Site icon የሕይወት እንጀራ

ትንሣኤዎች

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምሕርት ጥናት

የመጀመሪያው አስፈላጊ ነጥብ

እግዚአብሔር አለን?

እግዚአብሔር ራሱን እንዴ ገለጠ?

የእግዚአብሔር መለያዎች

እግዚአብሔር ራሱን ማን ብሎ ይጠራል?

ሥላሴ ማለት ምን ማለት ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር እስትንፋስ የተጻፈ ነውን?

የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት

የክርስቶስ ሰብአዊነት

የክርሰቶስ መለኮታዊና ሰብአዊነት ውህደት

የክርስቶስ ራሱን ባዶ ማድረግ [Kenosis/ኪኖሲስ]

ክርስቶስ ኃጢአት ሊያደርግ አለመቻሉ [Impeccability/ ኢምፔኬቢሊቲ]

የክርስቶስ ምድራዊ ሕይወት

የክርስቶስ ትንሣኤና ዕርገቱ

መንፈስ ቅዱስ አካል ነውን?

መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አምላክ ነውን?

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በብሉይ ኪዳን

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በክርስቶስ ሕይወት

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በድነት (ደኅንነት) ውስጥ

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ፥ በክርስቲያኑ ሕይወት

የመንፈስ ቅዱሰ የወደፊት ሥራ

ስለ መላእክት ትምህርት

ስለ ለይጣን ትምህርት

ስለ አጋንንት ትምህርት

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3)

የሰው ኃጢአት

ምርጫ ምንን ያካትታል?

የክርስቶስ ሞት

በክርስቶስ ሞት የተገኙ አንዳንድ ጥቅሞች

የአማኙ ዋስትና

የድነት (የደኅንነት) ቃላት

ቤተ ክርስቲያን በሚለው ፅንሰ አሳብ ውስጥ የሚካተተው ምንድነው?

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን

የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች

ዓለም-አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን መቼ ተጀመረች?

ስለ ወደፊቱ ጊዜ ያሉ መሠረታዊ አመለካከቶች

የፍዳው ዘመን [Tribulation]

የሺህ ዓመት ግዛት

የዘመኑ መጨረሻ

የወደፊቱ ፍርድ

ትንሣኤዎች

መንግሥተ ሰማያትና የቅጣት ስፍራ

አሳቡ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም፥ አንድና አጠቃላይ የትንሣኤ ቀን አይኖርም። ከጊዜ ሳይሆን ከሰዎች አንጻር ሲታይ ሁለት ዓይነት ትንሣኤ እንደሚኖር ይታወቃል። ይህም የጻድቃንና የኃጥአን ትንሣኤ ነው (ሐዋ. 5፡28-29፤ ሉቃስ 14፡14)። በሞትና በትንሣኤ መካከል ባለው ጊዜ ጻድቃንም ሆን ኃጥአን “በነቃ ሕሊና” ይኖራሉ። አማኙ በዚህ ጊዜ ከጌታ ጋር ሲሆን (2ኛ ቆሮ. 5፡1-8፤ ፊልጵ. 1፡23)፣ የማያምኑት በስቃይ ይኖራሉ (ሉቃስ 16፡19-31)። 

የጻድቃን ትንሣኤ 

የጻድቃን ትንሣኤ የመጀመሪያው ትንሣኤ ሲባል፥ ይህም በተለያየ ደረጃ የሚሆን እንጂ፥ በአንድ ጊዜ የሚፈጸም አይደለም። በክርስቶስ የሞቱት ከቤተ ክርስቲያን ጋር አስቀድመው ይነጠቃሉ (1ኛ ተሰ. 4፡16)። በፍዳው ዘመን የሚዋጁትና በዚያው ዘመን የሚሞቱ ከሺህ ዓመቱ አገዛዝ በፊት ይነሳሉ (ራእይ 20፡4)። በብሉይ ኪዳን የተዋጁትም በጻድቃን ትንሣኤ የመካፈል ዕድል ይኖራቸዋል። እርግጥ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪዎች፥ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን የሚነሱበትን ጊዜ በተመለከተ ያላቸው አሳብ የተለያየ ነው። አንዳንዶቹ በቤተ ክርስቲያን መነጠቅ ጊዜ ከቅዱሳን ጋር ይነሳሉ ሲሉ፥ ሌሎቹ ደግሞ ትንሣኤያቸው በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይሆናል ይላሉ (ዳን. 12፡2)። ጸሐፊው ሁለተኛውን አመለካከት ይደግፋል። 

የኃጥአን ትንሣኤ 

ስለ ነጩ ዙፋን ፍርድ ስናጠና እንደተመለከትነው፥ ያልዳኑ ሰዎች ከሺህ ዓመቱ በኋላ ይነሱና ወዲያው ይፈረድባቸዋል፤ ከዚያም ለዘላለም ወደ እሳት ባሕር ይጣላሉ (ራእይ 20፡11-15)። በትንሣኤያቸውም የእሳት ባሕር ስቃይ ሊሰማው የሚችልና ለዘላለም የሚኖር ልዩ አካል ይሰጣቸዋል።

ምንጭ፡- “የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምህርት ጥናት”፣ በዶክተር ቻርልስ ሲ. ራይሪ ተጽፎ፣ በሲሳይ ደሳለኝ የተተረጎመ እና በየላፕስሊ/ብሩክስ ፋውንዴሽን የታተመ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓተ ትምሕርት ጥናት

የወደፊቱ ፍርድ መንግሥተ ሰማያትና የቅጣት ስፍራ
Exit mobile version