የሕይወት እንጀራ

ኦሪት ዘሌዋውያን

ዘሌዋውያን 23-27

ሰዎች እግዚአብሔርን የሚያመልኩባቸው የተለዩ ቀናት ከሌሏቸው በቀር፥ የሳምንቱን ቀናት በሙሉ በሥራ ወደ ማሳለፍ በማዘንበል፥ ስለ መንፈሳዊ ነገር ለማሰብና እግዚአብሔርን ለማምለክ ጊዜ ሊያጡ ይችላሉ። ለአይሁድ ከተለመደው ዕለታዊ ተግባራቸው ዞር የሚሉባቸውንና ስለ እግዚአብሔር በማሰብ እርሱን የሚያመልኩባቸው የተለያዩ ሃይማኖታዊ በዓላትን ሰጣቸው። አይሁድ ሳምንታዊ የአምልኮ ቀን፥ ወርኃዊ የአምልኮ ቀን፥ በየዓመቱ የሚደረጉ ሰባት የአምልኮ ቀናት፥ በየሰባት ዓመቱ የሚሆን የአምልኮ ዓመትና […]

ዘሌዋውያን 23-27 Read More »

ዘሌዋውያን 11-22

እግዚአብሔር ሕዝቡን የጠራው በፊቱ ቅዱሳን እንዲሆኑ ነው። ከዓለም የተለዩ መሆን አለባቸው። ይህ ልዩ መሆን በውስጣዊ ሕይወታችን ከሚኖር ለውጥ ይጀምራል። እኛ አዲስ ፍጥረት ነን (2ኛ ቆሮ. 5፡17)። ለውጥ ሁልጊዜ መጀመር ያለበት ከውስጥ (ከልብ) እንጂ ከድርጊት አይደለም። ይህም ማለት ልባችን በፍቅር፥ በደስታ፥ በሰላም፥ በትዕግሥት፥ ወዘተ. (ገላ. 5፡22-23) መሞላት አለበት ማለት ነው። የተለዩ ዝንባሌዎችና ዓላማዎች ሊኖሩን ይገባል። ደግሞም

ዘሌዋውያን 11-22 Read More »

ኦሪት ዘሌዋውያን 1-10

መሥዋዕቶችንና ዓላማቸውን በትክክል መረዳት እግዚአብሔር የኃጢአት ይቅርታ ያዘጋጀበትን መንገድ ለመረዳት ይጠቅማል። ኦሪት ዘሌዋውያን ኃጢአተኛ የሆነው የእስራኤል ሕዝብ የተቀደሰውን እግዚአብሔርን እንዴት ማምለክ እንዳለበት ዝርዝር መመሪያ ይሰጣል። እግዚአብሔር ቅዱስ ባይሆን ኖሮ፥ መሥዋዕት የሚባል ነገር ባላስፈለገም ነበር፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነና ኃጢአትን ሳይቀጣ ስለማያልፍ፥ እንዲሁም መሐሪ ስለሆነ፥ ለእስራኤላውያን ወደ እርሱ እንዴት እንደሚመጡና የኃጢአታቸውን ይቅርታ እንደሚያገኙ ዝርዝር መመሪያ

ኦሪት ዘሌዋውያን 1-10 Read More »

የኦሪት ዘሌዋውያን ዓላማ እና ቁልፍ ሃሳቦች

የኦሪት ዘሌዋውያን ዓላማ የኦሪት ዘሌዋውያን ዋና ዓላማ «ቅዱስ» በሚለው ቃል ተጠቃሏል። በመጽሐፉ ውስጥ ቅዱስ የሚለው ቃል ከ90 ጊዜ በላይ ተጠቅሶአል። ጌታ ራሱ ቅዱስ እንደሆነ ይገልጻል። ሕዝቡም በእርሱ ፊት ቅዱስ ይሆኑ ዘንድ ይነግራቸዋል። ቅድስና በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ የማይነካው ነገር የለም። እግዚአብሔርን ለእስራኤል ሕዝብ እንዴት የተቀደሱ ሕዝብ እንደሚሆኑና የማያቋርጥ በረከት እንደሚያገኙ ነግሮአቸዋል። ያ ቅድስናቸው የሚያተኩረው በሁለት

የኦሪት ዘሌዋውያን ዓላማ እና ቁልፍ ሃሳቦች Read More »

የኦሪት ዘሌዋውያን መግቢያ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልንረዳቸው በጣም አስፈላጊ ከሆኑት አሳቦች አንዱ «የቅድስና» አሳብ ነው። ይህም የእግዚአብሔር ባሕርይ መሠረት ነው። እግዚአብሔር በኦሪት ዘሌዋውያን ውስጥ ቅዱስ እንደሆነ በመደጋገም ይናገራል። የእግዚአብሔር ሕዝቦች ማንነትና እግዚአብሔር ሕዝቦቹን ሊሆኑ የሚገባቸውን የሚያስረዳ መሠረታዊ አሳብ የቅድስና አሳብ ነው። የእግዚአብሔር ሕዝብ እንደ መሆናችን መጠን እግዚአብሔርን መምሰል አለብን። ዘሌዋ. 11፡44፡- «እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና፤ ሰውነታችሁን ቀድሱ፥ ቅዱሳንም

የኦሪት ዘሌዋውያን መግቢያ Read More »