ወደ ቆላስይስ ሰዎች

በቤትና በሥራ ቦታ መንፈሳዊ ግንኙነቶችን መጠበቅ (ቆላ. 3፡18-4፡18)

ክርስትና የግለሰብ ወይም የቤት ውስጥ እምነት ብቻ አይደለም። የአንድ ግለሰብ መላ ሁለንተና ሌላውን ይገነባል። ስለሆነም፥ ጳውሎስ ሰዎች እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ ይመላለሱ ዘንድ ከማኅበራዊ ነገሮች አንዳንድ ማብራሪያዎችን ይሰጣል። ሀ. በቤት ውስጥ፥ ሚስቶች ተገዥዎች፥ ባሎች አፍቃሪዎች፥ እንዲሁም ልጆች ታዛዦች ሊሆኑ ይገባል። ለ. በሥራ ቦታ፥ ባሪያዎች (ሠራተኞች) እግዚአብሔርን ለማስደሰት በማሰብ በትጋት መሥራት ይኖርባቸዋል። ለሰብአዊ ጌቶቻቸው የሚሠሩ ቢመስልም፥ ለመለኮታዊ […]

በቤትና በሥራ ቦታ መንፈሳዊ ግንኙነቶችን መጠበቅ (ቆላ. 3፡18-4፡18) Read More »

የተቀደሰ አኗኗር (ቆላ. 3፡1-17)

አንድ ጊዜ አንድ መምህር ለስኬታማ ክርስቲያናዊ ሕይወት ምሥጢሩ በሕይወታችን እውነቶችን ሚዛናዊ ማድረግ ነው ብሎ ነበር። ብዙውን ጊዜ የተሳሳተ ልምምድና ትምህርት የሚከሠተው አንድን እውነት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሚገኙ ሌሎች እውነቶች ጋር ሚዛናዊ ከማድረግ ይልቅ እንደ ዋነኛ እውነት አድርገን ስንወስደው ነው። ይህንን በብዙ መንገዶች መመልከት ይቻላል። በልሣን መናገር መንፈሳዊ ስጦታ መሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተመልክቷል። ነገር ግን

የተቀደሰ አኗኗር (ቆላ. 3፡1-17) Read More »

አማኞች ከንቱ ሰብአዊ ትምህርቶችን ከመከተል ይልቅ በክርስቶስ ላይ ማተኮር ይኖርባቸዋል (ቆላ. 2፡6-23)

አሁን ደግሞ ጳውሎስ በሐሰተኛ ትምህርቶች ላይ ያተኩራል። እነዚህንም ትምህርቶች ጳውሎስ፥ እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ያለ ፍልስፍናን ከንቱ መታለል» ሲል ይገልጻል። አማኞች በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲያድጉ ያበረታታቸዋል። ሥር እንደሌላቸውና ማዕበል በተነሣ ጊዜ እንደሚወድቁ ዛፎች ከመሆን ይልቅ ከክርስቶስ ጋር ጥልቅ የእውቀትና የግንኙነት ሥሮች ልንይዝ ይገባል። መጀመሪያ ባመንን ጊዜ ባገኘነው እውነት

አማኞች ከንቱ ሰብአዊ ትምህርቶችን ከመከተል ይልቅ በክርስቶስ ላይ ማተኮር ይኖርባቸዋል (ቆላ. 2፡6-23) Read More »

ክርስቶስ ጳውሎስ የሚያስተምረው የወንጌል መልእክት እምብርት ነው (ቆላ. 1፡24-2፡5)

ኖስቲኮች ሰው ከክፉ ዓለም ለማምለጥ ሊያከናውናቸው ይገባል ከሚሏቸው ምሥጢራዊ እውነቶች በተቃራኒ፥ ጳውሎስ ግልጽ የወንጌል እውነቶችን ሰብኳል። ለመሆኑ የዚህ ወንጌል መሠረቱ ምንድን ነው? የወንጌል ትኩረቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ጳውሎስ በዚህ ክፍል ውስጥ በሚከተሉት ነገሮች ላይ አጽንኦት ይሰጣል። ሀ. ጳውሎስ ወንጌሉን የመስበክ ቀዳማዊ ተልዕኮ ያለው የክርስቶስ አገልጋይ ነው። ይህ ተልዕኮ መከራ መቀበልን ይጨምር ነበር። ጳውሎስ በዚህ ጊዜ

ክርስቶስ ጳውሎስ የሚያስተምረው የወንጌል መልእክት እምብርት ነው (ቆላ. 1፡24-2፡5) Read More »

ክርስቶስ ከተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ የበለጠና እንደ እግዚአብሔር አብ ያለ አምላክ ነው (ቆላ. 1፡15-23)

ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች እንደ ፈውስ፥ በልሳን መናገር፥ ቁሳዊ ሀብት፥ መንፈሳዊ ያደርጉናል ብለው በሚያስቧቸው መንፈሳዊ ነገሮች ላይ ሲያተኩሩ፥ ወይም በሐሰት ትምህርት ሲወሰዱ ምን ይከሰታል? በዚህ ጊዜ ክርስቶስን ሳይሆን ሰዎችን (ራሳቸውን ወይም ሌሎች)፥ ወይም የዓለምን ነገሮች ይመለከታሉ። የቆላስይስ ክርስቲያኖች አንዳንድ ስዎች ጠቃሚዎች ናቸው ያሏቸውን ነገሮች ይመለከቱ ነበር። አንዳንዶች የተወሰኑ ሕግጋትን ወይም ደንቦችን መጠበቃቸው ወሳኝ እንደሆነ ይነግሯቸዋል። ሌሎች

ክርስቶስ ከተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ የበለጠና እንደ እግዚአብሔር አብ ያለ አምላክ ነው (ቆላ. 1፡15-23) Read More »

ጳውሎስ ስለ ቆላስይስ ክርስቲያኖች ያቀረበው ምስጋናና ጸሎት (ቆላ. 1፡1-14)

«ይህ ታላቅ ጀማ ስብከት ወንጌል እንዳያመልጥዎ። በጉባኤው ላይ ታላቅ የፈውስ አገልጋይ ይጋበዛል። ማንኛውም ዓይነት በሽታ ያለበት ሰው ከበሽታው ይፈወሳል»። «ይህ ከአያት ቅድማያቶቻችን ያገኘነው ሃይማኖት ነው። ስለሆነም እንከተለዋለን።» «ዶ/ር እገሌ ሦስት ዲግሪዎች ያሉት ዝነኛ የዩኒቨርስቲ ሌክቸረር ነው። ትምህርቱን መስማት አለብን።» ዓለም ቀልባችንን በሚስቡ ድምፆች የተሞላች ነች። ሁሉም እንድንሰማቸው ይፈልጋሉ። «እኛ ምሥጢር አለንና። እኛ ጥሩውንና ትክክለኛውን እናውቃለን»

ጳውሎስ ስለ ቆላስይስ ክርስቲያኖች ያቀረበው ምስጋናና ጸሎት (ቆላ. 1፡1-14) Read More »

የቆላስይስ መጽሐፍ ዓላማ፣ ልዩ ባሕሪያት፣ መዋቅርና አስተዋጽኦ

፩. የቆላስይስ መጽሐፍ ዓላማ የመጀመሪያው ዓላማ፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የተነሣውን የሐሰት ትምህርት መመከት። ጳውሎስ በኤፌሶን ካገለገለ ስምንት ዓመታት ያህል አልፈዋል። በዚህ ጊዜ በቆላስይስ ክርስቲያኖች እምነት ውስጥ መጠነኛ ለውጥ ተከስቷል። በክርስቶስ ላይ የነበራቸውን እምነት ባይክዱም፥ የይሁዲና በትንሹ እስያ የተለመዱ ፍልስፍናዎችን የቀየጡበት ይመስላል። ይህ የሌሎችን እምነቶች የመጨመር ተግባር ወንጌሉን ስለሚለውጥ አደገኛ ነው። ይህም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የይሁዲነት

የቆላስይስ መጽሐፍ ዓላማ፣ ልዩ ባሕሪያት፣ መዋቅርና አስተዋጽኦ Read More »

የቆላስይስ መልእክት በማን ተጻፈ፣ ለማን ተጻፈ፣ የተጻፈበት ዘመንና ቦታ

፩. የቆላስይስ መልእክት ጸሐፊ የውይይት ጥያቄ፡- ቆላ. 1፡1-2 አንብብ። ሀ) ጸሐፊው ማን ነው? ለ) ጸሐፊው ራሱን የሚገልጸው እንዴት ነው? ይህ ከፊልጵ. 1፡1 የሚለየው እንዴት ነው? ሐ) መልእክቱን የጻፈው ለማን ነው? የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ቆላስይስ ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብ። ስለ መጽሐፉ ጸሐፊ፥ ስለ ከተማይቱ፥ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱና ስለ መጽሐፉ የተሰጠውን ትምህርት ጠቅለል አድርገህ ጻፍ። ጳውሎስ

የቆላስይስ መልእክት በማን ተጻፈ፣ ለማን ተጻፈ፣ የተጻፈበት ዘመንና ቦታ Read More »

የቆላስይስ መልእክት መግቢያ

አንድ ሳይንቲስት በእንቁራሪት ላይ ምርምር አደረገ። መጀመሪያ ውኃ አፈላና እንቁራሪቷን እዚያው ውስጥ ጨመራት። ውኃው በነካት ጊዜ እንቁራሪቷ ትዘል ጀመር። የፈላው ውኃ ሲያቃጥላትም አልሞተችም። ሌላዋን እንቁራሪት ደግሞ በቀዝቃዛ ውኃ ውስጥ ጨመራት። የውኃውና የእንቁራሪቱ የሙቀት መጠን ተመጣጣኝ ስለነበር ይህችኛዋ እንቁራሪት ሳትዘል ዝም ብላ ተቀመጠች። ከዚያም ላይንቲስቱ ቀዝቃዛውን ውኃ እዚያው ውስጥ ካለችው እንቁራሪት ጋር አነስተኛ ሙቀት ባለው ምድጃ

የቆላስይስ መልእክት መግቢያ Read More »