የሕይወት እንጀራ

የጌታ እራት ሥርዓት እንዴት እንደ ተጀመረ?

This entry is part 172 of 8 in the series የጌታ እራት

የጌታ እራት

«ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት»

የጌታ እራት ሥርዓት እንዴት እንደ ተጀመረ?

ስለ ጌታ እራት ኢየሱስ የሰጣቸውን በርካታ መመሪያዎች መገንዘብ አስፈላጊ ነው።

የጌታ እራት ሥረ መሠረት

ቅዱስ ቁርባን (የጌታ እራት) ማለት ምን ማለት ነው?

አላግባብ የጌታን እራት ስለመውሰድ የተሰጡ ማስጠንቀቂያዎች

ክርስቲያኖች በጌታ እራት ላይ ያላቸው የግንዛቤ ልዩነት

ጌታን እራት ለሚያስፈጽሙ መሪዎች አስተያየት

ኢየሱስ በምድራዊ ሕይወቱ መጨረሻ ላይ የጌታን እራት ሥርዓት አስጀመረ። የጌታ እራት እንዴት እንደ ተጀመረ በአዲስ ኪዳን ሰአራት ዋና ዋና ምንባቦች ውስጥ ተጽፎ ይገኛል። ማቴ. 26፡17 30፤ ማር. 14፡17-26፤ ሉቃስ 22፡14-20 እና በ1ኛ ቆሮ. 1፡23-34። (እነዚህን ምንባቦች በዝግታ ለማንበብ ጊዜ ውሰድ። 

ከመሰቀሉ በፊት በነበረችው ሌሊት ኢየሱስ የአይሁድን የቂጣ በዓል (ፋሲካን) ሊያከብር ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተሰበሰበ። የፋሲካ በዓል እግዚአብሔር በአስገራሚ ማዳኑ አይሁዶችን ከግብፅ ባርነት ነፃ ያወጣበትን ቀን በማሰብ የሚከበር ነበር (ዘጸአት 12፡1-30)። ኢየሱስም አዲስ ፋሲካ ሊጀምር የተቃረበበት ወቅት ነበር። በማግስቱ በመስቀል ላይ ሲሞት ለአይሁዶች ብቻ ሳይሆን፥ ለሚያምኑበት ሕዝብ ሁሉ ከኃጢአት ነፃ መሆንን አምጥቷል። 

ደቀ መዛሙርት በዙሪያው እንዳሉ ኢየሱስ የጌታን እራት ሥርዓት ወሰነ። የእርሱ ተከታዮችም የጌታን እራት ሥርዓት በዘመናት ሁሉ እንዲፈጽሙ ተናግሯል። ይህ ሥርዓት ኢየሱስ ዘላለማዊ መንግሥቱን ለመመሥረት እስከሚመለስበት ጊዜ ድረስ ይቀጥላል። በፋሲካ በዓል መጨረሻም ኢየሱስ እንጀራን ያዘ። ሲቆርሰውም ይህ ስለ እነርሱ የሚቆረሰው አካሉ መሆኑን ነገራቸው። እንጀራውንም ሲበሉ ኢየሱስን ማስታወስ አለባቸው። ከዚያም ኢየሱስ ወይን ያለበትን ዋንጫ አንስቶ ደቀ መዛሙርት እንዲጠጡት ሰጣቸው። ወይኑም 

ለኃጢአታቸው ይቅርታ የሚፈሰው ደሙ መሆኑን ነገራቸው። ደቀ መዛሙርት መጠጣት የነበረባቸው ኢየሱስን በማስታወስ ነው። በቀጣዩ ቀን ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሲሞት ሥጋው ተቆረሰ፤ ደሙም ፈሰሰ። እርሱ ስለ እያንዳንዳችን ሲል ሞተ። የሥጋው መቆረስና የደሙ መፍሰስ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል የተደረገ የኃጢአት ይቅርታ ማስገኛ ኪዳን መሆኑን ኢየሱስ ተናግሯል።

ምንጭ፡- “የጌታ እራት”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ ተሾመ ነጋሽ የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም የታተመ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የጌታ እራት

«ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት» ስለ ጌታ እራት ኢየሱስ የሰጣቸውን በርካታ መመሪያዎች መገንዘብ አስፈላጊ ነው።

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading