የሕይወት እንጀራ

ሌሎች ትምሕርቶች

የግል ፀሎት ምንድን ነው?

አንተ ግን ስትጸልይ፣ ወደ እልፍኝህ ግባ፣ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፣ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሀል፡፡ ማቴዎስ 6፡6 ኢየሱስ ‹‹በስውር ላለው አባታችሁ ፀልዩ›› እንጂ ‹‹በስውር ስፍራ ወዳለው አባታችሁ ህልምን አልሙ፡፡›› አላለም፡፡ ፀሎት ፈቃድን ማስገዛት ይጠይቃል፡፡ ወደ እልፍኛችን ከገባንና በራችንን ከዘጋን በኋላ ልናደርግ የሚቸግረን ትልቁ ነገር ቢኖር መፀለይ ነው፡፡ አእምሮአችንን ለፀሎታችን ልንጠቀምበት በምንችለው ሁኔታ ማዘጋጀት […]

የግል ፀሎት ምንድን ነው? Read More »

የዘላለም ሕይወት፣ የእግዚአብሔር ታላቁ ስጦታ

የዘላለም ሕይወትን የማገኘው እንዴት ነው? የዘላለም ሕይወትን እንዳገኝ የየትኛው ቤተ ክርስቲያን አባል መሆን አለብኝ የሚል ጥያቄ ያስጨንቆታል? የዘላለም ሕይወት ለማግኘት ከእኔ የሚጠበቀውስ ምን ይሆን በሚል ሃሳብ ተወዛግበው ያውቃሉ? እርሶ ሃጢአተኛ በመሆኖ እና እግዚአብሔር ደግሞ ፍጹም ፃድቅ ስለሆነ የዘላለም ሕይወት ሊደረስበት የማይቻል እና የተወሰኑ ሰዎች ብቻ የሚያገኙት እንደሆነስ አስበው ያውቃሉ? ከእነዚህ ጥያቄዎች አንዱ የሚመለከትዎ ከሆነ ምላሹን

የዘላለም ሕይወት፣ የእግዚአብሔር ታላቁ ስጦታ Read More »

የእግዚአብሔር ቃል ፋይዳ ምንድን ነው?

የእውነት ምንጭ እኔ ወይም ሌላ ሰው አይደለም፡፡ የእውነት ምንጭ የመንግስትና የግል ዜና ማሰራጫዎች ወይም ሚዲያዎችም አይደሉም። የእውነት ምንጭ የታዋቂ ሰዎች አስተያየቶች አልያም የሳይንቲስቶች ላብራቶርም አይደለም። የእውነት ምንጭ ስሜት ሕዋሶቻችንም አይደሉም። እውነት ከራሱ ከእግዚአብሔር ብቻ ትፈልቃለች፡፡ እናም እውነት ብዬ የያዝኳቸውን እውቀቶች ሁሉ ወይም ደርሼባቸዋለው የምላቸውን ‘‘እውነቶች’’ ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል ፈትሼ በእርግጥም እውነት ስለመሆናቸው ማረጋገጥ ይኖርብኛል። ሀ.

የእግዚአብሔር ቃል ፋይዳ ምንድን ነው? Read More »

የሰይጣን ዋነኛ የጦር ስልት ምንድን ነው?

የሰይጣን ዋነኛ የጦር ስልት የእግዚአብሔር ባህሪ አጣሞ፣ ቀይሮ እና አወናብዶ በማስቀመጥ ለሚሰሙት ሁሉ መስበክ ነው። ያለው ትልቁ የውጊያ መሳሪያ ማታለል፣ የተዘራውን እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል መንጠቅ፣ መዋሸት እና የመሳሰሉትን የማወናበድ ስራዎች መስራት ነው። ውሸትን እውነት አስመስሎ ማቅረብ የተዋጣለት ብልሃቱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ስለሰይጣን የጦር ስልቶች የሚለውን የተወሰኑ አብነቶች እንመልከት፡- የማቴዎስ ወንጌል 4፥15 በሰሙት ጊዜም ሰይጣን ወዲያው

የሰይጣን ዋነኛ የጦር ስልት ምንድን ነው? Read More »

እግዚአብሔር የማያምኑ ሰዎችን/የኢ-አማኒያንን ፀሎት ሰምቶ ይመልስ ይሆን?

ዮሐንስ 9፡31 ‘‘እግዚአብሔርን የሚፈራ ፈቃዱንም የሚያደርግ ቢኖር ያንን እግዚአብሔር ይሰማዋል እንጂ ኃጢአተኞችን እንዳይሰማ እናውቃለን’’ ይላል። ከዚህ በተጨማሪ፣ ‘‘እግዚአብሔር፣ ኢ-አማኒው ኢየሱስን ለመቀበል ሲል የሚያደርገውን የንስሃ ፀሎት ብቻ ነው ሰምቶ የሚመልሰው’’ የሚል የተለመድ አባባል አለ። በእነዚህ ምክንያቶች አንዳንዶች እግዚአብሔር፣ የማያምኑ ሰዎችን ፀሎት ሰምቶ እንደማይመልስ ያምናሉ። የዮሐንስ 9፡31 የአውድ ትርጉም ግን እግዚአብሔር በማያምን ሰው እጅ ተአምራትን አያደርግም የሚል

እግዚአብሔር የማያምኑ ሰዎችን/የኢ-አማኒያንን ፀሎት ሰምቶ ይመልስ ይሆን? Read More »

እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ መሆኑ ፀሎትን አላስፈላጊ አያደርገውም ወይ?

እግዚአብሔር የማያውቀውን ነገር ልንነግረው አንችልም፡፡ ስንፀልይ የምንናደርገው ነገር ቢኖር እርሱ አስቀድሞ የሚያውቀውን ነገር በቃላችን መደርደር ነው፡፡ ይህ ጉዳይ እንድንፀልይ የሚያበረታታን እንጂ ፀሎትን አላስፈላጊ የሚያደርገው አይደለም፡፡ ስለ እኛ እና ስላለንበት ሁኔታ በሚገባ ከሚያውቅ ሰው ጋር ያው የሚያውቀውን ጉዳይ ስናወራ እረፍት ይሰማናል፡፡ የእግዚአብሔር ምላሽ በሰጠነው መረጃ ላይ ሳይሆን እርሱ ስለእኛ ሁኔታ በሚያውቀው ፍፁም እውቀት ላይ የተመሰረተ መሆኑ

እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ መሆኑ ፀሎትን አላስፈላጊ አያደርገውም ወይ? Read More »

እውን እግዚአብሔር አለ?

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች እግዚአብሔር እንዳለ ያምናሉ፡፡ ጥቂቶች ማስረጃ አለን ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ እግዚአብሔር እንዳለ በማስረጃ አረጋግጠህ ታውቃለህ? በውኑ የእርሱ መኖር በሳይንስ ሊረጋገጥ ይችላልን? አንተን ራስህንና አለማትን አንድ ድንቅ አዕምሮ እንዲፈጠራቸው በእርግጠኝነት ታውቃልህ? ወይስ ይህ ጉዳይ በእምነት ብቻ ሊቀበሉት የተገባ ነው ብለህ ትደመድማለህ? እስቲ ይህን ጥያቄ እንዳስ፡፡ ሰዎች በእግዚአብሔር መኖር ጥያቄ ላይ መከራከር ከጀመሩ ብዙ ሺ አመታት

እውን እግዚአብሔር አለ? Read More »

ኢየሱስን መቀበል – መጽሐፍ ቅዱሳዊ ወይስ መናፍቃዊ?

እስቲ ለአፍታ በቡድ ማሰብ ትተን በግላችን፣ ለግላችን እናስብ። ሰከን ባለ ስሜት መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረንን ቃል እንመርምር። ለማሸነፍ ወይም ለመሸነፍ ሳይሆን ለማወቅ ቃሉን እንመርምር። ‘‘የትኛው ቡድን እንዲህ ያምናል?፣ የትኛውስ እንዲህ አያምንም?’’ የሚለውን ውጤት አልባ ክርክር ወደጎን ትተን ‘‘መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ያለው እውነት፣ የትኛው ነው?’’ በሚል መንፈስ ርዕሰ ጉዳዩን እንመርምር። ለመሆኑ ኢየሱስን መቀበል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው ወይ?

ኢየሱስን መቀበል – መጽሐፍ ቅዱሳዊ ወይስ መናፍቃዊ? Read More »

አስቀድሞ መወሰን ማለት ምን ማለት ነው? አስቀድሞ የመወሰን ሃሳብ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው?

ሮሜ 8፡29-31 የሚከተለውን ይላል፣ ‘‘ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤ አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው። እንግዲህ ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን ይቃወመናል?’’ ኤፌሶን 1፡5 እና 11 ደግሞ የሚከተለውን ያስነብበናል፣ ‘‘በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ

አስቀድሞ መወሰን ማለት ምን ማለት ነው? አስቀድሞ የመወሰን ሃሳብ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው? Read More »

በውኑ፣ ክርስቶስ ያማልዳልን?

1. መግቢያ፡- የሰው ልጅ ውድቀት የዚህ ጽሁፍ አቢይ አላማ በየዕለቱ በሚገጥሙን ጉዳዮች ማለትም፣ ስለታመሙ ሰዎች፣ በእስር ስላሉ ሰዎች፣ ስለ መሪዎች፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ አገር፣ ስለ አገልግሎት፣ ወዘተ አንዱ ለሌላው ወደ ፈጣሪው የሚያደርሰው የምልጃ ጸሎት፣ ክርስቶስ ለእኛ ባደረገው የማማለድ ሥራ ላይ ጥላውን እንዳያጠላበት ጥንቃቄ እንድናደርግ ለማሳሰብ ነው፡፡ እነደነዚህ አይነቶቹ – አንዱ ስለ ሌላው የሚጸልየው ጸሎት

በውኑ፣ ክርስቶስ ያማልዳልን? Read More »