የዚህ ጥናት ዓላማ ከእያንዳንዱ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ጋር በሚገባ እንድትተዋወቅ ለማድረግና የመጽሐፉን እውነቶች ከዘመናችን ጋር ለማዛመድ በመጣር እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን ያለውን መልእክት ለመረዳት ነው። የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ ከሕይወታችንም ጋር ማዛመድ አስፈላጊ እንደሆነ ልብ በል። የእግዚአብሔርን ቃል ባናጠናና በግል ከሕይወታችን ጋር ባናዛምደው፥ ከእግዚአብሔር ጋር በምናደርገው ጉዞ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያስከትልብናል፤ መንፈሳዊ ሕይወታችንም ይጠወልጋል። ይህ ጥናት ከእያንዳንዱ ተማሪ ብዙ ሥራን የሚጠይቅ ነው፤ ዳሩ ግን ከራስህ ሕይወት ጋር በማዛመድ ጥያቄዎቹን ሁሉ በጥንቃቄ ብትመልስና የሚሰጡህን ሥራዎች በሙሉ ብትሠራ፥ ብሉይ ኪዳንን በተሻለ መንገድ በመረዳት ከእግዚአብሔር ጋር ያለህ እርምጃ በይበልጥ ዕድገት ከማሳየቱም ሌላ፥ በሚገባ በምታውቀውና በተወሰነ የእግዚአብሔር ቃል ክፍል ላይ ከማተኮር ይልቅ ለሁሉም ክፍል ፍቅር ይኖርህና እንዴት ልትጠቀምበት እንደሚገባ ታውቃለህ። ሮሜ 15፡4 እንዲህ ይላል፡«በመጽናትና መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፎአልና።»
የጥያቄዎቹን መልሶች በደብተር ጻፍ። የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ከሌለህ ለጥናትህ ይረዳህ ዘንድ ለመግዛት ሞክር። አዲሱ ትርጒም የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስና የእንግሊዝኛ መጽሓፍ ቅዱስ ካለህ፥ በተጨማሪ ከእነርሱም አንብብ።
በትምህርቶቹ ውስጥ በርካታ ማብራሪያ ጥቅሶች ተሰጥተዋል። ከተሰጡት ጥቅሶች መካከል «ተመልከት» ተብለው የተጻፉትን ሁሉ መመልከት አስፈላጊ ነው። «ተመልከት» የሚል ትእዛዝ ያልተሰጠባቸውን ግን ጊዜ ካለህ ልትመለከታቸው ትችላለህ፤ አለበለዚያም ለሌላ የጥናትህ ጊዜ የሚጠቅሙህ ይሆናሉ።
የዚህ ጥናት አንዱ ግብ ተማሪው ብሉይ ኪዳንን በሙሉ እንዲያጠና ለመርዳት ነው። ስለዚህ ለአንድ ተማሪ የተሰጠውን የንባብ ክፍል ሁሉ አጠናቅቆ ማንበብ በጣም አስፈላጊ ነው።
በጥናቱ ውስጥ የተካተቱትን ጥያቄዎች ከመስራትዎ በፊት፣ መመሪያውን ጨምሮ በጥያቄዎቹ የፊት ገጽ ላይ የሚጠየቁትን ትክክለኛ ስምዎን (ወይም የብዕር ስምዎን) እና ትክክለኛ የኢ-ሜይል አድራሻዎን መሙላትዎን አይዘንጉ። ትክክለኛ የኢ-ሜይል አድራሻ እንዲሞሉ የተጠየቁበት ምክንያት ውጤትዎ የሚላከው በዚሁ አድራሻ ስለሆነ ነው፡፡ ጥያቄዎቹን ሰርተው ሲያበቁ “submit” የሚለውን ቁልፍ ይጫኑ። አንዳንድ ጊዜ “Google” ጥያቄዎቹን የሰራው ኮምፒውተር ወይም ሰው መሆኑን ለማጣራት የሴኪውሪቲ ጥያቄዎችን ሊጠይቆት ይችላል። “Submit” የሚለውን ቁልፍ ከተጫኑ በኋላ “view your score” የሚለውን ቁልፍ በመጫን ውጤትዎን እና የተሳሳቱትን ጥያቄ ግብረ መልስ (feedback) ማየት ይችላሉ። በጥያቄዎቹ ላይ የሚያነሱት ሃሳብ ካለ በሚከተለው ኢ-ሜይል ይላኩልን። tsegaewnet@gmail.com
የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
- የብሉይ ኪዳን ጥናት መግቢያ
- ብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ቃል ነው
- የብሉይ ኪዳን ቅጂዎቻችን እንዴት ሊደርሱን እንደቻሉ
- መጽሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም የሚጠቅሙ አጠቃላይ ሕጎች
- ትምህርት ብሉይ ኪዳን
- የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት እንዴት እንደተሰበሰቡ
- የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ታሪክ ጥናት
- የመካከለኛው ምሥራቅ መልክዓ ምድር
- የፔንታቱክ መግቢያ
- የፔንታቱክ መጻሕፍት ስሞች በውስጣቸው የሚታይ ታሪክ
- በፔንታቱክ ውስጥ የሚገኙ የሥነ ጽሑፍ ዓይነቶች
፩. ኦሪት ዘፍጥረት
- ዘፍጥረት 1-2 የዓለም አፈጣጠር
- የአዳምና የሔዋን ኃጢአት (ከዘፍ. 3)
- ዘፍጥረት 4-11 የኃጢአት በመላው ዓለም መሠራጨት
- የአብርሃም ታሪክ (ዘፍጥረት 12-24)
- ዘፍጥረት 25-36 የይስሐቅና የያዕቆብ ታሪክ
- ዘፍጥረት 37-50 የዮሴፍ ታሪክ
፪. ኦሪት ዘጸአት
- የእግዚአብሔር ሕዝብ በባርነት ቀንበር ሥር መሆን እና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ለማውጣት መሪ መጥራቱ (ዘጸአት 1-4)
- የእግዚአብሔር ሕዝብ ነጻነት (ዘጸ. 5-12)
- ዘጸአት 13-18
- ዘጸአት 19-24
- ዘጸአት 25-40
፫. ኦሪት ዘሌዋውያን
፬. ኦሪት ዘኁልቁ
፭. ኦሪት ዘዳግም
፮. መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ
፯. መጽሐፈ መሳፍንት
፰. መጽሐፈ ሩት
፱. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ
- የሳሙኤል መወለድና ጥሪ (1ኛ ሳሙ. 1-3)
- 1ኛ ሳሙ.4-7
- ሳኦል የእስራኤል ንጉሥ ይሆን ዘንድ ተመረጠ (1ኛ ሳሙ. 8-11)
- 1ኛ ሳሙኤል 13-15
- በዳዊትና በሳኦል መካከል የቀረበ ንጽጽር (1ኛ ሳሙ. 16-20)
- 1ኛ ሳሙኤል 21-31
- የ1ኛ ሳሙኤል ዋና ዋና ትምህርቶች
፲. መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ
፲፩. መጽሐፈ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ
፲፪. መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ
፲፫. እና ፲፬. መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ እና ካልዕ
- የ1ኛና 2ኛ ዜና መዋዕል መግቢያ
- የዜና መዋዕል ታሪካዊ ሥረ መሠረት
- የዜና መዋዕል አስተዋጽኦ እና አወቃቀር
- መጽሐፈ ዜና መዋዕል የተጻፈባቸው ዓላማዎች
- የመጽሐፈ ዜና መዋዕል ዋና ዋና ትምህርቶች
፲፭. መጽሐፈ ዕዝራ
፲፮. መጽሐፈ ነህምያ
፲፯. መጽሐፈ አስቴር
፲፰. መጽሐፈ ኢዮብ
፲፱. መዝሙረ ዳዊት
፳. መጽሐፈ ምሳሌ
፳፩. መጽሐፈ መክብብ
፳፪. መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን
፳፫. ትንቢተ ኢሳይያስ
- የትንቢት መጻሕፍት አጠቃላይ ገጽታ
- ነቢያትና ትንቢቶች
- ትንቢትን ለመተርጐም የሚጠቅሙ መመሪያዎች
- ስለ ትንቢት የሚቀርቡና በአተረጓጐሙ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ የተለያዩ አመለካከቶች
- የትንቢተ ኢሳይያስ መግቢያ
- ኢሳይያስ የኖረበት ዘመን ታሪካዊ ሥረ-መሥረት እና የነቢዪ ኢሳይያስ ሥረ-መሠረት
- የትንቢተ ኢሳይያስ አስተዋጽኦ
- የትንቢተ ኢሳይያስ ዓላማ
- በትንቢተ ኢሳይያስ ውስጥ የሚገኙ ዋና ዋና አሳቦች
፳፬. ትንቢተ ኤርምያስ
፳፭. ሰቆቃው ኤርምያስ
፳፮. ትንቢተ ሕዝቅኤል
- የትንቢተ ሕዝቅኤል መግቢያ
- የትንቢተ ሕዝቅኤል ታሪካዊ ሥረ መሠረት
- ትንቢተ ሕዝቅኤል በርካታ የሆኑ ልዩ ገጽታዎች እና አስተዋጽኦ
- የትንቢተ ሕዝቅኤል ዓላማ እና የሥነ መለኮት ትምሕርት
- የእግዚአብሔር ራእይና የሕዝቅኤል ጥሪ (ሕዝቅኤል 1-3)
- ሕዝቅኤል 4-12
- ሕዝቅኤል 13-17
- ሕዝቅኤል 18-24
- ሕዝቅኤል 25-32
- ሕዝቅኤል 33-39
- ሕዝቅኤል 40-48
፳፯. ትንቢተ ዳንኤል
፳፰. ትንቢተ ሆሴዕ
- የትንቢተ ሆሴዕ መግቢያ
- የትንቢተ ሆሴዕ ታሪካዊ ሥረ-መሠረት
- የትንቢተ ሆሴዕ አስተዋጽኦ እና ዋና ዋና አላማዎች
- ትንቢተ ሆሴዕን የሚመለከቱ ዋና ዋና ጉዳዮች
- በትንቢተ ሆሴዕ የሚገኙ ዐበይት የሥነ-መለኮት እውነቶች
፳፱. ትንቢተ አሞጽ
፴. ትንቢተ ሚክያስ
፴፩. ትንቢተ ኢዮኤል
፴፪. ትንቢተ አብድዩ
፴፫. ትንቢተ ዮናስ
፴፬. ትንቢተ ናሆም
፴፭. ትንቢተ ዕንባቆም
፴፮. ትንቢተ ሶፎንያስ
፳፯. ትንቢተ ሐጌ
፴፰. ትንቢተ ዘካርያስ
፴፱. ትንቢተ ሚልክያስ