የሕይወት እንጀራ

ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

የድነት ማረጋገጫ

This entry is part 32 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ህ. የፅንሰ-አሳቡ አስፈላጊነት  በክርስትና ሕይወት ልምምድ ሰው በክርስቶስ በማመን የድነት ማረጋገጫ ማግኘቱ፥ በጸጋና ክርስቶስን በማወቅ ለማደጉ አጠቃላይ ሂደት መሠረት ነው። የድነት ማረጋገጫ፥ የልምምድ ጉዳይ በመሆኑ፥ ከእሁኑ ድነት እርግጠኛነት ጋር ይዛመዳል። ይህ ሰሚቀጥለው ምዕራፍ ከምንነጋገርበት ዘላለማዊ የድነት ዋስትና ጋር ሊደነጋጎር እያገባም። ዘላለማዊ ዋስትና የእውነታ ጥያቄ ሲሆን፥ የድነት ማረጋገጫ ግን አንድ ሰው በአንድ ጊዜ ስለ ራሱ ድነት […]

የድነት ማረጋገጫ Read More »

ቅድስና

This entry is part 31 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሀ. የትክክለኛ አተረጓጎም አስፈላጊነት  ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ አስፈላጊ ጭብጥ ላይ ጥልቅ መገለጥ ቢያቀርብም፥ ሰዎች የቅድስናን አስተምህሮ በተሳሳተ መንገድ ይረዱታል። ከዚህ የአስተምህሮ ታሪክ አንጻር፥ ሦስት የአተረጓጎም ሕጎችን ልብ ማለቱ ተገቢ ነው።  የመቀደስን አስተምህሮ በትክክል ለመረዳት፥ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህን በተመለከተ የተወቀሱ ክፍሎችን ሁሉ መመልከት ያሻል።  2. የቅድስና አስተምህሮ ስልምድ ሊለጥ እይችልም። ከቅድስና አስተምህሮ ሦስት

ቅድስና Read More »

የጽድቅ አራት ገጽታዎች

This entry is part 30 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

መጽሐፍ ቅዱስ አጽንኦት ሰጥቶ እንደሚያመለክተው፥ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል የሚገኘው ዋነኛ ልዩነት እግዚእብሔር ጻድቅ ሲሆን (1ኛ ዮሐ. 1፡5)፥ ሰው ግን ሮሜ 3፡10 ውስጥ “ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ” የሚል መሠረታዊ ክስ የቀረበበት ነው። ከመለኮታዊ ጸጋ ክብሮች አንዱ በሆነውና እንከን በሌለው የሠርግ ልብስ የተመሰለው ፍጹም መለኮታዊ ጸጋ መሰጠቱና ለሚያምኑ ሁሉ በነጻ መታደሱም ተገልጧል (ሮሜ 3፡22)።  መጽሐፍ ቅዱስ አራት

የጽድቅ አራት ገጽታዎች Read More »

ከኃጢአት ኃይል ነጻ መውጣት

This entry is part 29 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሀ. ከኃጢአት ነጻ መሆን ለክርስቲያኖች ብቻ  ከኃጢአት ኃይል ነጻነት፥ እግዚአብሔር ከኃጢአት በደልና ቅጣት ላዳናቸው ሰዎች የተሰጠ ምሕረት እንደመሆኑ፥ ይህ ትምህርት ክርስቲያኖችን ብቻ የሚመለከት ይሆናል። ክርስቲያኖች በክርስቶስ የዳኑና ዋስትና ያገኙ ቢሆኑም፥ ኃጢአታዊ ባሕርይ ስላላቸው፥ ኃጢአት ይሠራሉ። ይህን እውነት በተመለከተ የእግዚአብሔር ቃልም ሆነ ሰብአዊ ልምድ አያሌ ማረጋገጫ ይሰጣሉ። ክርስቲያኖች ኃጢአት ይሠራሉ በሚለው እውነት ላይ በመመሥረት፥ ከዚህ የኃጢአት

ከኃጢአት ኃይል ነጻ መውጣት Read More »

ከኃጢአት ቅጣት መዳን

This entry is part 28 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሀ. የድነት ትርጉም  ድነትን የሚመለከተው መለኮታዊ መገለጥ፥ በእምነት የእግዚአብሔር ልጅ በሆነ ሰው ሁሉ በሚገባ መታወቅ አለበት። ምክንያቱም፡- (1) የግል ድነት የሚመሠረተው በርሱ ላይ ስለሆነ፥ (2) አማኝ ለዓለሙ ሁሉ እንዲያውጀው እግዚአብሔር የሰጠው ዋነኛ መልእክት ስለሆነና፥ (3) የእግዚአብሔርን ፍቅር በሙላት የሚገልጠው መለኪያ ይኸው ብቻ ስለሆነ ነው።  መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተገለጠው ሰፊ ትርጉም መሠረት፥ “ድነት” የሚለው ቃል እግዚአብሔር

ከኃጢአት ቅጣት መዳን Read More »

ኃጢአት፡- ባሕርዩና ሁሉን አቀፍነቱ

This entry is part 27 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሀ. ሰው ስለ ኃጢአት ያለው አስተሳሰብ።  ኃጢአት በሰው ሕይወት ውስጥ ዋና እውነታና የመጽሐፍ ቅዱስ ታላቅ ጉዳይ በመሆኑ፥ የማያቋርጥ የውይይት ርዕስ ሆኖ ቆይቷል። መንፈሳዊ መገለጥን የማይቀበሉ ክፍሎች ስለ ኃጢአት በቂ ያልሆን ፅንሰ-አሳቦችን በመደጋገም ሰንዝረዋል። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነውና የተለመደው አመለካከት፥ ኃጢአት በዓለም መልካምና ክፉ አለ በሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ላይ በመመሥረት የሚመጣ የተሳሳተ እምነት ነው ብለውታል። ይህ ፅንሰ-አሳብ

ኃጢአት፡- ባሕርዩና ሁሉን አቀፍነቱ Read More »

ሰው፡- ውድቀቱ

This entry is part 26 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ኃጢአት ወደ ዓለም እንዴት ገባ የሚለው ጥያቄ ማንኛውም የአስተሳሰብ ሥርዓት የሚያነሣው ሲሆንም፥ ለእነዚህና ለመሳሰሉት ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ ያለው ግን መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው። ባለፉት ምዕራፎች ስለ መላእክት በተደረገው ጥናት እንደተመለከተው ሁሉ፥ ኃጢአት ወደ ዓለም የገባው፥ ሰው ከመፈጠሩ በፊትና በመጀመሪያ ቅዱሳን ሆነው በተፈጠሩ፥ በኋላ ግን ከሰይጣን ዓመፅ ጋር በተባበሩ መላእክት አማካይነት መሆኑን ለማስረዳት ተሞክሯል። የዘፍጥረት መጽሐፍ

ሰው፡- ውድቀቱ Read More »

ሰው፡- አፈጣጠሩ

This entry is part 25 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሀ. የሰው ፍጡርነት  ሰው በዚህ አስደናቂ በሆነ ፍጥረተ ዓለም መካከል በመሆን፥ የዚሁ ፍጥረተ ዓለም ቁንጮ ሆኖ ሲኖር፥ የራሱንና የሌሎቹን ፍጥረታት አጀማመር ለመረዳት ጥረት ያደርጋል። ተፈጥሮ የሰውን አፈጣጠር ስለማይገልጥና በቃል እየተወራረደ የመጣ ትምህርትም የሚያስተማምን መረዳት ስለማያስገኝ፥ እግዚአብሔር ራሱ ስለ ሰው አፈጣጠር በመጽሐፍ ቅዱስ አማካይነት የገለጠውን መመልከቱ አስተማማኝ ማረጋገጫ ይሆናል። በዘፍጥረት መጽሐፍ የመጀመሪያ ምዕራፎች በሌሎችም የመጽሐፍ ቅዱስ

ሰው፡- አፈጣጠሩ Read More »

ሰይጣን፡- ሥራውና የመጨረሻ ዕጣው

This entry is part 24 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሀ. ሰይጣንን በሚመለከት የሚቀርቡ ስሕተተኛ ፅንሰ-አሳቦች  የሰይጣንን ማንነት በሚመለከት በአሁኑ ጊዜ ሁለት ታላላቅ ስሕተቶች አሉ። የስሕተቶቹ ተጠቃሚ ራሱ ሰይጣን መሆኑን መረዳቱ ተገቢ ነው።  1. ብዙዎች ዕይጣን የለም፥ ሰይጣን የሚባለው በሰዎችና ስዓለማችን ያለው ክፉ አሠራር ወይም ተጽዕኖ ነው ብለው ያምናሉ። ይህ አስተሳሰብ ስሕተት ነው። ምክንያቱም የክርስቶስን መኖር የሚያረጋግጡ አያሌ ማስረጃዎች የመኖራቸውን ያህል፥ የሰይጣንንም መኖር የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች

ሰይጣን፡- ሥራውና የመጨረሻ ዕጣው Read More »

ሰይጣን፡- ማንነቱና ኃይሉ

This entry is part 23 of 52 in the series ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች

ሰይጣን ከእግዚአብሔር ፍጥረታት ሁሉ ብልጫ ያለው ሆኖ ቢፈጠርም፥ በርሱና በሕያው፥ ዘላለማዊ እና ባልተፈጠረው አምላክ መካከል ሰው ሊረዳ ከሚችለው በላይ የሆነ ልዩነት አለ። በሚቀጥለው ምዕራፍ እንደሚቀርበው ሰይጣን ቀድሞ ቅዱስ መልአክ የነበረ ቢሆንም፥ ካሰበት ቅድስና በመውደቅ የእግዚአብሔር ተፃራሪና የወደቁ መላእክት መሪ ሆነ ።  ሀ. የሰይጣን ማንነት  ልክ እንደ እግዚአብሔር እና እንደ ሌሎቹ መላእክት ሁሉ ሰይጣንም በአካለ ሥጋ

ሰይጣን፡- ማንነቱና ኃይሉ Read More »