1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች

ጳውሎስ አማኞች መሪዎቻቸውን እንዲያከብሩ ይመክራቸዋል (1ኛ ተሰ.5፡12-28)

ጳውሎስ በዚህ የማጠቃለያ ክፍል እያንዳንዱን የቤተ ክርስቲያን አባል የሚመለከቱትን ትእዛዛት ይዘረዝራል፡ ሀ) የቤተ ክርስቲያን አባላት መሪዎቻቸውን ማክበር ይኖርባቸዋል። እነዚህ መሪዎች ምእመናንን ለመምራት ጊዜያቸውን የሚሰዉና የክርስቲያኖችን መንፈሳዊ ፍላጎቶች የሚያሟሉ ናቸው። ለ) የቤተ ክርስቲያን መሪዎች እርስ በርሳቸው በሰላም መኖር አለባቸው። በእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ላይ ባላቸው የአመራር ኃላፊነት ክርስቲያኖች ተግተው እንዲሠሩ ሊያበረታቱና ራሳቸው ስደትን ለመጋፈጥና ለክርስቶስ ለመመስከር ቆራጦች […]

ጳውሎስ አማኞች መሪዎቻቸውን እንዲያከብሩ ይመክራቸዋል (1ኛ ተሰ.5፡12-28) Read More »

ጳውሎስ ክርስቶስ በድንገት በሚመለስበት ጊዜ የሞቱት አማኞች ምን እንደሚሆኑ ያብራራል (1ኛ ተሰ. 4፡13-5፡12)

ጢሞቴዎስ የተሰሎንቄ አማኞች ክርስቶስ በሚመለስበት ጊዜ የሞቱ አማኞች ምን እንደሚሆኑ ያነሷቸውን ጥያቄዎች ለጳውሎስ አቀረበ። ምንም እንኳ ጳውሎስ ተሰሎንቄን ከለቀቀ ከሦስት ወራት ባይበልጥም ቢያንስ አንድ ክርስቲያን በሞት የተለያቸው ይመስላል። ይህ ደግሞ የተሰሎንቄ አማኞች የሞቱ ክርስቲያኖች በተለይም ክርስቶስ በሚመለስበት ጊዜ ምን እንደሚሆኑ እንዲያስቡ አደረጋቸው። ለሁሉም ክርስቲያኖች ስለዚሁ ጉዳይ ጥርት ያለ አሳብ መያዙ በጣም አስፈላጊ ነው። ጳውሎስ ካስተማራቸው

ጳውሎስ ክርስቶስ በድንገት በሚመለስበት ጊዜ የሞቱት አማኞች ምን እንደሚሆኑ ያብራራል (1ኛ ተሰ. 4፡13-5፡12) Read More »

ጳውሎስ አማኞች የተቀደሰ፣ በፍቅር የተሞላና ሰላማዊ ሕይወት እንዲኖሩ ያበረታታቸዋል (1ኛ ተሰ. 4፡1-12)

ጢሞቴዎስ ለጳውሎስ ስለ ተሰሎንቄ አማኞች ጽናት በገለጸ ጊዜ፥ አንዳንድ አሳሳቢ ጉዳዮች እንደነበሩም መናገሩ አልቀረም። ጳውሎስ በዚህ የአንደኛ ተሰሎንቄ የመጨረሻ ክፍል ውስጥ እነዚህን ጉዳዮች ይዳስሳል። የጳውሎስ ቀዳማዊ ዓላማ አማኞች እግዚአብሔርን በሚያስደስት መልኩ እንዲኖሩ ነበር። እግዚአብሔር ባዳነን ጊዜ ከኃጢአት ብቻ ነፃ አላወጣንም። እርሱ እንቀደስ ዘንድ አድኖናል። የውይይት ጥያቄ፡- መቀደስ ማለት ምን ማለት ነው? ይህን ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ

ጳውሎስ አማኞች የተቀደሰ፣ በፍቅር የተሞላና ሰላማዊ ሕይወት እንዲኖሩ ያበረታታቸዋል (1ኛ ተሰ. 4፡1-12) Read More »

ጳውሎስ የጢሞቴዎስን ሪፖርት ከሰማ በኋላ የተሰማውን ደስታ ይገልጻል (1ኛ ተሰ. 3:1-13)

ጳውሎስ የተሰሎንቄን አማኞች አኗኗር ለማወቅ የወሰዳቸውን እርምጃዎች የፍቅሩ መግለጫ አድርጎ ይጠቅሳል። ከደረሰባቸው ስደት የተነሣ እምነታቸውን እንዳይተዉ ሰግቶ ነበር። ይህንንም ለማጣራት ጢሞቴዎስን ወደ ተሰሎንቄ ላከው። ጢሞቴዎስ ጳውሎስ ወደሚያገለግልባት የተሰሎንቄ ከተማ በተመለሰ ጊዜ፥ ከስደቱ ባሻገር የተሰሎንቄ አማኞች በክርስቶስ ማመናቸውን እንደቀጠሉና ታላቅ ፍቅርም እንደነበራቸው ለጳውሎስ አብራራ። ይህ ጳውሎስን እጅግ በማስደሰቱ እነርሱን ለማየት የነበረውን ጉጉት አናረው። ጳውሎስ ስደትን ተቋቁሞ

ጳውሎስ የጢሞቴዎስን ሪፖርት ከሰማ በኋላ የተሰማውን ደስታ ይገልጻል (1ኛ ተሰ. 3:1-13) Read More »

ጳውሎስ ለአማኞች ስለ ሕይወቱ ምላሌነት ያስታውሳቸዋል (1ኛ ተሰ. 2:1-20)

የጳውሎስ አገልግሎት በተሳሳተ ፍላጎት የተሞላ ነው የሚሉ ከሳሾች ሳይነሡ አልቀሩም። አንዳንድ ሰዎች ጳውሎስ ሰዎችን ለማስደሰት እንደሚሞክርና ገንዘብ የመሰብሰብ ዓላማ እንዳለው ለተሰሎንቄ አማኞች ሳይናገሩ አልቀሩም። በመሆኑም ጳውሎስ እነዚህ ክሶች እውነት ሊሆኑ የማይችሉባቸውን ምክንያቶች ይዘረዝራል። ሀ) ጳውሎስ በተሰሎንቄ ከመቆየት ያገኘው ነገር ቢኖር ተጨማሪ ቁሳቁስ ሳይሆን ስደትን ነበር። ከስደቱ ሥቃይ ባሻገር ጳውሎስ የወንጌል ስብከት አገልግሎቱን ቀጥሏል። ለ) በሚሰብኩበት

ጳውሎስ ለአማኞች ስለ ሕይወቱ ምላሌነት ያስታውሳቸዋል (1ኛ ተሰ. 2:1-20) Read More »

ጳውሎስ ስለ ተሰሎንቄ አማኞች እግዚአብሔርን ያመሰግናል (1ኛ ተሰ. 1:1-10)

ገብረ እግዚአብሔር በክርስቶስ ካመነ ብዙም ሳይቆይ እናቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። እናቱም እንደ እርሱ አዲስ አማኝ ነበረች። ገብረ እግዚአብሔር እናቱን ከልቡ ይወዳት ስለነበር ልቡ በኀዘን ቆሰለ። አሁን ምን ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ይሆን ያለችው ሲል አሰበ። በሥቃይ ርዶ ድምፁን ጮክ አድርጎ አለቀሰ። ሌላ ክርስቲያን ሲያለቅስ ሰምቶት ክርስቲያኖች ሊያለቅሱ አይገባም ሲል በብርቱ ገሠጸው። የገብረ እግዚአብሔር ዘመዶች በአብዛኛው

ጳውሎስ ስለ ተሰሎንቄ አማኞች እግዚአብሔርን ያመሰግናል (1ኛ ተሰ. 1:1-10) Read More »

የ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መልእክቶች ዓላማ፣ ልዩ ባሕሪያት እና አስተዋጽኦ

የ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መልእክቶች ዓላማ የመጀመሪያው ዓላማ፡- ጳውሎስ ከተሰሎንቄ ከተማ ብዙም ሳይቆይ በፍጥነት መውጣት ስለነበረበት አማኞቹን በእግዚአብሔር ቃል ለማስታጠቅ የሚበቃ ጊዜ አላገኘም ነበር። ከዚህም በላይ የተሰሎንቄ ቤተ ክርስቲያን በከፍተኛ ስደት ውስጥ ነበረች። በመሆኑም ጳውሎስ እነዚህ ጥቂት አማኞች ለክርስቶስ ታማኞች እንዲሆኑና በዚህ በጥላቻ በተሞላው አካባቢ እግዚአብሔር እንደሚፈልገው እንዴት ሊኖሩ እንደሚገባቸው ለማስተማር ፈለገ። ሁለተኛ ዓላማ፡- የተሰሎንቄ አማኞች

የ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መልእክቶች ዓላማ፣ ልዩ ባሕሪያት እና አስተዋጽኦ Read More »

የ1ኛና የ2ኛ ተሰሎንቄ ማን ጻፈው፣ ለማን ተጻፈ፣ የትና መቼ ተጻፈ

የ1ኛና የ2ኛ ተሰሎንቄ ጸሐፊ የውይይት ጥያቄ፡- 1ኛ ተሰ. 1፡1 እና 2ኛ ተሰ. 1፡1 አንብብ። ሀ) የእነዚህ ሁለት መጻሕፍት ጸሐፊ ማን ነው። ለ) እነዚህ መግቢያዎች የሚመሳሰሉት እንዴት ነው? ሐ) በዚህ ክፍልና በገላ. 1፡1 ጸሐፊው ራሱን የገለጸባቸው መንገዶች የሚለያዩት እንዴት ነው? መ) እነዚህ መልእክቶች የተጻፉት ለማን ነበር? የመልእክቶቹ ተቀባዮች የተገለጹት እንዴት ነው? የ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መልእክቶች የሚጀምሩት

የ1ኛና የ2ኛ ተሰሎንቄ ማን ጻፈው፣ ለማን ተጻፈ፣ የትና መቼ ተጻፈ Read More »

የ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መግቢያ

አንዲት ነቢይ፥ «ክርስቶስ የዛሬ ዓመት ይመጣል። ስለሆነም ሁላችሁም በፍጥነት መጋባት ይኖርባችኋል። ሥራ ያላችሁ ደግሞ ሥራችሁን ለቅቃችሁ ባላችሁ ገንዘብ ራሳችሁን ማስደሰት አለባችሁ። እህል መዝራቱ አስፈላጊ አይሆንም። ባጨዳው ጊዜ እዚህ አትኖሩምና» ስትል ተነበየች። ብዙ ሰዎች አስተዋይ ሽማግሌዎች የሰነዘሩትን ማስጠንቀቂያ ችላ ብለው ምክሯን ተቀበሉ። ወጣቶቹ ስለ ነገ ሳያስቡ የትዳር ጓደኞችን መረጡ። ወዲያውም እነዚህ ልጃገረዶች አረገዙ። ሰዎች ሥራቸውን ለቅቀው

የ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ መግቢያ Read More »