ምዕራፍ 6 – ሕብረት

ጸሎት

‹‹አባት ሆይ በዘላለማዊው ቤተሰዎችህ ውስጥ ሰለጨመርከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ በዚህ ቤተሰብ ውስጥ እንዴት በሰመረ ሁኔታ መኖር እንዳለብኝ፣ እንዴት ወንድሞቼንና እህቶቼን መርዳት እንዳለብኝ እና እንዴት በእነሱ መረዳት እንዳለብኝ እንዳውቅ እርዳኝ፡፡ አሜን፡፡››

ስለ ሕብረት ጠቀሜታ ማወቅ ለምን ያስፈልጋል?

ወደ ሰሜን ካሊፎርኒያ ሄደህ በተለያዩ ፓርኮች ውስጥ ያሉትን አስደናቂ የሬድውድ ዛፎችን ጎብኝተህ ታውቃለህ? እነዚህ ዛፎች በምድራችን ላይ ካሉ ረጃጅምና ግዙፍ ዛፎች መካከሉ የሚመደቡ ናቸው፡፡ በርካቶቹ ቁመታቸው ከ 350 ጫማ በላይ ሲሆኑ እድሚያቸው ደግሞ እስከ 4000 አመታት ያዘልቃል፡፡ በዝምታ ቀናት፣ በእነዚህ እጅብ ባሉ ዛፎች መካከል መገኘት በጥንታዊያን ቅዱሳት ካቴድራሎች ውስጥ የመገኘት ያህል ይሰማል፡፡ አንዳንድ ጊዜ እነዚህ ዛፎች አፍ አውጥተው ከአብርሃም፣ ይስሃቅና ያዕቆብ ዘመን ጀምሮ መኖር ምን እንደሚመስል እንዲነግሩህ መጠየቅ ያሰኝሃል፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የጸሃይ ወራትን አሳልፎ አሁንም ድረስ በጥንካሬ፣ በብቃትና፣ በፅናት ግዙፍነትን ጠብቆ መዝለቅ ምንኛ አስደናቂ ነገር ይሆን!

አሁን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ፡- ለመሆኑ የሬድውድ ዛፍ ብቻውን በእርሻ መካከል በቅሎ አይተህ ታውቃለህ? ምናልባት አካበቢው የነበሩትን መሰል ጓደኞቹን ሰው ጨፍጭፎ እርሱ ብቻ ቀርቶ አግኝተኸው ከላሆነ በቀር መልሱ፣ ‹‹ፈፅሞ!›› የሚል ይሆናል፡፡ በዚህ ሁኔታ ብቻውን የተገኘ የሬድውድ ዛፍ ቢኖርም እንኳ እድሜው ረጅም አይሆንም፡፡ እግዚአብሔር የእነዚህን ዛፎች ድብቅ ታሪክ ስለሚያውቅ በአጀብ (በሕብረት) ብቻ እንዲገኙ ወስኗል፡፡ የእነዚህ ዛፎች ደካማ ጎን ሥሮቻቸው አጫጭሮች መሆናቸው ነው፡፡

የሬድ ውድ ዛፎች እንደሌሎች በርካታ ዛፎች ስሮቻቸው ወደ ምድር ውስጥ የዘለቀና የጠለቀ ሳይሆን ድንጋያማ በሆነው አካባቢያቸው የሚዘንበውን ዝናብ በበቂ ሁኔታ ለመቀራመት ይረዳቸው ዘንድ ስሮቻቸው ወደታች ጥልቅ ከመሆን ይልቅ ወደጎን ሰፊ ቦታን በመሸፈን ይበቅላሉ፡፡ እነዚህ ዛፎች በከባድ ነፋስ ተገፍተው እንዳይወድቁ ስሮቸው ምድር ለምድር ለረጅም ርቀት እርስ በእርሳቸው የተቆላለፉ ናቸው፡፡ በአካባቢያቸው ጠንካራ ንፋስ በሚነፍስበት ወቅት በስሮቻቸው እርስ በእርስ የተያያዙ ስለሆኑ ለንፋሱ አይበገሩም!

ይህ ምሳሌ የክርስቲያኑ ማህበረሰብ እንዴት መኖር እንዳለበት አስደናቂ መልዕክት ያስተላልፋል፡፡ በዚህ አለም ውስጥ መኖር በየዕለቱ አስቸጋሪ እየሆነ ነው፡፡ ይህንን አስቸጋሪ ሁኔታ ‹‹ብቻውን›› ለመወጣት የሚሞክር ክርስቲያን ለአደጋው ተጋላጭ ነው፡፡ ብቻውን ሊቋቋመው ከሚችለው በላይ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ብዙ ሳይቆይ ያጋጥመዋልም፡፡ በአስቸጋሪ ወቅቶቻችን ወቅት ‹‹ስሮቻችንን›› አቆላልፈን አንዳችን በአንዳችን ሕይወት ውስጥ በመሳተፍ የመኖር አስፈላጊነትን ከዚህ እንማራለን። የክርስቲያኖች ሕብረት ፍሬ ነገር ይሄ ነው፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ በመመሪያዎች፣ በሕጎች እና ትዕዛዛት የተሞላ ነው፡፡ በእውኑ እግዚአብሔር ሕይወታችንን እስከሞት ድረስ ጠፍንጎ የሚገዛ የደስታችን ጠር አምላክ ነውን? ፈፅሞ፡፡ እርሱ ለሕይወታችን የትኞቹ ነገሮች መልካም፣ የትኞቹ ደግሞ አጥፊዎቻችን እንደሆኑ እንድንገነዘብ በመርዳት የሚንከባከበን ድንቅ አባት እንጂ፡፡ የሕጎቹም አላማ ይኸው ነበር፡፡

እንዴት ነው ታዲያ እነዚህን ሁሉ ህጎች ማስታወስ የሚቻለው? እንዴትስ ነው መታዘዝ የሚቻለው? ኢየሱስ ይህንን ጉዳይ ቀሊል አድርጎልናል፡፡ በሙሉ ልባችን ሁለት ሕጎችን ብቻ ብንታዘዝ የተቀሩትን በሞላ ልንታዘዛቸው እንደምንችል ነግሮናል፡፡

ማቴዎስ 22፡37-40 ካነበብክ በኃላ እነዚህን ሁለት ህጎች ፃፍ፡-

  1. __________
  2. __________

እስቲ ጥቂት ጥያቄዎች ራሳችንን እንጠይቅ። መጪውን የዘላለማዊ ሕይወታችንን ዘመን ከእርሱ ጋር በመንግስቱ ስለምናሳልፍ፣ አሁን በሕይወታችን ውስጥ ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች እርሱ ከሚሰጣቸው ነገሮች ጋር መግጠም የለባቸውምን? እኛስ ለተፈጠርንለት አላማ መኖር የለብንምን? እርሱ ዋጋ በሚሰጣቸው ነገሮች ላይ እኛም ቅድሚያ በመስጠት የተካንን መሆንስ የለብንምን?

ለእነዚህ ጥያቄዎች ምልሽህ አወንታዊ ከሆነ፣ እንግዳው እግዚአብሔርንና አብረውህ ያሉትን (ክርስቲኖችና ክርስቲያን ያልሆኑትን) በሞላ በመውደድ የተካንክ ልትሆን ይገባሃል፡፡ የዚህ ጥናት አላማ ክርስቲያን ወንድሞችህንና እህቶችህን በማፍቀር እንድታድግ መረዳት ሲሆን ምዕራፍ 9 ላይ ‹‹ምስክርነት›› በሚለው ርዕስ ስር ደግሞ ክርስቶስን ያላወቁትን እንዴት በዚህ ፍቅር መቅረብ እንደምትችል የሚያግዝህ መረጃ ይቀርብልሃል፡፡

የፍቅርን ብያኔን እንመልከት፡-

‹‹ፍቅር›› ለሚለው ቃል ሦስት የግሪክ አቻ ቃላት አሉ፡-

ኤሮስ፡- ለማግኘት የሚወድ ራስወዳድ ፍቅር፤ ወሲባዊ ፍቅር፡፡

ፊሊዬ፡- ወንድማዊ ፍቅር፤ በደምሳሳው የሆነ ፍቅር

አጋፔ፡- እግዚአብሔራዊ፣ ራስወዳድ ያልሆነ ፍቅር – ክርስቲያኖች ሊኖራቸው የሚገባ ፍቅር

‹‹እውነተኛዎቹ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ብዙ የሚያውቁቱ ሳይሆኑ ብዙ የሚያፈቅሩቱ ናቸው፡፡›› -ፍሬድሪክ ስፓንሄይም

በክርስቲያኖች ሕብረት ውስጥ የፍቅር የበላይነት

  1. በዮሐንስ 13፡34-35 መሠረት የኢየሱስ ተከታዮች እውነተኛ የእርሱ ደቀ መዛሙርት መሆናቸው የሚታወቅበት መታወቂያ ምንድን ነው?
  2. እርሱ እንደ ወደደን፣ እርስ በእርሳችን መዋደድ እንዳለብን ኢየሱስ ተናግሯል፡፡ ይህን ሲል ምን ማለቱ ይመስልሃል? ኢየሱስ ለእኛ ያለውን ፍቅር ከገለጠበት መንገዶች መካከል ጥቂቶቹ ግለጽ?

ከዚህ በታች በቀረቡት ጥቅሶች ውስጥ ስለ ክርስቲያን ፍቅር ያስተዋልከውን ቁም ነገር ፃፍ፡-

  1. ‹‹ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፣ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።›› -1ቆሮንቶስ 13፡2
  2. ‹‹ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ።››-1ጴጥሮስ 4፡8 
  3. ‹‹ልጆቼ ሆይ፣ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት አንዋደድ።››-1ዮሐንስ 3፡18 
  4. ‹‹ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?››-1ዮሐንስ 4፡20

‹‹ሌላውን ማዕከል›› ያደረገ የክርስቲያኖች ሕብረት

ከእርስ በእርስ ግንኙነት ጋር በተገናኘ ክርስቲያኖች እንዲያደርጉ የሚጠበቅባቸውን ነገሮች ለመረዳት፣ ከርዕሱ ጋር በተያያዘ ‹‹እርስ በርሳችሁ›› የሚሉ ሃረጋትን ያካተቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን መመርመር ያስፈልጋል፡፡ በአወንታዊ መንገድ በአዲስ ኪዳን ውስጥ የተገለጹ እንደ እነዚህ አይነት 31 ጥቅሶች እናገኛለን፡፡ ከዚህ በታች ለአብነት ስድስቱ ቀርበዋል፡፡ እያንዳንዱን በመጽሐፍ ቅዱስህ ላይ ካነበብክ በኃላ ምን እንድናደርግ እንደሚያመለክቱን ግለጽ፡፡

  1. ዮሐንስ 15፡12______________
  2. ሮሜ 12፡10________________
  3. ሮሜ 12፡10________________
  4. ኤፌሶን 4፡2________________
  5. ኤፌሶን 4፡32_______________
  6. ዕብራዊያን 10፡25___________
  7. ከላይ ከተገለፁት የ ‹‹እርስ በርሳችሁ›› ጥቅሶች መካከል ለማድረግ የሚያስቸግርህ የቱ ነው? ለምን?
  8. ይህ ጉዳይ ወደፊት በሕይወትህ ውስጥ አስቸጋሪ ሆኖ እንዳይቀጥል ምን ለማድረግ አቅደሀል?

‹‹እግዚአብሔር እኛን ለመስራት ሁሉንም ነገር ይጠቀማል፡፡ ከሁሉ በላይ ግን አንዳንችንን በሌላው በመጠቀም ያበጀናል፡፡ እያንዳንዱ ሰው ለሌላው መስታዋት ነው፤ ወይም የክርስቶስን ሕይወት በ ‹‹መሸከም›› ለሌላው የሚያሳይ ነው፡፡ ክርስቶስን ለሌላው ሰው ሊያስተዋውቁት የሚችሉት የሚያቁቱ ሰዎች ናቸው፡፡ ለዚህ ነው የክርስቲያኖች እርስ በእርስ መተያየት አስፈላጊ የሚሆነው፡፡›› -ሲ.ኤስ. ሊዊስ

‹‹እውነተኛ ሕብረት›› ምን ማሟላት ይገባዋል?

በሚከተሉት ጥቅሶች መሠረት ክርስቲያኖች ሕብረት ሲያደርጉ ምን መፈጠር አለበት?

  1. ‹‹ብረት ብረትን ይስለዋል፣ ሰውም ባልንጀራውን ይስላል።››-ምሳሌ 27፡17 
  2. ‹‹አንዱም አንዱን ቢያሸንፍ ሁለቱ በፊቱ ይቆማሉ፤ በሦስትም የተገመደ ገመድ ፈጥኖ አይበጠስም።››-መክብብ 4፡12 
  3. ‹‹በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።››-የሐዋሪያት ሥራ 2፡42 
  4. ‹‹በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።››-ሮሜ 15፡1 
  5. ‹‹በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤››-ኤፌሶን 5፡19 
  6. ‹‹ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤››-ዕብራዊያን 10፡24 

ከላይ የተገለፁት ድርጊቶች ሁሉ ክርስቲያኖች ሕብረት ባደረጉ ቁጥር እንዲኖሩ አንጠብቅም፣ ነገር ግን የተለመዱና አዘውትረው የሚስተዋሉ መሆን አለባቸው፡፡ በዚህ መሰረት፣ ከዚህ በታች የቀረቡት ሁኔታዎች እውነተኛ የክርስቲያኖችን ሕብረት ይገልፅ ይሆን?

  1. ሦስት ክርስቲያኖች ለምሳ ተገናኝተው ስለ እግር ኳስ ቡድናቸው የወደፊት እጣ ፈንታ፣ ስለ ተሻሻሉ ኮምፒውተሮች እና ስለ አየሩ ሁኔታ ቢያወሩ፡፡
    • አዎ
    • ፈፅሞ
  2. ሦስት ሴቶች ከምሳ በኃላ ተገናኝተው ካርታ እየተጫወቱና ሻይ እየጠጡ ስለዘመናዊና ስለተሻሻሉ የልብስ ዲዛይኖች ጉዳይ ቢጨዋወቱ፡፡
    • አዎ
    • ፈፅሞ
  3. ሁለት ክርስቲያን ጥንዶች በሚያምር የበጋ ወር ተገናኝተው ስለ ስፖርት ውድድር ቢያወጉ፡፡
    • አዎ
    • ፈፅሞ

በሁሉም አንፃር ‹‹ፈፅሞ›› የሚል ከመረጥክ፣ እንዚህን ሁኔታዎች አበረታች ወደ ሆነ እውነተኛ የክርስቲያኖች ሕብረት ለመቀየር በእያንዳንዱን ዐረፍተ ነገሮች ላይ ምን መጨመር አለበት ትላልህ?

  1. ______________
  2. ______________
  3. ______________

ማህበራዊ ግንኙነታቸው፣ ‹‹እውነተኛ›› የክርስቲያን ሕብረትን ሃሳብ ካላሟላ በቀር፣ ክርስቲኖች እርስ በእርስ ተገናኝተው መልካም ጊዜ ማሳለፍ አይችሉምን?

ሕብረት መደረግ ያለበት የት ነው?

ለዚህ ጥያቄ ወደ አእምሮህ የሚመጣው የመጀመሪያ ምላሽ ‹ቤተ ክርስቲያን› የሚለው ሊሆን ይችላል! ይህ ስፍራ በእርግጥ እርስ በእርስ ለመበረታታትና በሌሎች የክርስቶስ አካል ብልቶች ለመጠቀም፣ የእግዚአብሔርን ቃል ለመመገብ፣ በህብረት እግዚአብሔርን ለማምለክ፣ በአንድነት ለመጸለይ፣ እና እንደ ሬድውድ ዛፎቹ ‹‹እርስ በእርስ እንያያዝ›› ዘንድ በጥልቀት ለመተዋወቅ አማኞች ዘወትር የምንገናኝበት ልዩ ስፍራ ነው፡፡ ‹‹ቤተ ክርስቲያን›› የሚለው ቃል ሁል ጊዜ የአማኞች ስብስብን የሚያመለክት ሲሆን አባላቱና የሚገናኙበት ስፍራ ግን የተለያየ ነው፡፡ ከዚህ በታች የቀረቡትን ጥያቄዎች መልስ፡፡ የሚከተሊትን ጥቅሶች ካነበብክ በኋላ የተስመሩባቸው ሃረጋት የሚገልጡትን ሃሳብ አሰላስል።

  1. ‹‹በቆሮንቶስ ላለች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ለተቀደሱት፣ የእነርሱና የእኛ ጌታ የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በየስፍራው ከሚጠሩት ሁሉ ጋር ቅዱሳን ለመሆን ለተጠሩት፤››– 1ቆሮንቶስ 1፡2
  1. ‹‹የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። አቂላና ጵርስቅላ በቤታቸው ካለች ቤተ ክርስቲያን ጋር በጌታ እጅግ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።››-1ቆሮንቶስ 16፡19
  1. ‹‹(ጳውሎስ ስለራሱ ሲናገር እንዲህ ይላል) እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፣ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤››-1ቆሮንቶስ 15፡9

‹‹የምንመስለው አካባቢያችንን ነው፡፡ ጓደኞችህን አሳየኝና ከአስር አመት በኋላ የምትሆነውን አሳይሀለው፡፡›› -ኸርብ ኢቫንስ።  በተጨማሪ 1ቆሮንቶስ 15፡33 ተመልከት

ማብራሪያ፡- ቤተ ክርስቲያን – በነጭ ቀለም የተቀባች፣ ጉልላት ያላት እና በጉልህ በሚታይ አንድ ቦታ ላይ መስቀል የተከለች ቋሚ ሕንፃ መሆን አለባትን? በአሁኑ ሰአት ያሉ ቤተ ክርስቲያናት ብዙ ጊዜ ይህን ይመስላሉ፤ ከክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ በኋላ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ግን በሰዎች መኖሪያ ቤት ውስጥ፣ በአይሁድ ምኩራቦች ውስጥ እና አንዳንዴ ደግሞ በገላጣ ስፍራ ትሰባሰብ ነበር፡፡ በቤተ ክርስቲያን የስደት ዘመናት ደግሞ በዋሻዎች ውስጥ፣ በዛፎች ስርና በመቃብር ስፍራዎች ሳይቀር ይሰበሰቡ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎቶች በተሰሩ በተዋቡ ሕንፃዎች ውስጥ የመገናኘት እድል ገጥሞናል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በተለየ መንገድ ቤተ ክርስቲያን በቤቶች፣ በትምህርት ቤቶች፣ በመጋዘኖች በእስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በመስሪያ ቤቶች፣ በጂምናዚየሞች እና ሬስቶራንቶች ውስጥ ልትገናኝ ትችላለች፡፡ ዛሬም ክርስቲያኖች በስደት ውስጥ ባሉባቸው ስፍራዎች፣ ቤተ ክርስቲያን ከአሳዳጆቿ አይን በምትሰወርበት ማናቸውም ስፍራዎች ትሰባሰባለች፡፡ አስተውል፡- ቤተ ክርስቲያን ሕዝቦቹ እነጂ ሕንፃው አይደለም!

ሌሎች የሕብረት አውዶች

ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለሆነው ሕብረት አጥቢያ አቢያተ ክርስቲያናት መሰረታዊውን ሃሳብ የሚሰጡን ቢሆንም፣ (አንተም ደግሞ በእነዚህ ስፍራዎች ለመጠቀም ስትል ንቁ ተሳትፎ የሚጠበቅብህ ቢሆንም)፣ ሕብረት በተለያዩ ስፍራዎች ሊደረግ ይችላል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ልትሰባሰብ የሚገባት የግድ አራት ግድግዳ ባለበት ስፍራ ወይም በተወሰነ ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ ከዚህ በታች በቀረበው ባዶ ቦታ ከተለመደው የቤተ ክርስቲያን ስፍራ በሰባሰቢያ ስፍራ ውጪ፣ የተሳካ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሕብረት ልታደርግባቸው የምትችልባቸውን አራት ስፍራዎች ፃፍ፡፡

  1. ___________________
  2. ___________________
  3. ___________________
  4. ___________________

የበሰለ የሕብረት አድራጊ ሰው ባሕሪያት

መጽሐፍ ቅዱሳችን መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆነውን ሕብረት በብስለት በተረዳ ሰው ውስጥ የሚስተዋሉ ቢያንስ ሃያ ድስት ባሕሪያትን ይገልፅልናል፡፡ እነዚህ ባሕሪያት በእሁድ ማለዳ ብቻ ሳይሆን ሁል ጊዜ አንድ ግለሰብ ከሌሎች ጋር የሚያደርገውን ሕብረት የሚገልጹ ባህሪያት ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡

የሚከተሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ከእነዚህ 26 መካከል አስሩን ባሕሪያት ይገልጻሉ፡፡ አንዳንዶቹ ስፍራ ላይ ጥቅሶቹ የቀረቡ ሲሆን ሌሎቹን ግን ራስህ ከመጽሐፍ ቅዱስህ ላይ ፈልገህ ማንበብ ይጠበቅብሃል፡፡ እያንዳንዱን ጥቅሶች ካነበብክ በኃላ በጥቅሶቹ ውስጥ ያገኘኸውን የበሰለ ሕብረት አድራጊ ባሕሪይ (ባሕሪያት) ፃፍ፡፡

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ

  1. ‹‹እንግዲያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል።›› ሮሜ 1419   
  2. ‹‹የጌታምባሪያ ለሰው ሁሉ ገር ለማስተማርም የሚበቃ ለትዕግሥትም የሚጸና ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም።›› -2ጢሞቴዎስ 224
  3. ‹‹በወንድማማችመዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤›› ሮሜ 1210
  4. ‹‹ለጸሎትምበቆማችሁ ጊዜ፣ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ፣ በማንም ላይ አንዳች ቢኖርባችሁ ይቅር በሉት።›› ማርቆስ 1125 1ጴጥሮስ 55-6
  5. ‹‹ስለዚህ፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፣ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤››ያዕቆብ 119-20ማቴዎስ 543-48
  6. ‹‹ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።›› ሮሜ 1213
  7. ‹‹ደስከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፣ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።›› ሮሜ 1215  

በሕብረት ውስጥ የሚከሰቱ ችግሮችን መፍታት

አንድ ሰው እንዲህ አለ፡ ‹‹ፍፁም ቤተ ክርስቲያን ካጋጠመህ፣ ሕብረት አታድርግ- ታበላሸዋለህና!›› ቤተ ክርስቲያንን የመሠረታት ኢየሱስ ክርስቶስ ቢሆንም፣ እያንዳንዱ ቤተ ክርስቲያን በቀላሉ ሊሳሳቱ በሚችሉ ሰዎች የተሞላ መሆኑም መዘንጋት የለብህም፡፡ እነዚህ ሰዎች እንደ ክርስቲያን በእግዚአብሔር የተወደዱ፣ ምህረት ያገኙ፣ ከጠላት እጅ የተዋጁ እና ወደ መንግስተ ሰማይ ጉዞ የጀመሩ ቢሆኑም ሊስቱ የሚችሉ ሰዎች ደግሞ ናቸው፡፡ ከክርስቶስ ጋር በዘላለማዊ የክብር መንግስት ውስጥ አብረን እስክንሆን ድረስ ማናችንም ብንሆን ፍፁም ልንሆን አንችልም፡፡ ይህ አንተንም ያካትታል!

በዚህ ጉዞ መካከል አልፎ አልፎ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር የሚከሰቱ ችግሮችን ልትጠብቅ ይገባል፡፡ ኢየሱስ በማቴዎስ 9፡12 ላይ እንደ ገለጸልን፣ ‹‹ሕመምተኞች እንጂ ባለ ጤናዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም፡፡›› ከታላቁ ሃኪም ውጪ ጤነኛ መሆናቸው የሚሰማቸው ሰዎች ወደ እርሱ አይመጡም፡፡ የሚያስፈልጋቸውን እና ጉድለታቸውን የተረዱ ግን አንድ በሽተኛ እርዳታ ፍለጋ ወደ ሃኪም እንደሚሄድ ሁሉ እርሱን ይፈልጉታል! ስለዚህ ያለህበት ቤተ ክርስቲያን የታመሙ ሰዎች ያሉባት እንደሆነች ልታውቅ ይገባል! ምቾት የማይሰጥ ነጥብ ቢመስልም ጉዳዩን ልትረዳ ይገባል፡፡ ክርስቲያኖች ፍፁማን አይደሉም፤ ነገር ግን እየተሻሉ ለማደግ ጉዞ ጀምረዋል፤ (ቢያንስ ወደ ሆስፒታሉ መጥተዋል!)፡፡ ራስህን ከሌሎች ክርስቲኖች ጋር በማይመች ሁኔታ ውስጥ ስታገኝ አንተንም ሆነ እነሱን በሚጠቅም መልክ ችግሩን ለመፍታት የሚረዱህ ጥቂት መርሆዎች እነሆ፡፡

  1. በሌሎች ላይ አትፍረድ፡፡

በሌሎች ላይ መፍረድ ከሌለብን ምክንያቶች አንዱ ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት የተሟላ መረጃ የሌለን በመሆኑ ነው! ይህን ሊያደርግ የሚችል አንድ ብቻ ነው – እርሱም እግዚአብሔር ነው፣ እኛ ደግሞ እርሱን አይደለንም! በሌላው ሰው አነሳሽ ምክንያቶች፣ ባሕሪያት፣ ምኞቶች፣ ቃሎች እና ድርጊቶች ላይ ማጠቃለያ ላይ ስንደርስ፣ ይህንን የምናደርገው በእውነታው ቅንጣቢ እውቀት ላይ ተመስርተን በመሆኑ ስህተት ለመስራት ቅርብ እንሆናለን፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልብ ይመለከታል፤ ሰው ግን ይህን ማድረግ አይችልም፡፡ ስለዚህ ፍርዱን ለእግዚአብሔር ስጥ- የአንተ ዋነኛ ስራ ማፍቀር ነው!

‹‹እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፣ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።›› -ማቴዎስ 7፡1-2

በሌሎች ላይ የመፍረድ ተቃራኒው ምንድን ነው?

  1. መጀመሪያ የራስህን አይን አጥራ፡፡

‹‹በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፣ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም? ወይም ወንድምህን። ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፣ በዓይንህ ምሰሶ አለ። አንተ ግብዝ፣ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፣ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ።›› -ማቴዎስ 7፡3-5

ብዙ ጊዜ፣ ሰዎች በራሳቸው ላይ ቀለል ብለው በሌላው ሰው ላይ ግን ጠንካራ ሂስ የማድረግ ዝንባሌ ይታይባቸዋል፡፡ በአብዛኛው የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ሌሎችን ዝቅ በምናደርግበት ጊዜ የበላይ የመሆን ስሜት ስለሚሰማን ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ያለውን ሰይጣናዊ ሃሳብ አስተዋልክ አይደል? ከዚህ ይልቅ ሁኔታውን የተገላቢጦሽ እናድርገው፡- ለራስህ ጉድለቶች ጠንካራ ሂስ በመስጠት በሌሎች ላይ ቀላል በል፡፡ መንፈሳዊው የብረት መጋዝህ በአይንህ ውስጥ ባለው ዛፍ ላይ ካነጣጠረ በኋላ የ‹‹ምንጣሮ ለክርስቶስ›› ክለብ አባል መሆን ትችላለህ!

ከአይንህ ሊወገድ የሚገባ ምን ግንድ አለብህ? በመጀመሪያ የቱን ልታስወግድ አቀድክ?

‹‹የክርስቲያን ማህበረሰብ እኛ ወደ ክርስቶስ መልክ የምንቀየርበት የሥራ ስፍራ ነው፤ በመሆኑም በዚህ የሥራ ስፍራ ንጽሕናን ልንጠብቅ አይገባም፡፡›› -ስቴቭ ኦቨርማን

  1. ‹‹ለትልቁ ጉዳይ›› ትኩረት ስጥ፡፡

በአንድ ወይም በሁለት ዋና ጉዳዮች ላይ ከሌላ ክርስቲያን ጋር አለመግባባት ላይ ልትደርስ ትችላለህ፡፡ ነገር ግን ይህ አለመግባባት ጓደኝነታችሁን እንዲያቋርጥ ፈፅሞ አትፍቀድ! በአማኞች ሕይወት ውስጥ በጣም ወሳኙ ነገር ምንድን ነው? ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ሕብረትና ስለኢየሱስ ክርስቶስ ያላቸው አስተያየት አይደለምን? በእዚህ ጉዳይ ላይ የምትስማሙ ከሆነ የቀረው ነገር ሁሉ ኢምንት ሊሆን ይገባል፡፡ ጥቃቅን በሆኑ የልዩነት ነጥቦቻችሁ ላይ ሳይሆን ዋና በሆኑ የስምምነት ነጥቦቻችሁ ላይ ትኩረት አድርግ፡፡

‹‹አስፈላጊ በሆኑ ነገሮች ላይ አንድነት፣ አጠያያቂ በሆኑቱ ደግሞ የመምረጥ ነፃነት፣ ነገር ግን በሁሉ ነገር ፍቅር ይኑርህ፡፡››-ሩፓርተስ ሜልዴኑስ

  1. ፋታ ስጥ፡፡

‹‹በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤›› -ኤፌሶን 4፡2። ጥቅሱ እንደሚያዘው፣ ለምን ትሑት፣ የዋህና ትዕግስተኛ መሆን ያስፈልገኛል? ምክንያቱማ፣ አንተም እንደማንኛውም ሰው ታጠፋልህ፡፡ ከዛም ሰዎች ‹‹እንዲያልፉህ›› የምትፈልግበት ወቅቶ ይኖራልና ነው፡፡ ከሌሎች ጋር ያለህን የሕብረት መልክ ራስህ ልትወስን ትችላለህ፡፡ ስህተት ፈላጊ ከሆንክ ምናልባት ሰዎችም ባንተ ላይ ይህንኑ ያደርጉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ዝንባሌህ፡- ‹‹አብረን ማደግ አለብን፤ እርስ በእርሳችን እንረዳዳ፣›› የሚል ከሆነ፣ ሕብረታችሁ ጥልቅና ጠንካራ እየሆነ ይሄዳል፡፡ በወንድምህ ወይም እህትህ ላይ የምታየውን የተገለጠ አጥፊ ኃጢአት ችላ በማለት ማበረታታት እንደሌለብህ ሁሉ በእያንዳንዱ ስህተቶቻቸው ላይ እጅ ማንሳትም አይገባህም፡፡

ማን ፋታ እንዲሰጥህ ትፈልጋለህ? በምን መንገድ?

  1. ምቹ በሚሆንበት ጊዜ፣ በፍቅር አርም፡፡

‹‹የተገለጠ ዘለፋ ከተሰወረ ፍቅር ይሻላል። የወዳጅ ማቍሰል የታመነ ነው፤ የጠላት መሳም ግን የበዛ ነው።››– -ምሳሌ 27፡5-6። አስቀድሞ የተገለጹትን- አለመፍረድ፣ በራስህ አይን ውስጥ ያለውን ማጥራትና የሌሎችን ሰዎች ስህተቶች ማለፍ- ከግምት ውስጥ አስገብተህ ለአማኙ ድነት ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ላለ ሕብረት ሲባል አንዳንድ ጉዳዮችን ለመፍታት በፍቅር እርምጃዎችን ልትወስድ ትችላለህ፡፡ ያን ሰው የምትወድ ከሆነ በእርግጥ እርምጃ ትወስዳለህ፡፡ ነገር ግን ድርጊትህ በፍቅርና ትህትና ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይገባል፡፡ እርምጃውን ስትወስድ ውስጥህ እንዲህ ሊል ይገባል፡- ‹‹ይህን ሳደርግ ካንተ የተሻልኩ ነኝ እያልኩ አይደለም፤ መፍትሄ እየጠቆምኩ ያለሁ፣ ነገር ግን እኔም ብሆን ችግር ያለብኝ ሰው ነኝ፡፡ ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ላናግርህ እወዳለሁ…››

  1. አነሳሽ ምክንያትህንና ስልቶችህን መርምር፡፡

‹‹እንደሚዋጋ ሰይፍ የሚለፈልፍ ሰው አለ፤ የጠቢባን ምላስ ግን ጤና ነው።›› –ምሳሌ 12፡18። በሌላው ወንድምህ ወይም እህትህ ውስጥ ስላየኸው ነገር መነጋገር እንዳለብህ ሲሰማ፣ ከማናገርህ በፊት ራስህን ይህን ጥያቄ ጠይቅ፡- ‹‹አላማዬ፣ ማረድ ወይስ ቀዶ ጥገና ማድረግ?›› ከምክርህ በኋላ ሰዎቹ በመንፈስ እና በፍቅር ከተቀመመው ትሁት ምክርህ የተነሳ ይበረታታሉ ወይስ በደረሰባቸው ውጊያ ቆስለው ይደማሉ?

የጤናማ ቤተ ክርስቲያን ምልክቶች

  • መጋቢው ለመጽሐፍ ቅዱስ ክብር ይሰጣል፣ እሱንም ያስተምራል
  • ጸሎትና አምልኮ በግላጭ ይታያሉ፡፡
  • ወንጌል በግልጽ ይቀርባል፡፡
  • ሰዎችን ለክርስቶስ ደቀ መዝሙር በማድረግ፣ ለታላቁ ተልዕኮ ትኩረት ይሰጣል፡፡
  • አማኞች፣ እርስ በእርሳቸውና ለጎብኚዎች ምቹ ናቸው፡፡
  • ሁሉም አማኝ በቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት ውስጥ የራሱን ድርሻ ይወጣል፡፡
  • ለተቸገሩ ለጋሶች ናቸው፡፡
  • በእግዚአብሔ ላይ ያለ እምነት ለሁሉም ውሳኔዎች መሠረት ነው፡፡

ከሕይወትህ ጋር ማዛመድ፡-

  1. በሣምንት ምን ያህል ጊዜ በክርስቲያኖች ሕብረት ውስጥ ትካፈላለህ? (ይህ ሕብረት፣ ቤተ ክርስቲያን በመካፈል፣ መጽሐፍ ቅዱስ በማጥናት፣ የጸሎት ስብሰባዎች ላይ በመካፈል፣ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር በተለየ መንገድ አብሮ ጊዜ በማሳለፍ የሚገለጽ ሊሆን ይችላል)
  2. ይህንን በበቂ ደረጃ እያደረክ ያለህ ይመስልሃል?
  3. ለውጥ ለማድረግ የምታቅድ ከሆነ ምን አይነት ለውጦች ታደርጋለህ? በምን ያህል ፍጥነት?

የቃል ጥናት ጥቅስ፡-

‹‹ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፣ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፣ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ፤›› -ዕብራዊያን 3፡13

ማጠቃለያ፡- ‹‹ከመንጋዎቼ ጋር አብረህ ትሆናለህ ወይ?›› ሲል ኢየሱስ ይጠይቅሀል፡፡

ምዕራፍ 7ትን ያጥኑ

Leave a Reply

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading