የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

ትንቢተ ኢዮኤል

የትንቢተ ኢዩኤል ዓላማ እና ዐበይት የሥነ መለኮት ትምሕርቶች

የትንቢተ ኢዩኤል ዓላማ ብዙ ጊዜ የነቢያት ዓላማ ወደፊት ስለሚሆኑ ነገሮች መተንበይ እንደሆነ እንገምታለን። ምንም እንኳ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ስለ መጪው ጊዚያት የተነበዩ ቢሆኑም፥ የመልእክታቸው አብዛኛው ክፍል በዘመኑ የነበሩትን ሰዎች የሚመለከት ነበር። ነቢያት የእግዚአብሔር ሕዝብ በክፋታቸው ተጸጽተው ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ የሚለምኑ የእግዚአብሔር ቃል አቀባዮች ነበሩ። ትንቢቶቹ የሚነገሩት ብዙውን ጊዜ የሕዝቡን አደራረግ ውጤቶች ለማመልከት ነበር። የትንቢት ዓላማ ስለ መጪው ጊዜ ብዙ እንድናውቅ ሳይሆን፥ እግዚአብሔር አሁንና ወደፊት በሚያደርጋቸው ነገሮች ምክንያት አሁን ያለውን ኑሮአችንንና አካሄዳችንን እንድንለውጥ ለማድረግ ነው። እግዚአብሔር ነቢዩ ኢዩኤልን ወደ ይሁዳ የላከው፥ ለእግዚአብሔር ባለመታዘዛቸው ምክንያት የሚደርሱባቸውን ነገሮች በመዘርዘር ሊያስጠነቅቃቸው ነበር። የአንበጣው መቅሠፍት እግዚአብሔር በእነርሱ ደስ አለመሰኘቱን የሚያሳይ ምልክት መሆኑን በመጥቀስ አስጠነቀቃቸው። በንስሐ ካልተመለሱ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ታላቅ መቅሠፍት ለማምጣት፥ በንስሐ ከተመለሱ ግን እንደገና ምድራቸውን ለመባረክ ቃል ገብቶ ነበር። እንዲሁም ኢዩኤል የአንበጣውን መቅሠፍት ይሁዳን ለመውረር የሚመጣ የሌላ ጦር ኃይል ምልክት አድርጎ ተጠቅሞበታል። ይህ ጦር ስለ ባቢሎን ወይም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ከመመለሱ ጥቂት ቀደም ብሉ ስለሚመጣ ሌላ ጦር የሚናገር ሊሆን ይችላል። በይሁዳ ላይ የሚመጣው ጦር የአንበጣ መንጋን ያህል እጅግ አጥፊና ብዙ ሊሆን ይችላል። እግዚአብሔር ግን ሕዝቡን በመታደግ፥ እነርሱ የማያውቁአቸውን በረከቶች ያመጣላቸዋል። መንፈስ ቅዱስ በሕዝብ ሁሉ ላይ ይወርዳል። ይህ የመጨረሻ ዘመን እግዚአብሔር ምድርን ከክፋት የሚያጠራበትና በአሕዛብ ሁሉ ላይ የሚፈርድበት ስለሆነ የታላቅ ጥፋት ቀንም ይሆናል። የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) እግዚአብሔር ንስሐ እንድንገባ እኛንና አገራችንን በሚያስጠነቅቀን ወቅት በሕይወታችንና በአገራችን ላይ የሚመጣውን የማስጠንቀቂያ ጥፋት መገንዘብ ጠቃሚ የሚሆነው ለምንድን ነው? ለ) ከርስቲያኖች ከፍተኛ ጥፋት የሚደርስበትንና ታላቅ በረከት የሚያመጣውን የመጨረሻውን ዘመን በንቃት መገንዘባችን ጠቃሚ የሚሆነው በምን መንገድ ነው? ሐ) ይህ ነገር በአኗኗራችን ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድረው እንዴት ነው? በትንቢተ ኢዩኤል ውስጥ የሚገኙ ዐበይት የሥነ-መለኮት ትምህርቶች 1) ክርስቲያን ስለተለያዩ አደጋዎች ያለው ግንዛቤ  ሰዎች የተለያዩ አደጋዎችን በሚመለከቱበት ጊዜ በአመዛኙ ምላሻቸው ከሚከተሉት ሦስት አሳቦች አንዱ ይሆናል፡- ሀ) በተለይ በምዕራቡ ዓለም እግዚአብሔር የተለያዩ አደጋዎችን በምንም ዓይነት እንደ ማይቆጣጠራቸው አድርጎ ማሰብ የተለመደ ነው። በሕዝቡ ላይ ያለምንም ዓላማ በድንገት የሚመጡ ነገሮች ስለሆኑ፥ እኛ ማድረግ የምንችለው ነገር ቢኖር እስኪያልፉ ድረስ መታገሥ ብቻ ነው ይላሉ።  ለ) ብዙ ክርስቲያኖች ወይም ሙስሊሞች የተፈጥሮ አደጋዎች በቀጥታ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሚመጡ ያምናሉ። ነገር ግን እነዚህ ነገሮች የሚከሠቱት ያለምንም ዓላማ ነው የሚል እምነት አላቸው። እግዚአብሔር እነዚህ ሁኔታዎች እንዲከሠቱ የሚያደርግበትን ምክንያት ሰዎች ሊያውቁ እንደማይችሉ ይናገራሉ። ስለዚህ ማድረግ የምንችለው ነገር ቢኖር፥ እነዚህን ነገሮች እግዚአብሔር እንደሚያደርጋቸውና እኛም ምንም የምንለውጠው ነገር ስለሌለ አሜን ብሎ መቀበል ነው ይላሉ።  ሐ) እግዚአብሔር የራሱን ዓላማ ለመፈጸም በሕይወታችንና በአገራችን ላይ የሚደርሱትን ነገሮች ሁሉ እንደሚመራ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል። ዝናም፥ ፀሐይ፥ ሰብሎች ቁሳዊ ሀብትና የመሳሰሉት መልካም ነገሮች ሁሉ የሚመጡት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ይሁን እንጂ አደጋዎች ወይም ችግሮች የሚመጡት በእርሱ ፈቃድ ነው። የሚመጡትም ያለ ዓላማ ሳይሆን፥ እግዚአብሔር በሚያውቀው ዓላማ ነው። የሁሉ ነገር ኃላፊ እግዚአብሔር ስለሆነ እርሱን ማሰብ ለእኛም ሆነ ለአገራችን እንደሚያስፈልገን ለማሳሰብና ለመርዳት ነው። ስለሚሰጠን በረከቶች እግዚአብሔርን ልናመሰግነውና በችግራችን ጊዜ ልናስበው ይገባናል። ችግሮች እግዚአብሔርን በማወቅና በመንፈሳዊ ባሕርይ እንድናድግ ሊረዱን የሚከሰቱ ናቸው። እግዚአብሔር አደጋ የሚያመጣባቸውን ምክንያቶች ሁሉ ለማወቅ ባንችልም፥ የሚመጡት በእግዚአብሔር ቁጣና ምሕረት የለሽ ፍርድ ሳይሆን፥ በእግዚአብሔር ፍቅርና ምሕረት ጭምር እንደሆነ እናውቃለን። የሚመጣውን በረከትና አደጋ የሚቆጣጠር እግዚአብሔር እንደሆነ ብናውቅም፥ የበረከትን ወይም የአደጋን መኖር እግዚአብሔር በአንድ ሰው ሕይወት ወይም በአንዲት አገር ላይ ፍቅሩ ወይም ፍርዱ እንዲገለጽ የሚጠቀምበት መሣሪያ እንደሆነ ለመወሰን እንዳንጠቀምበት ልንጠነቀቅ ይገባል። እጅግ ሀብታሞች የሆኑ ክፉና ኃጢአተኞች ሰዎች ወይም አገሮች ብዙ ናቸው። በመከራና በችግር ውስጥ የሚያልፉ ብዙ የእግዚአብሔር ሰዎች አሉ። በአንድ ሰው ወይም በአንድ አገር ሕዝብ ክፋት ወይም በጎነት ምክንያት መቅሠፍት ወይም በረከት ይደርሳል ብሎ መወሰኑ የእኛ ድርሻ አይደለም። የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) በእነዚህ ሦስት መንገዶች መቅሠፍት የደረሰባቸው ሰዎች ምን እንዳደረጉ የሚገልጽ ታሪክ በምሳሌነት ጥቀስ። ለ) በሕይወትህ ለገጠሙህ የተለያዩ ችግሮች ምላሽ የሰጠህባቸውን የተለያዩ መንገዶች ጥቀስ። ከእነዚህ ምላሾችህ መካከል ዕድገት ያስገኙልህ የትኞቹ ናቸው? ምንም ዕድገት ያላስገኙትስ? 2. የጌታ ቀን  የውይይት ጥያቄ፥ ኢዩኤል 1፡15፤ 2፡1-2፤ 3፡18 አንብብ። ሀ) የጌታን ቀን የተለያዩ ባሕርያት ግለጽ። ለ) ይህንን ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ውስጥ በመመልከት የጌታ ቀን ምን እንደሆነ የሚገልጽ አጠር ያለ አንቀጽ ጻፍ። የብሉይ ኪዳን ነቢያት በሰፊው ከተጠቀሙባቸው ሐረጎች አንቱ «የጌታ ቀን» የሚለው ነው። አይሁድ አንዳንድ ዐበይት ድርጊቶች የተፈጸሙባቸውን ጊዜያት «ቀን» በማለት ይጠሩአቸው ነበር። ነቢያት «የጌታ ቀን» ብለው የጠሯቸው ቀናት እግዚአብሔር በሰዎች ታሪክ ውስጥ ጣልቃ በመግባት ታላቅና ኃይለኛ ተግባር የፈጸመባቸው ማንኛዎቹም ቀናት ነበሩ። አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ የፈረደባቸው ቀናት «የጌታ ቀን» ተብለዋል (ሰቆቃወ ኤርምያስ 2፡22)። በሌሉች ጊዜያት ደግሞ እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ ወደፊት የሚፈርድባቸው ጊዜያት «የጌታ ቀን» ተብለዋል (ኢዩኤል 2፡1-11)። እንደዚሁም ይህንን ሐረግ በዓለም ታሪክ መጨረሻ ገደማ የሚፈጸሙትን ታላላቅ ድርጊቶች ለመግለጥ ተጠቅመውባቸዋል። ነቢያት እግዚአብሔር ከዚህ ቀደም አድርጎት የማያውቀውን ነገር የሚያደርግበት ጊዜ እንደሚመጣ ነቢያት አመልክተዋል። አንዳንዴ ይህ ጊዜ የሚያመለክተው ክርስቶስ በመስቀል ላይ ለመሞት የመጣበትን ወቅት ነው። በሌላ ጊዜ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚነግሥበትን ዳግም ምጽአቱን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሁለት የክርስቶስ ምጽአቶች በግልጽ ሳይለዩ በአንድነት ተጠቅሰዋል። አንዳንድ ጊዜ ነቢያቱ የእስራኤል ሕዝብ ይለማመዱት የነበረውን ታሪካዊ ድርጊት በማየት፥ በመጨረሻው ዘመን የሚመጣውን ታላቁን የጌታ ቀን እንደሚያመለክት አድርገው ይጠቀሙበታል (ኢሳይያስ 13፡5-10)። ከጌታ ቀን ባሕርያት ውስጥ ጥቂቶቹ እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡- ሀ. የጌታ ቀን በጨለማ፥ ደብዘዝ ባለ ብርሃንና በፍርድ ባሕርዩ ይታወቃል። (ኢሳይያስ 13፡9-10፤ ማቴዎስ 24፡29)።  ለ. የጌታ ቀን እንደ መሬት መንቀጥቀጥና ረሀብ ባሉ የተፈጥሮ አደጋዎች ይሞላል።  ሐ. የጌታ ቀን የጦርነት ጊዜ ይሆናል፥ ሕዝብ በሕዝብ ላይ፥ በተለይም በእስራኤል ሕዝብ ላይ በመነሣቱ ይታወቃል፡፡  መ. የጌታ ቀን እግዚአብሔር በአሕዛብ ሁሉ ላይ የሚፈርድበት ቀን ይሆናል (ኢዩኤል 3፡19)።  ሠ. የጌታ ቀን የእስራኤል ሕዝብ በብዛት ወደ እግዚአብሔር የሚመለሱበት ቀን ነው። እነዚህ ቅሬታዎች ከእግዚአብሔር ከፍተኛ በረከትን ያገኛሉ (ኢዩኤል 2፡32፤ አሞጽ 9፡11-15)።  ረ. የጌታ ቀን ከዚህ በፊት በጭራሽ ተደርጎ በማያውቅ አኳኋን የእግዚአብሔር መንፈስ በእያንዳንዱ ሰው ሕይወት ውስጥ የሚሠራበት ጊዜ ይሆናል፤ (ኢዩኤል 2፡28)።  ሰ. የጌታ ቀን ምድር በቃል ሊገለጽ የማይችል ታላቅ በረከትና ብልጽግና የምትለማመድበት ጊዜ ይሆናል (ኢዩኤል 3፡18)።  ሸ. የጌታ ቀን ምድር በእሳት ፍርድ የምትጠራበት ጊዜ ይሆናል (2ኛ ጴጥሮስ 3፡10-13)።  ቀ. የጌታ ቀን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚገለጥበት ጊዜ ይሆናል (1ኛ ቆሮንቶስ 1፡8) የውይይት ጥያቄ፥ ስለ ጌታ ቀን የተሰጠው ትምህርት ታላቅ ማስጠንቀቂያና ክርስቲያኖች በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠብቁት ጊዜ የሚሆነው እንዴት ነው?  የውይይት ጥያቄ፥ ኢዩኤል 1-3 አንብብ። ሀ) ኢዩኤል በእስራኤል ሕዝብ ላይ ፈጥኖ እንደሚደርስ የተናገረው ትንቢት ምን ነበር? ለ) ኢዩኤል ንስሐ እንዲገባ የሚያስጠነቅቀው ማንን ነበር? ሐ) ሕዝቡ ንስሐ ከገቡ በኋላ ተስፋ የተሰጣቸው በረከቶች ምን ነበሩ? መ) ለአይሁድ ስለ መጨረሻው ዘመን የተሰጡ የበረከት ተስፋዎች ምንድን ናቸው? 1. ኢዩኤል የጌታን ቀን በአንበጣ መቅሠፍት ተመለከተ (ኢዩኤል ) ትንቢተ ኢዩኤል፥ የእስራኤልን ምድር ሰብል ሙሉ በሙሉ ስላጠፋውና የይሁዳን ሕዝብ ሁሉ ችግር ላይ ስለጣለው የአንበጣ መቅሠፍት በማስረዳት ይጀምራል። ኢዩኤል ይህ የእግዚአብሔር ፍርድ መሆኑን በመገንዘብ፥ ሕዝቡ ሁሉ ንስሐ እንዲገቡ ይጋብዛል።  2. ኢዩኤል ስለሚመጣው የጌታ ቀን ተነበየ (ኢዩኤል 2፡3) የትንቢተ ኢዩኤል የመጨረሻ ግማሽ ክፍል ወደፊት ከረጅም ጊዜ በኋላ ስለሚሆነው ስለ ሌላ የጌታ ቀን ወደ መናገር ይመለሳል። በዚህ የትንቢተ ኢዩኤል ክፍል «ጣምራ ትንቢት»ን የሚያመለከቱ በርካታ መግለጫዎችን እናያለን። ይህም ሲባል እግዚአብሔር አንድን ትንቢት

የትንቢተ ኢዩኤል ዓላማ እና ዐበይት የሥነ መለኮት ትምሕርቶች Read More »

ትንቢተ ኢዩኤል መግቢያ

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ከዚህ ቀደም ያጋጠሙህን ጥፋቶች ወይም አስቸጋሪ ሁኔታዎች ዘርዝር። ለ) ከእነርሱ ምን ተማርህ? ሐ) በኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ በፊት የደረሱትን ጥፋቶች ዘርዝር። መ) ከእነዚህ ጥፋቶች ሰዎች መማር ያለባቸው ትምህርቶች ምንድን ናቸው? መጽሐፍ ቅዱስ፥ እግዚአብሔር በሕይወታችን የሚደርሱትን ክፉና በጎ ነገሮች ሁሉ እንደሚቆጣጠር ያስተምራል። እንደ ፀሐይና ዝናብ ያሉ በረከቶች የሚመጡት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው (ማቴዎስ 5፡44-45)። ደግሞም እግዚአብሔር ወደ ሕይወታችን የሚመጡትን አደጋዎች ሁሉ ይቆጣጠራል (ኢሳያይስ 45፡5-8 ተመልከት)። እኛ ወይም ከቤተሰቦቻችን አንዱ ሲታመም የምንወዳቸው በሞት ሲለዩን በአገራችን ድርቅ ሲኖር፥ እነዚህ ሁሉ እግዚአብሔር ለእኛ ካለው ፍቅር የተነሣ ሊመጡ ይችላሉ። እግዚአብሔር አደጋዎችን በተለያዩ መንገዶች በመጠቀም በሕይወታችን ምሕረቱን ያሳየናል። አደጋ እግዚአብሔር በኃጢአት ላይ እንደሚፈርድ በማሳየት የከፋ ፍርድ ከመምጣቱ በፊት ወደ እርሱ በንስሐ እንድንመለስ የሚጋብዝ ሊሆን ይችላል። ብዙ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን እንዲመረምሩና ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ይሄዱ እንደሆነ በማረጋገጥ ወደ ንስሐ እንዲመጡ ለማድረግ የሚያስጠነቅቅ ነው። አንዳንድ ጊዜ አደጋ እግዚአብሔር በእምነታችን ሊያጠነክረን ማለትም ጽናትን፥ ራስ መግዛትንና ሌሎችንም ጠቃሚ የሕይወት ብቃቶች መፈለጉን የሚያሳይ ምልክት ሊሆን ይችላል (ያዕቆብ 1፡2-4)። በኢዩኤል ዘመን እግዚአብሔር ታላቅ የአንበጣ መንጋ መቅሠፍት በእስራኤል ላይ አፈሰሰ። የምድሪቱ ሰብል ጠፋ። እንስሳት የሚግጡትን ሣር አጡ። ኢዩኤል ይህ የእግዚአብሔር ፍርድ መሆኑን ያውቅ ነበር። ስለዚህ የእግዚአብሔር ሕዝብ በንስሐ በመመለስ፥ በመታዘዝና በመቀደስ እንዲኖሩ ይለምናል። ችግሮችና አደጋዎች በሕይወታችን በሚከሰቱበት ጊዜ የእግዚአብሔር ዓላማ ምን እንደሆነ ለመረዳት ትልቅ ጥበብና የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ያስፈልገናል። ይህ የሚሆነው ለግል መንፈሳዊ ዕድገት ኃጢአትን ለመቅጣት ይሁን ወይም በእግዚአብሔር ላይ እንድንደገፍ ሊያስታውሰን በመፈለጉ፥ የምናውቀው እኛ ብቻ ነን። ሌሎች ሰዎች መከራን የሚቀበሉት ለምን እንደሆነ ከመፍረድ መጠንቀቅ አለብን። የእግዚአብሔር ዓላማ የተለያየ ስለሆነ፥ በሌሎች ላይ የምንፈርድ ወይም የመንፈስ ቅዱስን የመውቀስ ሥራ የምንሻማ መሆን የለብንም። ትንቢተ ኢዩኤል ለይሁዳ ከተጻፉ ሦስት አነስተኛ የነቢያት መጻሕፍት አንዱ ነው። ሚክያስና ሶፎንያስ ሁለቱም ለይሁዳ ሕዝብ የተጻፉ ነበሩ።  የትንቢተ ኢዩኤል ጸሐፊ በኢዩኡል 1፡1፥ «ወደ ባቱኤል ልጅ ወደ ኢዩኡል የመጣው ቃል ይህ ነው» ተብሉ በተገለጸው ቃል መሠረት ጸሐፊው ኢዩኤል እንደሆነ ይገመታል። ከዚህ ሌላ ስለ ኢዩኤል ማወቅ አስቸጋሪ ነው። ኢዩኤል በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተለመደ ስም ነበር። ቢሆንም በሌሎች ስፍራዎች የምናገኘው ይህ ስም የዚህ መጽሐፍ ጸሐፊ አይመስልም። ኢዩኤል የትና መቼ እንደተወለደና እንደኖረ አናውቅም። አብዛኞቹ ሊቃውንት ኢዩኤል በተደጋጋሚ የሚጠቅሰው ይሁዳንና ኢየሩሳሌምን ስለሆጎ (ኢዩኡል 2፡32፤ 3፡1፥6፥8) ከደቡብ፥ መንግሥት ከይሁዳ ነገድ ሳይሆን እንደማይቀር ይናገራሉ። ትንቢተ ኢዩኤል ከሌሎች የትንቢት መጻሕፍት በተለየ ሁኔታ ኢዩኤል ማገልገሉን አይገልጽም። የይሁዳም ሆነ የእስራኤል ንጉሥ አልተጠቀሱም። የተጠቀሱት ነገሥታት ሳይሆኑ ካህናት ብቻ ነበሩ። ስለዚህ መጽሐፉ የተጻፈው ብቁ የሆነ ንጉሥ ባልነበረበት ጊዜ ይመስላል። ትንቢተ ኢዩኤል መቼ እንደተጻፈ በርግጠኝነት ለመናገር የሚቻልበት መንገድ ጨርሶ የለም። ትንቢተ ኢዩኤል ስለተጻፈበት ጊዜ ምሁራን ሁለት አሳብ አላቸው፡-  1. ትንቢተ ኢዩኤል የተጻፈው ከ 835-830 ዓ.ዓ. ባለው ጊዜ ነበር። በዚህ ጊዜ የዳዊት ንጉሣዊ የዘር ግንድ በክፉዋ ንግሥት በጎቶልያ አማካይነት ጨርሶ ሊጠፋ ደርሶ ነበር። ኢዮአስ ብቻ ተርፎ ነበር። ኢዮአስ የሰባት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ በዙፋን ላይ ተቀመጠ። ኢዮአስ ንጉሥ ቢሆንም እንኳ ራሱን ችሎ እስኪያስተዳድር ድረስ አገሪቱ በካህናት ትመራ ነበር። እነዚህ ምሁራን ትንቢተ ኢዩኤል የተጻፈው በዚህ ጊዜ ነው ብለው የሚያምኑባቸው ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡- ሀ. አይሁድ ትንቢተ ኢዩኤልን ከታናናሽ ነቢያት መጻሕፍት መጀመሪያ አካባቢ ማድረጋቸው ልክ እንደ ትንቢተ ሆሴዕ ከምርኮ በፊት አንደተጻፈ ያምኑ እንደነበር የሚያሳይ ነው።  ለ. የአሦር ወይም የባቢሎን ስም አለመጠቀሱ፥ ታሪኩ ከእነዚህ ሁለት ታላላቅ መንግሥታት በፊት መፈጸሙን የሚያሳይ ነው።  ሐ. ኢዩኤል «የጌታ ቀን» የሚለውን ሐረግ የሚጠቀመው ከምርኮ በፊት ከተጻፉ መጻሐፍት ጋር በሚመሳሰል መንገድ ነው። ይህ አመላካከት እውነት ከሆነ፥ ትንቢተ ኢዩኤል ከመጽሐፍ ቅዱስ የትንቢት መጻሕፍት ሁሉ ቀዳሚ ይሆናል።  2. ሌሎች ምሁራን ደግሞ ትንቢተ ኢዩኤል የተጻፈው አይሁድ ተማርከው ከሄዱና ምርኮው ተፈጽሞ ወደ አገራቸው ከተመለሱ በኋላ ነው ብለው ያምናሉ። ከትንቢተ ሐጌና ዘካርያስ በኋላ ቢሆንም፥ ነገር ግን ከትንቢተ ሚልክያስ በፊት ተጽፏል የሚል አስተሳሰብ አላቸው። ትንቢተ ኢዩኤል የተጻፈበት ጊዜ ከ525-475 ዓ.ዓ. ነው ብለው ይገምታሉ። ይህም በጊዜ ቅደም ተከተል፥ ትንቢተ ኢዩኤልን ከብሉይ ኪዳን የትንቢት መጻሕፍት መካከል ከመጨረሻው መጽሐፍ ብቻ ቀዳሚ ያደርገዋል። ትንቢተ ኢዩኤል በዚህ ጊዜ እንደተጻፈ የሚያምኑ ምሁራን የሚከተሉትን ምክንያቶች ያቀርባሉ፡- ሀ. በትንቢተ ኢዩኤል 3፡1-2 የተጠቀሰው አሳብ፥ የእግዚአብሔር ሕዝብ መበተን ያለፈ ጉዳይ እንጂ ገና የሚመጣ መሆኑን የሚያመለክት አይመስልም።  ለ. ከምርኮ በፊት እጅግ ተደጋግሞ ይታይ የነበረው፥ ከምርኮ በኋላ ግን ያልተከሰተው የጣዖት አምልኮ ኃጢአት አልተጠቀሰም። ሐ. ከምርኮ በፊት በመካከለኛው ምሥራቅ ጨርሶ የማይታወቁ የነበሩት ግሪኮች ተጠቅሰዋል።  መ. የኢዩኤል አጻጻፍ ስልት ከኢየሩሳሌም ውድቀት በኋላ የተጻፉትን የታናናሽ ነቢያት መጻሕፍት እንጂ፥ የመጀመሪያዎቹን የነቢያት መጻሕፍት አይመስልም።  ሁለቱም አመለካከቶች የየራሳቸው የሆኑ ጠንካራ ጎኖች አሏቸው። እርግጥ ኢዩኤል ቀደም ሲል እንደተጻፈ የሚናገረው አመለካከት የተሻለ ቢመስልም፥ መቼ እንደተጻፈ አናውቅም ማለቱ ግን ከሁሉም የሚሻል ነው። ትንቢተ ኢዩኤል መቼ እንደተጻፈ አለማወቃችን ስለ መጽሐፉ የሚኖረንን ግንዛቤ ብዙ አይለውጠውም።  ታሪካዊ ሥረ መሠረት ትንቢተ ኢዩኤል የተጻፈበትን ጊዜ ስለማናውቅ ስለ መጽሐፉ ታሪካዊ ሥረ-መሠረት እርግጠኞች ለመሆን አንችልም። ስለዚህ መጽሐፉን በሚገባ ለመረዳት ሁለቱን የታሪክ ቅደም ተከተሎች መገንዘብ ጠቃሚ ነው።  1. የኢዮአስ ዘመነ መንግሥት (835-796 ዓ.ዓ.)  የውይይት ጥያቄ፥ የዚህን ጊዜ ታሪክ ለመረዳት 2ኛ ነገሥት 11 አንብብ። ሀ) የዳዊት የዘር ግንድ ምን ሊሆን ተቃርቦ ነበር? ለ) ንጉሥ ኢዮአስን ያሳደገው ማን ነው? ሐ) ንግሥት ጎቶልያ ምን ዓይነት ሴት ነበረች? ንጉሥ ኢዮራም ሲሞት ልጁ አካዝያስ ነገሠ። ይህ ሰው በእስራኤል ንጉሥ በኢዩ ከመገደሉ በፊት በሥልጣን ላይ የቆየው ለአንድ ዓመት ብቻ ነበር። ይህንን ሥልጣን ለመጨበጥ የደረሰ ሌላ ልጅ ስላልነበረ የኢዮራም ሚስት ጎቶልያ ዙፋኑን ያዘች። ዙፋኑን የሚወርስ ሌላ ሰው እንዳይኖር ወዲያውኑ የዳዊትን ዝርያዎች በሙሉ ለመግደል ሞከረች። ካህናቱ ኢዮአስ የተባለውን ሕፃን ብቻ አድነው ሰባት ዓመት እስኪሞላው ድረስ በቤተ መቅደስ ውስጥ ደብቀው አሳደጉት። ከዚህ በኋላ በሊቀ ካህኑ በዮዳሄ መሪነት ንግሥት ጎቶልያን ከሥልጣንዋ የማስወገድ ተግባር ተከናወነ። ዮዳሄ በሕይወት እስካለ ድረስ የይሁዳ ዋና የፖለቲካ መሪ ሆኖ አገለገለ። ዮዳሄ በኢዮአስ በመጠቀም መንፈሳዊ መነቃቃት ለማምጣት ቻለ። ዮዳሄ እንደሞተ ግን ኢዮአስ ከጌታ ፊቱን መለሰ። ዮዳሄ ከዙፋኑ በስተኋላ የነበረውን ሥልጣን በሚገባ የተጠቀመበት በንግሥት ጎቶልያ ሞትና በንጉሥ ኢዮአስ መንገሥ መካከል በነበረው ጊዜ ነበር። እግዚአብሔር ነቢዩ ኢዩኤልን በማስነሣት ቃሉን እንዲናገር ያደረገውም በዚህ ጊዜ ነበር። ኢዩኤል ምድሪቱን የመታትን የአንበጣ መቅሠፍት በምሳሌነት በመጠቀም፥ እንደ አንበጣ ምድሪቱን የሚያጠፋ በሰዎች የተገነባ ሌላ የጦር ኃይል እንደሚመጣ ተናገረ።  2. ከምርኮው በኋላ የነበሩት ጊዜያት (500 ዓ.ዓ. ገደማ) የውይይት ጥያቄ፥ ስለ መጽሐፈ ዕዝራ ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብ። በዕዝራ ዘመን የፖለቲካ ሁኔታ ምን ይመስል ነበር? መጽሐፉ የተጻፈው ዕዝራ በነበረበት ዘመን ገደማ ከሆነ የፖለቲካ ሁኔታው የተለየ ነበር ማለት ነው። በይሁዳ ከነበሩት ምርኮኞች አብዛኛዎቹ ወደ ይሁዳ ለመመለስ ሳይሆን በባቢሎን ለመቆየት የመረጡ ቢሆኑም፥ በዘሩባቤል፥ በዕዝራና በነህምያ መሪነት አንዳንድ አይሁዳውያን ተመልሰዋል። በላያቸው የነገሠ ንጉሥ አልነበረም። ይልቁንም በሜዶንና በፋርስ መንግሥት ቁጥጥር ሥር ስለነበሩ በሕዝቡ ላይ የተሾሙ ገዥዎች ነበሩ። እንደ እውነቱ ከሆነ ሕዝቡን የሚመሩት እንደ ዕዝራ ያሉ ካህናት ነበሩ። እነዚህ ካህናት መንፈሳዊ አመራር መስጠት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ መሪዎችም ሆኑ። ይህም የካህናቱን ሕይወት በማበላሸቱ፥ ከአመራር ስለሚያገኙት ሥጋዊ ጥቅም እንጂ፥ ስለ ሕዝቡ መንፈሳዊ ሕይወት የማይገዳቸው ሆኑ። ሕዝቡ በቃላቸው እግዚአብሔርን እንከተላለን እያሉ ቢናገሩም፥ የቅድስና ሕይወት የማይኖሩና የእግዚአብሔርን ሕግጋት በመታዘዝ የማይራመዱ ነበሩ። ኢዩኤል ነቢይ የነበረው በዚህ ዘመን ከሆነ፥ የተጠራው ወደ ምድራቸው የተመለሱት አይሁድ እግዚአብሔርን እንዳይተው፥ ነገር ግን

ትንቢተ ኢዩኤል መግቢያ Read More »