የሕይወት እንጀራ

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3)

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምሕርት ጥናት

የመጀመሪያው አስፈላጊ ነጥብ

እግዚአብሔር አለን?

እግዚአብሔር ራሱን እንዴ ገለጠ?

የእግዚአብሔር መለያዎች

እግዚአብሔር ራሱን ማን ብሎ ይጠራል?

ሥላሴ ማለት ምን ማለት ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር እስትንፋስ የተጻፈ ነውን?

የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት

የክርስቶስ ሰብአዊነት

የክርሰቶስ መለኮታዊና ሰብአዊነት ውህደት

የክርስቶስ ራሱን ባዶ ማድረግ [Kenosis/ኪኖሲስ]

ክርስቶስ ኃጢአት ሊያደርግ አለመቻሉ [Impeccability/ ኢምፔኬቢሊቲ]

የክርስቶስ ምድራዊ ሕይወት

የክርስቶስ ትንሣኤና ዕርገቱ

መንፈስ ቅዱስ አካል ነውን?

መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አምላክ ነውን?

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በብሉይ ኪዳን

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በክርስቶስ ሕይወት

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በድነት (ደኅንነት) ውስጥ

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ፥ በክርስቲያኑ ሕይወት

የመንፈስ ቅዱሰ የወደፊት ሥራ

ስለ መላእክት ትምህርት

ስለ ለይጣን ትምህርት

ስለ አጋንንት ትምህርት

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3)

የሰው ኃጢአት

ምርጫ ምንን ያካትታል?

የክርስቶስ ሞት

በክርስቶስ ሞት የተገኙ አንዳንድ ጥቅሞች

የአማኙ ዋስትና

የድነት (የደኅንነት) ቃላት

ቤተ ክርስቲያን በሚለው ፅንሰ አሳብ ውስጥ የሚካተተው ምንድነው?

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን

የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች

ዓለም-አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን መቼ ተጀመረች?

ስለ ወደፊቱ ጊዜ ያሉ መሠረታዊ አመለካከቶች

የፍዳው ዘመን [Tribulation]

የሺህ ዓመት ግዛት

የዘመኑ መጨረሻ

የወደፊቱ ፍርድ

ትንሣኤዎች

መንግሥተ ሰማያትና የቅጣት ስፍራ

«ኃጢአት ለምን ከእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ ገባ?» የሚለው ጥያቄ ሰው በቀላሉ ሊመልሰው የማይችለው ምስጢር ነው። ሆኖም በምን አኳኋን ኃጢአት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ እንደገባ በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ላይ በግልጽ ተዘግቧል።

ይህን ምዕራፍ የይዘቱን ታሪካዊነት «ተረት፥ እውነተኛ ተረት፥ აፈ-ታሪክ፥ የተቀደሰ አፈ-ታሪክ» ወዘተ. እያሉ የሚክዱ ብዙ ነቃፊዎች አሉ። ይሁን እንጂ ታሪካዊ ያልሆነ ነገር ግን “እውነተኛ” ባሕርይ እንዳለው አድርገው አጥብቀው ይይዛሉ (ይህም መጨረሻው ውሸት የሆነ ታሪክ ማለት ነው)። እንዲህ ያለውን የተዛባ ሥነ-መለኮታዊ አመለካከት የሚያሳይ አንድ ምሳሌ እነሆ፦

«ጠንካራ ወግ አጥባቂዎች ካልሆንን በዘፍጥረት 3 ላይ የተጻፈውን ታሪክ “እውነተኛ አፈ-ታሪክ” ነው እንላለን። ይህም ማለት ኤደን በካርታ ላይ ባትገኝም፥ እንዲሁም የአዳም እውቀት ከሰው ልጅ የታሪክ ቀመር ወይም መዘክር ጋር ባይታረቅም፥ ምዕራፉ ልክ በሰው ልጅ የታሪክ ጅማሬ ወቅት እንደነበረው ሁሉ ዛሬ ያለውን የሰው ልጅ የኑሮ ልምድ ስፋት ያሳያል ማለት ነው። በቀላል ቋንቋ ለመናገር፥ እኛ የወደቅን ፍጡሮች ነን፤ የአዳምና የሔዋን ታሪክም የእኔና የእናንተ ታሪክ ነው።»

ይህ አባባል በዚህ መልኩ ይቅረብ እንጂ፥ የታሪኩን መዋቅር፥ ዝርዝር ሁኔታውንና ተከታታይ ጥቅሶቹን ልብ ብሎ ያጤነ ሰው ታሪኩ ፍጹም እውነታ እንዳለው ይረዳል። (ማቴ. 19:3-6 እና ሮሜ 5:12-21፤ እንደዚሁም ሉቃስ 3:38 እና ይሁዳ 14 አዳም ማለት ጠቅላላ የሰው ዘር ማለት ሳይሆን፥ አንድ የተወሰነ ግለሰብ መሆኑን ነው የሚያመለክቱት።)

ፈተናው

አዳምና ሔዋን የተፈተኑበት ሁኔታ ታላቅ ትርጉም ያለው ሲሆን፥ በአንጻሩ ደግሞ ቀላል ነው። ቀላልነቱም በኤደን ገነት ካሉት እጅግ ብዙ ፍሬዎች መካከል አንዱን ብቻ ከመከልከላቸው አንጻር ሲታይ ነው። ክፉን ነገር በሙከራ እንዳያውቁ መከልከላቸው የእግዚአብሔር በረከት እንጂ፥ የሕይወታቸው ጉድለት አይደለም።

በሌላ አቅጣጫ ስንመለከተው ግን እገዳው የሞት ወይም የሕይወት ጉዳይ ነውና ታላቅ ጠቀሜታ ነበረው። ትእዛዙን ማክበር ወይም መጣስ፥ ለእግዚአብሔር ፈቃድ መገዛትን ወይም አለመገዛትን (መዛትን) የሚያሳይ ነበር። (እርግጥ አዳምና ሔዋን ሌላም ኃላፊነት ነበረባቸው፤ ለምሳሌ የኤደን ገነትን መንከባከብ።) በኋላ በግልጽ እንደሚታየው ክፉውንና መልካሙን የምታስታውቀው ዛፍ እውነተኛ ዛፍ ስትሆን፥ እግዚአብሔር ይህንኑ እውቀት እንድታስተላልፍ መሣሪያ ያደረጋት ነበረች።

የፈተናው ሂደት

የሰይጣን ጥቃት በማባበል የተጀመረው በዘፍጥረት 3፡1 ላይ ነው። እግዚአብሔር አንዳች ነገር እስካልነፈጋቸው ድረስ ለእነርሱ መልካም አለመሆኑን ሔዋን እንድታምን ማድረግ ነበር የሰይጣን ዋና ሙከራ። ቁጥር 2 ላይ እንደተገለጠው የእርሷ መልስም እግዚአብሔር ሁሉን እንደፈቀደላቸውና አንድ ነገር መከልከሉ ቀላልና የማይጎዳቸው መሆኑን የሚገልጽ ነበር።

የሰይጣን ሥራ ሔዋን በእግዚአብሔር ቅር እንድትሰኝ ማድረግ ነበርና ማታለያው እንዲህ የሚል ነበር፦ “እግዚአብሔር መልካም ቢሆንማ አንዳችም ነገር አይከለከላችሁም ነበር። ነገር ግን የዚህን ዛፍ ፍሬ እንዳትበሉ ከልክሏልና መልካም ሊሆን አይችልም። በተቃራኒው የእኔ ዕቅድ እግዚአብሔር የከለከላችሁን ሁሉ እንድታደርጉ ይፈቅድላችኋል።”

የዚህ አሳብ መንደርደሪያ ነጥብ፥ የምክንያት አደራደር ቅደም-ተከተልን የተከተለ ነበር።

  • መነሻው (ዋናው ነጥብ)፦ እገዳ መልካም አይደለም የሚል ነው።
  • ቀጣዩ ነጥብ፦ የእግዚአብሔር ዕቅድ እገዳን ይደግፋል የሚል ሲሆን፥
  • ድምዳሜው፦ ከዚህ በመነሳት «የእግዚአብሔር ዕቅድ መልካም አይደለም፤ በተቃራኒው እገዳ የሌለው የሰይጣን ዕቅድ መልካም ነው» የሚል ሆነ።

ሔዋንም ልትፈጽመው ስለወሰነችው ስሕተት ራሷን በራሷ ትክክለኛ ለማድረግ ምክንያቶቿን በሕሊናዋ ደረደረች። የተከለከለውን ፍሬ በመመልከት፥ ለምግብነት መልካም ነው ብላ አሰበች። ደግሞም እግዚአብሔር ጣፋጭና የተለያየ ምግብ ለእነርሱ የማዘጋጀት ኃላፊነት እንደጣለባት በማስታወስ፥ ይህን መልካም ፍሬ መመገብ በምን አኳኋን ስሕተት ይሆናል ብላ አመነች። ስለ ፍሬውም ማማርና የእውቀት ምንጭነት የተለመደ ምክንያቷን አቀረበች። እግዚአብሔር ያን ፍሬ እንዳይበሉ የመከልከሉ እውነት ከአእምሮዋ ጠፋ። ድርጊቱን መልካም ለማስመሰል በምታደርገው ጥረት የተነሳ አእምሮዋ በምክንያቶች የተሞላ ስለነበር፥ እሱና አዳም የእግዚአብሔርን ፈቃድ በግልጽ በመጣስ ከፍሬው በሉ።

የኃጢአታቸው ውጤቶች

በዚህ ኃጢአት የተነሳ ቀጥሎ ያሉት መለኮታዊ ፍርዶችና ሁኔታዎች ተከሰቱ፦

  1. እባብ በደረቱ እንዲሄድ ተፈረደበት (ዘፍጥ. 3፡14)።
  2. የዘፍጥረት 3፡15 ትንቢት (Protevangelium)፦ ሰይጣን ከሴቲቱ ከሚወለደው ዘር ጋር ጠላትነት እንዲኖረውና ክርስቶስን የሚያሳምም፥ ግን ሊያጠፋ የማይችል ቁስል በተረከዙ ላይ እንዲያደርስ ተፈቀደለት። እርሱ (ሰይጣን) ግን ሕይወቱን የሚያጠፋ ፍርደ-ቁስል በራሱ ላይ እንዲደርስበት ተፈረደበት (“ራሱን” የሚለውን ቃል “ተረከዙን” ከሚለው ጋር ያነጻጽሩ)። (ማስታወሻ፦ በ1962 ዓ.ም. ታትሞ የወጣው የድሮው የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ እሳቡ የሔዋንን ዘር “ሰኮናውን ይቀጠቅጠዋል” በሚል የተተረጎመ ሲሆን፥ በ1988 ዓ.ም. ተሻሽሎ በታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ግን “እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ተረከዙን ትቀጠቅጣለህ” በሚል ተጽፏል።)
  3. በሴቲቱ ላይ የተላለፈው ፍርድ፦ ሔዋንና ሴቶች ሁሉ በፅንስና በወሊድ ጊዜ በጭንቅ እንዲወልዱና ለባሎቻቸውም ተገዢ እንዲሆኑ ተወሰነባቸው (ቁ. 16)።
  4. በወንዱና በምድር ላይ የተላለፈው ፍርድ፦ አዳምና ሰዎች ሁሉ በመሬት መረገም ምክንያት አድካሚና አታካች የሆነ የሥራ ሕይወት እንዲኖራቸው ተወሰነባቸው (ቁ. 17-19)።
  5. ሁለንተናዊና መንፈሳዊ ሞት፦ የሰው ዘር ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ቅዱስ ኅብረት ተቋረጠ፤ መንፈሳዊና ሥጋዊ ሞትም መጣ፤ ከኤደንም በረከት ተከለከለ። የአዳምና የሔዋን ኃጢአት የታሪክን አቅጣጫና የእነርሱን ዘር ሕይወት ሁሉ ቀየረ (ሮሜ 5፡12-21ን እንደገና ያንብቡ)።

ምንጭ፦ “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ-ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፥ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው። ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው። ይህን ጽሑፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሑፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው።

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምሕርት ጥናት

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ የሰው ኃጢአት

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading