የሕይወት እንጀራ

2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች

2ኛ ቆሮ. 9፡6-15

ጥያቄ 7. በቁጥር 6 ላይ ሐዋርያው መስጠትን ከምን ጋር ያመሳስላል?  ጥያቄ 8. በቁጥር 10 መሠረት መስጠት የማይችል ክርስቲያን ሊኖር ይገባዋል?  ጥያቄ 9. በቁጥር 12 መሠረት የመስጠት መንፈሳዊ ውጤት ምንድነው?  ጥያቄ 10. የመስጠት አርአያችን ማነው? (ቁጥር 15)  ቁጥር 6፡- መስጠት እንደመዝራት ይመስላል። በግብርና ዓለም በጥቂት የዘራና በብዙ የዘራ እኩል አያጭድም። እንዲሁም በመስጠት ለጋስነት ብዙ በረከትን ያስገኛል፤ […]

2ኛ ቆሮ. 9፡6-15 Read More »

2ኛ ቆሮ. 9፡1-5

ጥያቄ 5. ቁጥር 4ን አብራራ፤ በተለይ ያልተዘጋጃችሁም ሆናችሁ ቢያገኗችሁ … እኛ እንዳናፍር ይሁን» ያለውን አብራሪ።  ከቁጥር 1-2:- ሐዋርያው ጳውሎስ ከአንድ ዓመት በፊት የቆሮንቶስ ሰዎች ይህን መዋጮ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል ብሎ ለመቄዶንያ ሰዎች ተናግሮ ነበር። የቆሮንቶስ ሰዎች በውስጣቸው በተነሣው ጭቅጭቅ ምክንያት የሰጡትን ተስፋ ገና ሥራ ላይ ስላላዋሉት ጳውሎስ ስለእነርሱ ለመቄዶንያ ሰዎች በተናገረው ማፈር አልፈለገም። ሆኖም ይህ ከአንድ

2ኛ ቆሮ. 9፡1-5 Read More »

2ኛ ቆሮ. 8:16-24

ጥያቄ 1. በቁጥር 19 ላይ «በምናገለግለው በዚህ ቸር ሥራ ከእኛ ጋር እንዲጓደድ በአብያተ ክርስቲያናት ተመረጠ» ሲል ቸር ሥራ ያለው ምኑን ነው? (መጓደድ ማለት መጓዝ ማለት ነው)።  ጥያቄ 2. ቁጥር 20 እና 21ን በሰፊው አብራራ።  ከቁጥር 16-17:- ለኢየሩሳሌም ምእመናን ከቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን የተሰበሰበውን ገንዘብ ወደ ኢየሩሳሌም ለማድረስ መሪ ሆና እንዲያገላገል ቲቶ ተመረጠ። ቲቶም በሐዋርያው ስለታዘዘ ብቻ

2ኛ ቆሮ. 8:16-24 Read More »

2ኛ ቆሮ. 8:8-15

ጥያቄ 14. “በሌሎች ትጋት በኩል የፍቅራችሁን እውነተኛነት ደግሞ ልመረምር እላለሁ” ሲል ምን ማለቱ እንደሆነ አብራራ።  ጥያቄ 15. የክርስትና ልግሥና መመርያ ምንድነው? (ቁጥር 9)  ጥያቄ 16. ቁጥር 15ን የጠቀሰው ከየት ነው? ከየት እንደተጠቀሰ ካመለክትህ በኋላ ታሪኩን ሰፋ አድርገህ አብራራ ። ቁጥር 8:- ሐዋርያው ማዘዝ ሲችል ግን በፍቅር ይለምናቸዋል። የእግዚአብሔር ሥራ በፍቅር እንጂ በግድ መደረገ የለበትም፡፡ በሌሎች

2ኛ ቆሮ. 8:8-15 Read More »

2ኛ ቆሮ. 8፡1-7

በ2ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 8 እና 9 ሐዋርያው ስለመስጠት በሰፊው ያስተምራል። በኢየሩሳሌም የነበሩት ክርስቲያኖች ከአይሁዳውያን በደረሰባቸው ስደት ምክንያት ብዙ ችግር ነበረባቸው። የችግራቸው መንሥኤ ያላቸውን ማካፈላቸው አልበረም፤ (የሐዋ.4:32-37)። ግን ይህ ያላቸውን ማካፈላቸው በስደት ምክንያት የደረሰባቸውን ችግር ለመቋቋም የወሰዱት እርምጃ ነበር እንጂ!  ክርስትናን ላካፈሏቸው አይሁዳውያን የአሕዛብ ዕርዳታ በክርስቶስ ያላቸውን አንድነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ሐዋርያው ጳውሎስ ተገንዝቦት ነበር። ስለዚህ ለዚህ

2ኛ ቆሮ. 8፡1-7 Read More »

2ኛ ቆሮ. 7:5-16

ጥያቄ 5. በቁጥር 5 ላይ “በውስጥ ፍርሃት” ሲል ምን ዓይነት ፍርሃት ነበረ?  ጥያቄ 6. ከቁጥር 7-13 ባለው ክፍል ውስጥ የተጠቀሰውን በአጭሩ አብራራ።  በቁጥር 5 ላይ ያለው ሃሳብ 2:13 ላይ የተወውን ሃሳብ እንደገና ይጀምራል። በ2:13 ላይ «ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ እረፍት አልነበረውም። ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ»። አሁን ደግሞ ያንን ሃሳብ እንደገና አንሥቶ በ7:5

2ኛ ቆሮ. 7:5-16 Read More »

2ኛ ቆሮ. 7:2-4

ጥያቄ 1. በቁጥር 2 ላይ “በልባችሁ ስፍራ አስፋልን” ሲል ይህን መሰል ንግግር ከዚህ በፊት የት ተጽፎ እናገኛለን?  ጥያቄ 2. በቁጥር 3 “ለኩነኔ አልልም” ማለቱ ምን ማለቱ ነው? በቁጥር 2 ላይ ከዚህ በፊት በ6፡12 የተናገረውን በመድገም “በልባችሁ ሥፍራ አስፉልን” ይላል። ልባቸውን ለሐዋርያው የማያሰፉበት ምንም ምክንያት የለም፤ ምክንያቱም በሐዋርያው በኩል ምንም በደል አልነበረምና! በተለያዩ ሦስት ቃላት ይህንን

2ኛ ቆሮ. 7:2-4 Read More »

2ኛ ቆሮ. 6፡14-7:1

ጥያቄ 22. ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ ማለት ምን ማለት ነው?  ጥያቄ 23. በቁጥር 17 እና 18 ላይ «ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ» ሲል ምን ማለቱ ነው?  ቁጥር 14:- ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ የሚለው ስለ ጋብቻ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ ከማያምኑ ጋር ያለንን ግንኙነት ይመለከታል። ለምሳሌ ከዚህ በፊት ሐዋርያው ለቆሮንቶስ ምእመናን ከማያምኑ ጋር በሚከተሉት መንገዶች እንዳይጠመዱ

2ኛ ቆሮ. 6፡14-7:1 Read More »

2ኛ ቆሮ. 6፡1-13

ጥያቄ 13. በቁጥር 1 ላይ «አብረን እየሠራን» ሲል አብረን ያለው ማንን ሲጨምር ነው?  ጥያቄ 14. በቁጥር 1 ላይ እንደተጻፈው የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ መቀበል ማለት ምን ማለት ነው?  ጥያቄ 15. ቁጥር 3ን አብራራ።  ጥያቄ 16. በቁጥር 4 ማማጠን ምን ማለት ነው?  ጥያቄ 17. ቁጥር 12ን አብራራ።  በቁጥር 1 ላይ አብረን እየሠራን ያለው ሐዋርያው ከእግዚአብሔር ጋር ይሠራል

2ኛ ቆሮ. 6፡1-13 Read More »

2ኛ ቆሮ. 5:16-21

ጥያቄ 7. ክርስቶስን በሥጋ ማወቅ ማለት ምን ማለት ነው?  ጥያቄ 8. በቁጥር 17 ላይ «ሁሉም አዲስ ሆኖአል» ማለት ምን ማለት ነው?  ጥያቄ 9. በቁጥር 19 ላይ «እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና» ሲል ምን ማለቱ ነው?  ቁጥር 16፡- «ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም» ሲል ሥጋ ማለቱ በተፈጥሮ ሰው አስተሳሰብ መንገድ ማለቱ ነው። ለምሳሌ በዘር

2ኛ ቆሮ. 5:16-21 Read More »