ (ሮሜ 13፡14-15፡13)

ሰላማዊት በአጥባቂ ቤተሰብ ውስጥ ያደገች ክርስቲያን ነበረች። ጥሩ ክርስቲያኖች ጌጣጌጥ እንደማይጠቀሙ፥ ከንፈራቸውንም ሆነ ጥፍራቸውን ቀለም እንደማይቀቡ፥ ፊልም ቤት እንደማይሄዱ፥ ፋሽን ልብስ እንደማይለብሱ፥ በቤተ ክርስቲያን ስካርፎችን እንደማይለብሱ፥ ወዘተ… ገና በትንሽነቷ ተምራለች። ፍቅርተ ደግሞ ክርስቲያን ባልሆኑ ሀብታም ቤተሰብ ውስጥ ያደገች ሴት ነበረች። ሁልጊዜም ሕይወቷ በፋሽን ልብሶች፥ ጌጣጌጦች፥ ፊልሞች፥ የፀጉር ስታይሎች፥ ወዘተ… የታጀበ ነበር። ፍቅርተ ክርስቲያን ስትሆን፥ እነዚህ

ክርስቲያኖች የተለየ አመለካከት ያላቸውን ክርስቲያኖች የሚያስቀይም ነገር ባለማድረግ ፍቅራቸውን ያሳያሉ (ሮሜ 13፡14-15፡13) Read More »

አማኞች ባለሥልጣንት የሚታዘዙና በፍቅር የሚመላለሱ ናቸው (ሮሜ 13፡1-13)

፩. አማኞች ለሰብአዊ መንግሥታቸው ይጸልያሉ፥ ይታዘዛሉ (ሮሜ 13፡1-7) እንደ ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች ከመንግሥትና ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር የቀረበ ግንኙነት የለንም። በቀደመው ሥርዓት የስደት ምንጮች ሆነው እሠቃይተውናል። አሁን ድምፅ የመስጠት ዕድል ሲሰጠን ደግሞ ብዙ አማኞች ድምፅ ለመስጠት ፈቃደኞች አይደሉም። ለአገልግሎት ሲጠይቁንም አዎንታዊ ምላሽ አንሰጥም። ከመንግሥት በመራቃችን ደስ የምንሰኝ ይመስላል። ጳውሎስ ግን ከመንግሥት ጋር የጠበቀ ግንኙነት ሊኖረን እንደሚገባ ይመክራል።

አማኞች ባለሥልጣንት የሚታዘዙና በፍቅር የሚመላለሱ ናቸው (ሮሜ 13፡1-13) Read More »

ወንጌሉ የአማኞችን አኗኗር ይለውጣል (ሮሜ 12፡1-21)

ጥሩነሽ በቅርቡ በክርስቶስ አምናለች። መንፈስ ቅዱስ ኃጢአተኛ እንደሆነችና ይቅርታ ልታገኝ የምትችልበት ብቸኛው መንገድ ለኃጢአት በሞተው በክርስቶስ በማመን መሆኑን ለልቧ መስክሮላታል። ጥሩነሽም በኃጢአተኝነት ስሜት ተሞልታና እግዚአብሔር ለእርሷ ስላለው ፍቅር ተደንቃ ክርስቶስ ለኃጢአቷ የሞተ አዳኝዋና ጌታዋ እንደሆነ አመነች። በዚህ ጊዜ ሰላም ልቧን ሞላው። የእግዚአብሔር ልጅ ሆነች። ነገር ግን ከዚህ በኋላ ማድረግ ያለባት ነገር ምንድን ነው? አሁን ልጁ

ወንጌሉ የአማኞችን አኗኗር ይለውጣል (ሮሜ 12፡1-21) Read More »

አይሁድ፣ በዚህ ዘመን ቅሬታቸው ሲድኑ አንድ ቀን ደግሞ እንደ አንድ ሕዝብ ይድናሉ (ሮሜ 11፡1-36)

የውይይት ጥያቄ፡– ሮሜ 11ን አንብብ። ሀ) ጳውሎስ እግዚአብሔር ከአይሁዶች ጋር ስለሚያደርገው የአሁንና የወደፊት ግንኙነት ምን አለ? ለ) ጳውሎስ ለአሕዛብ ክርስቲያኖች የሰጣቸው ማስጠንቀቂያ ምን ነበር? አይሁዶች እንደ ሕዝብ የእግዚአብሔርን የድነት (ደኅንነት) መንገድ ለመቀበል ስላለመፈለጋቸው ጳውሎስ የሚሰጠውን ትንታኔ የሚሰማ አይሁዳዊ ክርስቲያን፥ «ይህ ማለት እግዚአብሔር ከእንግዲህ ለአይሁዶች ልዩ ዕቅድ የለውም ማለት ነው?» የሚል ጥያቄ ማንሣቱ የማይቀር ነው። ጳውሎስ

አይሁድ፣ በዚህ ዘመን ቅሬታቸው ሲድኑ አንድ ቀን ደግሞ እንደ አንድ ሕዝብ ይድናሉ (ሮሜ 11፡1-36) Read More »

ሮሜ 9፡30-10፡21

ብዙ አይሁዶች እግዚአብሔር የማይቀበለውን የድነት (ደኅንነት) መንገድ በመከተላቸው ምክንያት አልዳኑም (ሮሜ 9፡30-33)። «አይሁዶች በኢየሱስ የማያምኑት ለምንድን ነው? ይህ ክርስቶስ መሢሕ አለመሆኑን አያሳይምን?» በማለት ሰዎች ጳውሎስን ይጠይቁት ነበር። ጳውሎስ ላለማመናቸው ምክንያቱ የክርስቶስ መሢሕ አለመሆን ሳይሆን አይሁዶች ድነትን (ደኅንነትን) ወይም ጽድቅን በተሳሳተ መንገድ መፈለጋቸው እንደሆነ አብራርቷል። አይሁዶች ከእግዚአብሔር ዘንድ ድነት እና ማረጋገጫ ለመቀበል የፈለጉት በውርላሳቸው፥ በግርዛታቸውና በመልካም

ሮሜ 9፡30-10፡21 Read More »

የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ምርጫ (ሮሜ 9፡1-29)

የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ «ድነት (ደኅንነት)» የሚለው ቃል የሚያስተላልፋቸውን ፍቺዎች በሙሉ ዘርዝር። ለ) እግዚአብሔር አንተን ያደነባቸውን የተለያዩ መንገዶች ዘርዝር። ድነት (ደኅንነት)፡- በሁሉም ቋንቋዎች ውስጥ ከሚገኙ ውድ ቃላት አንዱ ድነት (ደኅንነት) ነው። ቃሉ በብዙ የተለያዩ መንገዶች ያገለግላል። አንድ ሰው ከአደጋ በሚተርፍበት ጊዜ ድኗል እንላለን። አንዲት ሴት በጠና በታመመች ጊዜ የታዘዘላት መድኃኒት ካሻላት አድኖአታል ማለት

የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ምርጫ (ሮሜ 9፡1-29) Read More »

ሮሜ 8፡1-39

፩. እግዚአብሔር ልጆቹ የኃጢአትን ኃይል ያሸንፉ ዘንድ መንፈስ ቅዱስን ሰጥቷቸዋል (ሮሜ 8፡1-17) የውይይት ጥያቄ፡- ሮሜ 8ን አንብብ። ) ክርስቲያን ሕግን ከመጠበቅ፥ በእግዚአብሔር ጻድቅ ከመደረግና ከኃጢአት ተፈጥሮ ኃይል ጋር ያለውን ግንኙነት ጠቅለል አድርገህ ግለጽ። 2) መንፈስ ቅዱስ ለአማኙ የሚያደርጋቸውን ነገሮች ዘርዝር። 3) ጳውሎስ የክርስቲያኑን የወደፊት ተስፋ እንዴት ይገልጸዋል? 4) ጳውሎስ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያለንን ግንኙነት አስተማማኝ

ሮሜ 8፡1-39 Read More »

አማኞች ብዙውን ጊዜ ከኃጢአት ባሕርያቸው ጋር ይዋጋሉ። ለሽንፈትም ይዳረጋሉ (ሮሜ 7፡7-25)።

ጳውሎስ ሕጉ የገለጣቸው የኃጢአት ምኞቶች በሕይወታችን ውስጥ የሚታየው የኃጢአት ችግር አካላት መሆናቸውን ገልጾአል። የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን ለሚያከብረው አይሁዳዊ ይህን መቀበሉ አስቸጋሪ ነበር። የእግዚአብሔር ሕግ መልካም ነው። መልካም የሆኑት የእግዚአብሔር ሕግጋት እንዴት የክፋት መሣሪያ ሊሆኑ ይችላሉ? ጳውሎስ ችግሩ ያለው ከሕጉ ሳይሆን ከኃጢአት ባሕሪያችንና ለእግዚአብሔር ሕግጋት ከሚሰጠው ምላሽ እንደሆነ ገልጾአል። ለልጅ፥ «ድስቱ ይፈጅሃልና አትንካው» ብትለው፥ ምን ያደርጋል?

አማኞች ብዙውን ጊዜ ከኃጢአት ባሕርያቸው ጋር ይዋጋሉ። ለሽንፈትም ይዳረጋሉ (ሮሜ 7፡7-25)። Read More »

ከኃጢአት ተፈጥሯችን ጋር ያለን ግንኙነትና እግዚአብሔር ኃጢአትን እንድናሸንፍ እንዴት እንደሚረዳን መገንዘብ (ሮሜ 6፡1-7፡6)

ዘሪሁን ወደ ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት የታወቀ ኃጢአተኛ ነበር። ብዙውን ጊዜ ጠጥቶ የሚሰክር ሲሆን፥ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ይሄድ፥ ዕጽ ይወስድና መጥፎ ዐመሉን ለማስታመም ገንዘብ ይሰርቅ ነበር። አንድ ሰው በክርስቶስ ካመነ እግዚአብሔር ኃጢአቶችን ይቅር እንደሚል ሲገለጽለት፥ ዘሪሁን በክርስቶስ አመነ። በዚህ ጊዜ የክርስቶስ ፍቅርና ጸጋ አስደነቀው፥ ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር ልጅ ሊመራ ስለሚገባው ሕይወት ያስተማረው ሰው አልነበረም። ዘሪሁን

ከኃጢአት ተፈጥሯችን ጋር ያለን ግንኙነትና እግዚአብሔር ኃጢአትን እንድናሸንፍ እንዴት እንደሚረዳን መገንዘብ (ሮሜ 6፡1-7፡6) Read More »