የሕይወት እንጀራ

የሉቃስ ወንጌል

ኢየሱስ በዐሥራ ሁለት ዓመቱ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ ( ሉቃስ 2፡41-52)

አንድም የወንጌል ጸሐፊ ኢየሱስ ከመወለዱ ጀምሮ ሠላሳ ዓመት እስኪሞላው ድረስ ስለ ነበሩት ዓመታት ምንም ነገር አልነገረንም። ስለ ኢየሱስ የልጅነት ጊዜ ብናውቅ እንወድ ነበር። ምን ሠርቶ ነበር? ምን ያደርግ ነበር? አንዳንዶች ይህንን ነገር ባለማወቃቸው ግራ ተጋብተው ኢየሱስ በልጅነቱ ስለፈጸማቸው ተአምራት የፈጠራ ታሪኮችን አዘጋጅተዋል። ይሁንና ኢየሱስ ኃጢአት ካለመሥራቱ በቀር ከሌሎች የናዝሬት ከተማ ልጆች የተለየ ነገር የታየበት አይመስልም። […]

ኢየሱስ በዐሥራ ሁለት ዓመቱ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ ( ሉቃስ 2፡41-52) Read More »

የመሢሑ የኢየሱስ መወለድ (ሉቃስ 2፡1-40)

የውይይት ጥያቄ፡- ምርጫው ቢሰጥህ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ በምን ዐይነት ቤት ውስጥ እንዲወለድ ታደርግ ነበር? የትኛውን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ደረጃ ትመርጥለት ነበር? የኢየሱስን ሕይወት ከዓለም ታሪክ አያይዞ ያቀረበው ሉቃስ ብቻ ነው። ከሮም ታላላቅ ነገሥታት አንዱ የሆነው አውግስጦስ ቄሣር በሥልጣን ላይ የቆየው ከ31 ዓ.ዓ. እስከ 14 ዓ.ም. ነበር። ቄሬኔዎስ ከ6–4 ዓ.ዓ (ሉቃስ የጠቀሰው ዘመን) ድረስ ሁለት ጊዜ

የመሢሑ የኢየሱስ መወለድ (ሉቃስ 2፡1-40) Read More »

የመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ (ሉቃስ 1:57-80)

በዚህ ታሪክ ሉቃስ የኢየሱስ መንገድ ጠራጊ ወደሆነው ወደ መጥምቁ ዮሐንስ መወለድ ይመለሳል። በአይሁድ ባህል መሠረት፣ ዮሐንስ ስምንት ቀን ስለ ሞላው ከተገረዘ በኋላ ስም የማውጣት ሥነ ሥርዓት ተካሄደ። አይሁዶች ብዙ ጊዜ ልጅን በአባት ወይም በዘመድ ስም ይጠሩ ስለ ነበር፣ ጎረቤቶቻቸው ዘካርያስ ብለው ሊሰይሙት ፈለጉ። ነገር ግን ኤልሳቤጥ ልጁ ዮሐንስ መባል እንዳለበት ታውቅ ነበር። ስለዚህ ዘካርያስም ልጁ

የመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ (ሉቃስ 1:57-80) Read More »

ማርያም ኤልሳቤጥን ጎበኘች (ሉቃስ 1፡39-56)

መልአኩ በቅርቡ ስለሚፈጸመው ሁለተኛው ተአምራዊ ልደት ለማርያም ነግሯት ሲሄድ፥ ማርያም በልቧ ውስጥ የሚጋጭ ስሜት እንደ ፈጠረባት ልንገምት እንችላለን። ማርያም ስለዚሁ ጉዳይ ለመነጋገር በመፈለጓ ምክንያት ብዙ ኪሎ ሜትር ተጉዛ ወደ ዘመዷ ወደ ኤልሳቤጥ ዘንድ ሄደች፡፡ በአይሁድ ባሕል ወጣት ሴቶች ከቤታቸው ወጥተው ሩቅ መንገድ ለመሄድ ስለማይችሉ፣ ይህንን ማድረጉ ለማርያም ቀላል አልነበረም። እግዚአብሔር አንድ ከባድ ነገር እንድናደርግ ሲጠይቀን፥

ማርያም ኤልሳቤጥን ጎበኘች (ሉቃስ 1፡39-56) Read More »

ስለ ኢየሱስ መወለድ አስቀድሞ ተነገረ (ሉቃስ 1፡26-38)

ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ከሚኖሩበት አካባቢ በሰሜን በኩል ራቅ ብሎ በሚገኝ ስፍራ ምናልባትም 15 ወይም 16 ዓመት የሚሆናት አንዲት ልጃገረድ ትኖር ነበር። ይህች ልጃገረድ ለዮሴፍ የታጨች ነበረች። መልአኩ ገብርኤል አንድ ቀን መጥቶ መልካም ዜና ባበሠራት ጊዜ አባባሉ አሳብ ላይ ጣላት። ገብርኤል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በስማቸው ከተጠሩ ሁለት መላእክት መካከል አንዱ ነው። ሌላው በስሙ የተጠራው ሚካኤል ነው (ዳን.

ስለ ኢየሱስ መወለድ አስቀድሞ ተነገረ (ሉቃስ 1፡26-38) Read More »

የሉቃስ ወንጌል ዐላማ እና የመጥምቁ ዮሐንስ በተአምር መፀነስ (ሉቃስ 1:1-25)

ደመራዝ የአንድ ዕውቅ ወንጌላዊ ልጅ ነበረች። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ካጠናቀቀች በኋላ የጸሐፊነት ሥልጠና እንድታገኝ እግዚአብሔር ረዳት። ከዚያም ለአንድ ነጋዴ ተቀጥራ ለመሥራት አሰበች። አንድ ቀን አንድ ከገጠሪቱ ኢትዮጵያ የመጣ ወንጌላዊ ለጋብቻ ጠየቃት። የወንጌላዊው ጥያቄ ደመራዝን አስከፋት። ሰውዬው የገጠር ወንጌላዊ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፥ አሥራ ሁለተኛ ክፍል ያጠናቀቀው በቅርቡ ነበር፡ ደመወዙ ትንሽ ስለሆነ ይጠቅሙኛል ብላ የምታስባቸውና የወርቅና የብር

የሉቃስ ወንጌል ዐላማ እና የመጥምቁ ዮሐንስ በተአምር መፀነስ (ሉቃስ 1:1-25) Read More »

የሉቃስ ወንጌል አወቃቀር እና አስተዋጽኦ

፩. የሉቃስ መጽሐፍ አወቃቀር የሉቃስ ወንጌል በአራት ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል። ሀ. የኢየሱስ ልደትና የልጅነት ጊዜ (ሉቃስ 1-2) ለ. የኢየሱስ አገልግሎት በገሊላ (ሉቃስ 3፡1-9፡50) ሐ. የኢየሱስ አገልግሎት ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ (ሉቃስ 9፡51–19፡27) መ. የኢየሱስ አገልግሎት በኢየሩሳሌም (ሉቃስ 19፡28-24፡53) ፪. የሉቃስ መጽሐፍ አስተዋጽኦ 1. የሉቃስ ወንጌል መግቢያ (ሉቃስ 1፡1-4) 2. ኢየሱስ በምድር ላይ ላለው አገልግሎት ያደረገው ዝግጅት (ሉቃስ 1፡5-4፡13)

የሉቃስ ወንጌል አወቃቀር እና አስተዋጽኦ Read More »

የሉቃስ ወንጌል ልዩ ገጽታዎች

1. የሉቃስ ወንጌል ከወንጌላት ሁሉ የላቀ ሥነ ጽሑፋዊ ውበት አለው። መጽሐፉ የተጻፈው ጥልቅ የግሪክ ቋንቋ ክህሎት ባለው ሰው ነው። 2. ከሦስቱ ተመሳሳይ ወንጌላት መካከል ሉቃስ የተለየ ነው። የማቴዎስንና የማርቆስን አጠቃላይ ገጽታ ቢከተልም፣ ካቀረባቸው መረጃዎች መካከል 50 በመቶው ከማቴዎስና ማርቆስ የተለየ ነው። 3. ሉቃስ የታሪክ ባለሙያ እንደ መሆኑ መጠን፣ ሁኔታዎቹ የተፈጸሙበትን ትክክለኛ ጊዜ ይገልጻል። መጥምቁ ዮሐንስ

የሉቃስ ወንጌል ልዩ ገጽታዎች Read More »

የሉቃስ ወንጌል ዓላማ

አዲስ ኪዳን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ላይ በማተኮር፣ ስለ ማንነቱ፣ ስላስከተላቸው ለውጦች በሕይወታችን ውስጥ እንዴት ልናስከብረው እንደሚገባን ያብራራል። መልእክቶች ሁሉ እውነትን ተግባራዊ የሚያደርጉት ከኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት አንጻር ነው። ለመሆኑ የጥንት ክርስቲያኖች እምነታቸውንና ተግባራቸውን የመሠረቱት በምን ላይ ነበር? በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ላይ ነበር። እያንዳንዱ መልእክት ከግምት ውስጥ የሚያስገቡት ነገር አለ። ይኸውም እያንዳንዱ ክርስቲያን ስለ ኢየሱስ የሚናገሩትን

የሉቃስ ወንጌል ዓላማ Read More »

የሉቃስ ወንጌል የተጻፈበት ጊዜና ቦታ

የሉቃስ ወንጌል መቼ እንደ ተጻፈ ለመገመት የሌሎቹን ወንጌላትና የሐዋርያት ሥራን ቅደም ተከተል መገንዘብ አስፈላጊ ነው። ለምሳሌ፣ ሉቃስ የማርቆስን ወንጌል ከምንጮቹ እንደ አንዱ አድርጎ ተጠቅሞ ይሆን? የሐዋርያት ሥራ የተጻፈው መቼ ነው? በሐዋርያት ሥራ 1፡1 ላይ ሉቃስ ስለ መጀመሪያው መጽሐፉ ማለትም ስለ ሉቃስ ወንጌል ስለሚጠቅስ፣ የሐዋርያት ሥራ ከሉቃስ ወንጌል በኋላ እንደ ተጻፈ አያጠራጥርም። የሐዋርያት ሥራ የሚያበቃው ጳውሎስ

የሉቃስ ወንጌል የተጻፈበት ጊዜና ቦታ Read More »