የእግዚአብሔር ስራ (ምግባሩ) ምነድን ነው?

ሀ) መግቢያ – በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማያትን ፈጠረ – ዘፍ 1፡1 ይህ የሆነው ምናልባት መላዕክት በተፈጠሩበት ጊዜ ሊሆን ይችላል፡፡ – የምድርና ቅርብ ያሉ ሰማያት መፈጠር – ዘፍ 1፡1-31 ይህ ስለምድርና አካባቢዎ ስላሉ ፍጥረታት ይመለከታል ለ) የፍጥረት ልደት – እግዚአብሔር አጽናፈ አለሙን ካለመኖረ ወደ መኖር አመጣ – ዘፍ 1፡1፤ ኢሳ 42፡5፤ ዓሞጽ 5፡8 እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ደግሞ ሊያበጅ ይችላል (ያበጃልም) – አሳ 65፡17፤ ራዕ 21፡1 – የተፈጠረው ነገር ሲፈጠር እጅግ መልካም ነበር – ዘፍ 1፡31 የክፋት ችግር ከዚህ የፍጥረት ልደት በኋላ የመጣ ነው የክፋት ችግር ከሰው እንጂ ከእግዚአብሔር አልመጣም – የፍጥረት ባለቤት አብ – ሮሜ 11፡36 ወልድ፣ ቃሉ – ዮሐ 1፡1-3 መንፈስ ቅዱስ – ዘፍ 1፡2 – በምድር ለሚኖሩ ሕዝቦች እስትንፋስን የፈጠረ እግዚአብሔር ነው – ኢሳ 42፡5፤ ዘካ 12፡1 – መንፈሳዊ ሃይላትንና ስልጣናትን የፈጠረው እግዚአብሔር ነው – ቆላ 1፡16-17 እግዚአብሔር ብቻውን መናፍስትን ሊያጠፋ ይችላል – ማቴ 10፡28፤ ሉቃስ 12፡4-5 – እግዚአብሔር በአፉ ቃል ፈጠረ – ዘፍ 1፡3፤ መዝ33፡6፣ 9፤ ዕብ 11፡3 እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ፣ አላማና ጥበብ – ኤፌ 1፡11፤ ራዕ 4፡11 – እግዚአብሔር የሁሉ ነገር ፈጣሪ ስለሆነ፣ ከዋክብትን፣ መናፍስትን፣ ጣኦትን፣ ሰዎችን፣ እፅዋትን ወይም እንስሳትን ልናመልካቸው አይገባም – ሮሜ 1፡20-25 ሐ) መግቦቱና መገኘቱ አይቋረጥም – እግዚአብሔር ሁሉን ነገር በቃሉ ደግፎ ይይዛል – ዕብ 1፡3 – እርሱ ለሁላችንም ቅርብ ነው – ሐዋ 17፡27-28 በተለይም ለአማኞች ግድ ይለዋል – ዕብ 13፡5 እንደያዕቆብ፣ መገኘቱን ላናስተውል እንችላለን – ዘፍ 28፡16 – የምንኖረው በእግዚአብሔር ያልተቋረጠ መግቦት ነው – መዝ 36፡6 – እግዚአብሔር ፍላጎቶችን ይሞላል – መዝ 23፡1-6፤ 147፡1-9፤ 1ጴጥ 5፡6-7፤ ማቴ 5፡45፤ 6፡25-34፤ ሐዋ 14፡17 – እግዚአብሔር ይጠብቀናል ያድነናል – ዘፍ 28፡15፤ ዘዳ 32፡11፤ ኢሳ 25፡4፤ ማቴ 23፡37፤ ዮሐ 17፡11፤ ፊል 4፡6-7፤ 2ተሰ 3፡3፤ ይሁዳ 24-2 – እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ ከተፈጥሮ ሥርዐት ውጪ በተአምራት ይሰራል – ክፍል ለ2 መ) እግዚአብሔር ድነትን ለሁሉ አቅርቧል – ክፍል ሠ ሠ) እግዚአብሔር በሚከተሉት መልኮች ከሰው ልጅ ጋር ሕብረት ማድረጉን አላቋረጠም፡ – እንደ አባት – የእግዚአብሔር አባትነት የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ለ7 – እንደ ፈጣሪ – የፍጥረት ልደት የሚለውን ይመልቱ – እንደ ባል – ለእስራኤል – ኤር 3፡20 – እንደ ንጉስ – የእግዚአብሔር መንግስት የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል መ6 – እንደ ፈራጅ – ሞትና የመጨረሻው ዘመን የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ሸ – እንደ አዳኝ – ደኅንነት የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ሠ – እንደ መምህር – መንፈስ ቅዱስ/የእግዚአብሔር ቃል የሚለውን ይመልቱ – ክፍል ለ12 እና ለ13 – እንደሙሽራና ባል – ሞትና የመጨረሻው ዘመን የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ሸ ረ) እግዚአብሔር ሰማያትና እና ምድርን ዳግመኛ ይፈጥራል – ራዕ 21፡5 – የመጀመሪያው ሰማይና የመጀመሪያው ምድር ይጠፋሉ – ራዕ 21፡1 – አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር – ራዕ 21፡1፣ 5፤ ኢሳ 65፡17 – በእዚያ ሃዘን፣ ሞትና በሽታ የሉም – ራዕ 21፡4 – እኛም ኢየሱስን እንመስላለን – 1ዮሐ 3፡2

የእግዚአብሔር ስራ (ምግባሩ) ምነድን ነው? Read More »