የእግዚአብሔር ባሕሪይ

ሀ) የእግዚአብሔር መልካምነት ማቴ 19፡16-17 ለ) የእግዚአብሔር ምህረትና ጭከና ሮሜ 11፡22 ሐ) ቅዱስ ራዕ 4፡8 – እንደእግዚአብሔር ያለ ቅዱስ የለም 1ሳሙ 2፡2፤ ራዕ 15፡4 – እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ፍጹም ነው ሌዋ 19፡2፤ ማቴ 5፡48 – ከቅድስናው ተካፋዩ ልንሆን ይገባል ዕብ 12፡10፣ 14፤ 1ጴጥ 1፡16 – መንፈስ ቅዱስ ሊቀድሰን ይመጣል ሮሜ 15፡16 – ቅድስና ውብ ነው 2ዜና 20፡21፤ መዝ 29፡2 – ቅድስና-ንጽሕና የሚለውን ርዕስ በተጨማሪ ይመልከቱ ክፍል ሠ11 መ) ጻድቅና ትክክል ራዕ 16፡15፤ 19፡2 – እግዚአብሔር ኅጢአትን ይጸየፋል ዕብ 1፡8-9 – በመንግስቱ ክፋት አያድርም 1ቆሮ 6፡9-10 – በተጨማሪ እነዚህን ጥቅሶች ይመልከቱ ኢዮብ 34፡12፤ መዝ 7፡9፤ 116፡5፤ 119፡137 – ጽድቁን ልንካፈል ይገባል 1ዮሐ 3፡7 – ኃጢአትን ልንጠላ ይገባል ዕብ 12፡4፤ 1ዮሐ 3፡8-9 ሠ) አፍቃሪና ርኅሩኅ ዮሐ 3፡16፤ መዝ 69፡16፤ ሰ.አር 3፡22-23 – እግዚአብሔር ፍቅር ነው 1ዮሐ 4፡8፤ ቲቶ 3፡4-5 – ፍቅሩን ልንካፈል ይገባል ዘሌ 19፡18፤ ሉቃስ 10፡27፤ ሮሜ 13፡9፤ ገላ 5፡14 – እግዚአብሔርን ለእኛ ያለው ፍጹም ፍቅር ፍርሃታችንን አስወግዶ ይጥላል 1ዮሐ 4፡18 – ወደ እግዚአብሔር በድፍረት መግባት ሆኖልናል ዕብ 4፡16 – ከእግዚአብሔር ፍቅር የሚለየን የለም ሮሜ 8፡38-39 – ከፍቅር ጋር በተያያዘ ለትምህርት የሚሆን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል 1ቆሮ 13፡4-7 ረ) ታማኝና እውነተኛ ኢሳ 25፡1፤ ራዕ 3፡14፤ 19፡11 – ሰው ሃሰተኛ ቢሆንም እንኳ እግዚአብሔር ታማኝ ሆኖ ይኖራል ሮሜ 3፡4፤ ዮሐ 17፡3 – ተስፋን የሰጠው አምላክ የታመነ ነው ዕብ 10፡23፤ 11፡11 – ለመታደስ እርሱን ተስፋ እናደርጋለን 1ተሰ 5፡23-24፤ 2ጢሞ 1፡12 – ከኃጢአት ሊያስመልጠን እርሱ የታመነ ነው 1ቆሮ 10፡13 – ታማኝ የሆኑ ሰዎችን ማግኘት አስቸጋሪ ነው ምሳሌ 20፡6 – እግዚአብሔር እንደ እርሱ ታማኝ የሆኑ ሰዎችን ይፈልጋል (ራዕ 2፡10፤ 17፡14፤ 2ጢሞ 2፡2) ሙሴ – ዘኁ 12፡7፣ ዳንኤል – ዳን 6፡4፣ ኤጳፍራ፣ ቲኪቆስ፣ አናሲስም – ቆላ 1፡7፤ 4፡7፣ 9፣ ዳዊት – 1ሳሙ 22፡14፣ ኢየሱስ – ራዕ 19፡11 – እግዚአብሔር ታማኞችን ይጠብቃል – መዝ 31፡23 – የእግዚአብሔር አይኖች በታማኞች ላይ ነው – መዝ 101፡6 – እግዚአብሔር ታማኝ ባሪያን ይሸልማል – ማቴ 25፡21 ሰ) ለጋስ – እግዚአብሔር ይሰጣል ቅዱሳት መጻሕፍትን – 2ጢሞ 3፡16 አንድያ ልጁን – ዮሐ 3፡16፤ ሮሜ 8፡32 መንፈስ ቅዱስን – ሉቃስ 11፡13፤ 1ተሰ4፡8፤ ሮሜ 5፡5 ንስሃን – 2ጢሞ 2፡25 የዘላለም ህይወት ስጦታን – ሮሜ 6፡23፤ 1ዮሐ 5፡11 ለትሁታን ጸጋን – 1ጴጥ 5፡5፤ ያዕ 1፡5 ለደካማው እረፍትን – ማቴ 11፡28 ጥበብን – ዳን 2፡23፤ ያዕ 1፡5 በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ድልን – 1ቆሮ 15፡57 የማገልገል ብቃትን – 1ጴጥ 4፡11፤ ኤፌ 3፡7 ለፍጥረት ሁሉ ምግብን – መዝ 136፡25 ኅ ብት የማፍራት ችሎታን – ዘዳ 8፡18 ለምድራዊ ገዢዎች ስልጣንን – ዳን 2፡37 – ከእግዚአብሔር የልግስና ባሕሪ ልንካፈል ይገባል። መስጠት የሚለውን ክፍል በተጨማሪ ይመልከቱ – ክፍል ሰ8 ሸ) የእግዚአብሔር ታላቅነት ሁሉን አዋቂ – በሁሉ ስፍራ የሚገኝ – ሁሉን ማድረግ የሚችል – ዘላለማዊ – የማይለወጥ ቀ) እግዚአብሔር ጠቢብ፣ ሁሉን አዋቂ ነው – ሮሜ 16፡27 – እግዚአብሔር አዋቂ ጌታ ነው – 1ሳሙ 2፡3 – ጥበቡ ጥልቅ ናት – ኢዮብ 9፡4 – ከሰው መረዳት በላይ ነው – መዝ 139፡4-6፤ ሮሜ 11፡33 – የእግዚአብሔር ጥበብ ባሕርይ – ያዕ 3፡17 ንጹሕ – ከሃሰት ጋር የማይቀየጥ ሰላማዊ – ጠብን የማይጭር ጨዋ – አስቸጋሪ/የማይመች ወይም ግትር ያልሆነ መኀሪ – ሕግን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ፍቅር የሚገልጥ የማያዳላ – ለራስ ወይም ለወገኔ ይጠቅማል በሚል የማይሰራ ግብዝነት የሌለበት – የሚለውን የሆነ – እግዚአብሔርዊ ያልሆነ ጥበብ ባሕሪይ አለማዊ፣ ሥጋዊ፣ የአጋንንት ጥበብ – ያዕ 3፡14-16 ለእግዚአብሔር ሞኝነት የሆነ – 1ቆሮ 3፡18-20 – ለአማኞች ጥበብ ተዘጋጅቷል – ያዕ 1፡5-7፤ ቆላ 1፡9፤ ኤፌ 1፡17 ክርስቶስ ጥበባችን ነው – 1ቆሮ 1፡24፤ ቆላ 2፡2 የክርስቶ ቃል ጥበባችን ነው – ቆላ 3፡16 – የጥበብ ቃል መንፈሳዊ ስጦታ – ክፍል ረ11 በ) እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ በአንድ ጊዜ ይገኛል – መዝ 139፡7-12 – ስለዚህ በየትኛውም ስፍራ ብንጸልይ እርሱ ይሰማናል፡፡ – ሁሉን ነገር በሁሉ ረገድ ይሞላል – ኤፌ 1፡22-23 – ከማናችንም ሩቅ አይደለም – ሐዋ 17፡27-28፤ ኤር 23፡23 – በሲኦል፣ በሰማይ – መዝ 139፡8፤ ዓሞጽ 9፡2-3 – ከእርሱ ልንደበቅ አንችልም – ኤር 23፡24 – ይህ ማለት እግዚአብሔር በሁሉም ነገር ውስጥ አለበት ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ሰዎች በሚከተሉት ነገሮች ሲወቅሳቸው እናነባለን፡ ጣኦትንና ዲያብሎስን ሲያመልኩ – ኢሳ 2፡8-11፤ 20-21፤ ራዕ 9፡20 የተፈጠሩትን ሲያመልኩ – ሮሜ 1፡25 መላዕክትን ሲያመልኩ – ቆላ 2፡18፤ ራዕ 22፡8-9 የሙታን መናፍስትን ሲያመልኩ – ዘሌ 20፡6፤ ዘጻ 18፡9-11፤ ኢሳ 8፡19 – ማስታወሻ፡ በድፍረት መጸለይ እንችላለን – ኤር 33፡3 ተ) እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነው – እርሱ የሰማያትና የምድር ፈጣሪ ነው – ዘፍ 1፡1 – ሁሉም ነገር በአንድ ላይ ተያይዞ የጸናው በእርሱ ነው – ቆላ 1፡17 – ሃይሉ ታላቅ ነው – ኢዮብ 9፡4 – ስለዚህ ሊያድንና ሊታደግ ይችላል – ኢሳ 50፡2 – ሁሉ ለእግዚአብሔር ይቻላል – ማቴ 19፡26፤ ኤር 32፡17 – ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን? – ኤር 32፡27 – የእግዚአብሔር ድካም ከሰዎች ብርታት ይበረታል – 1ቆሮ 1፡25 – ሃይሉን ልንካፈል ይገባል – ኢዮ 3፡10፤ 2ቆሮ 12፡10፤ ዕብ 11፡34 – በእግዚአብሔር ጸጋ ልንበረታ ይገባል – 2ጢሞ 2፡1 – በሃይ ልንበረታ ይገባል – ኤፌ 6፡10 – ሰይጣንን ለመርታት ልንበረታ ይገባል – 2ቆሮ 10፡3-5 – በእምነት ልንበረታ ይገባል – ሮሜ 4፡20 – ለመበርታትና ለመበዝበዝ – ዳን 11፡32 ቸ) እግዚአብሔር ዘላለማዊ ነው – 1ዮሐ 5፡20 – ከዘላለም እስከዘላለም – መዝ 90፡1-2 – መጀመሪያና መጨረሻ – ራዕ 22፡13 – ያለ፣ የነበረና፣ የሚመጣው – ራዕ 1፡8 – ከእርሱ በፊትና በኃላ ምንም የለም – ኢሳ 43፡10 – ዘላለማዊ ሕይወቱን መካፈል እንችላለን – ዮሐ 3፡15-16፤ ሮሜ 6፡23፤ 1ዮሐ 5፡11-13 – የሰጠነውን አደራ ይጠብቃል – 2ጢሞ 1፡12 ነ) እግዚአብሔር አይለወጥም – ሚል 3፡6 – ስለዚህ የፍቅር ስጦታው ሊታመን ይችላል፡፡ – ኢየሱስ ክርስቶስ ትላንትና፣ ዛሬ፣ ወደፊት ያው ነው – ዕብ 13፡8 – በእርሱ ዘንድ መለዋወጥ የለም – ዕብ 1፡17 – እርሱን ለመምሰል መለወጥ አለብን – 1ዮሐ 3፡2፤ 1ቆሮ 15፡51-53

የእግዚአብሔር ባሕሪይ Read More »