እስልምና

ለሙስሊም ወዳጆቻችን ጥያቄዎች የተሰጠ ምላሽ

በ ሀሪ ሞሪን፤ ትርጉም፣ አዳነው ዲሮ ዳባ

መታሰቢያነቱ

ወንጌል የሚያስከፍለውን ዋጋ፣ የጽድቅና የቅድስና መንገድ ያለባትን መከራና እንግልት ጌታ እየሱስን በማመኑና የመረጠለትን መንገድ በመከተሉ ምክንያት የሰው ህሊና ሊያስበው ከሚችለው በላይ በቤተሰቡና በዘመዶቹ ሳይቀር ከፍተኛ ስቃይ ከደረሰበት ወንድም ተምሪያለሁ፡፡ ይህ ሰው ዩሱፍ ጀማል ሞሃመድ ይባላል፡፡ የዚህ መጽሐፍ መታሰቢያነት ለእርሱ፣ እጅግ አስቸጋሪና አደገኛ እንዲሆም የሕይወት መስዋእትነትን ጭምር በሚጠይቁ የእስልምና አገሮች የምስራቹን ቃል በማሰራጨት ታላቅ የወንጌል መስዋእትነት እየከፈሉ ላሉ ቅዱሳን፣ እና ወንጌል በሚፈቅደው የፍቅርና የትህትና መንገድ ላይ በመቆም የክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነትን ለመመስከርና ሰዎችን በንፁህ ህሊና ለማገልገል ሲሉ ለተሰዉ የወንጌል አርበኞች በሙሉ ይሁን፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ መከራን ስለ መቀበል ምን ይላል?
2ጢሞ. 1፡8 እንግዲህ በጌታችን ምስክርነት ወይም በእስረኛው በእኔ አትፈር፣ ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር ኃይል መጠን ስለ ወንጌል አብረኸኝ መከራን ተቀበል፤

2ጢሞ. 3፡12 በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።

1ጴጥ. 2፡20-21 … መልካም አድርጋችሁ መከራን ስትቀበሉ ብትታገሡ፣ ይህ ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ምስጋና ይገባዋል። የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና። (በተጨማሪ 1ጴጥሮስ 3፡13-17 ይመልከቱ)

1ጴጥ. 5፡10 በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ ለጥቂት ጊዜ መከራን ከተቀበላችሁ በኋላ ራሱ ፍጹማን ያደርጋችኋል ያጸናችሁምል ያበረታችሁማል።

ሐዋ. 9፡15-16 ጌታም። ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው።
ራዕ. 1፡9 እኔ ወንድማችሁ የሆንሁ ከእናንተም ጋር አብሬ መከራውንና መንግሥቱን የኢየሱስ ክርስቶስንም ትዕግሥት የምካፈል ዮሐንስ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ኢየሱስ ምስክር ፍጥሞ በምትባል ደሴት ነበርሁ።

ሐዋ. 9፡15-16 ጌታም። ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው።

2ቆሮ. 6፡4-10 ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤ በብዙ መጽናት፣ በመከራ፣ በችግር፣ በጭንቀት፣ በመገረፍ፣ በወኅኒ፣ በሁከት፣ በድካም፣ እንቅልፍ በማጣት፣ በመጦም፣ በንጽህና፣ በእውቀት፣ በትዕግሥት፣ በቸርነት፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ ግብዝነት በሌለው ፍቅር፣ በእውነት ቃል፣ በእግዚአብሔር ኃይል፣ ለቀኝና ለግራ በሚሆን በጽድቅ የጦር ዕቃ፣ በክብርና በውርደት፣ በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤ ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤ ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው።

2ቆሮ. 11፡23-27 … በድካም አብዝቼ፣ በመገረፍ አብዝቼ፣ በመታሰር አትርፌ፣ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ። አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ። ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወገርሁ፤ መርከቤ ሦስት ጊዜ ተሰበረ፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ ኖርሁ። ብዙ ጊዜ በመንገድ ሄድሁ፤ በወንዝ ፍርሃት፣ በወንበዴዎች ፍርሃት፣ በወገኔ በኩል ፍርሃት፣ በአሕዛብ በኩል ፍርሃት፣ በከተማ ፍርሃት፣ በምድረ በዳ ፍርሃት፣ በባሕር ፍርሃት፣ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርሃት ነበረብኝ፤ በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፣ በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፣ በብርድና በራቁትነት ነበርሁ።

ፊል. 3፡7-11 ነገር ግን ለእኔ ረብ የነበረውን ሁሉ ስለ ክርስቶስ እንደ ጉዳት ቆጥሬዋለሁ። አዎን፣ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤ ስለ እርሱ ሁሉን ተጐዳሁ፣ ክርስቶስንም አገኝ ዘንድ፣ በክርስቶስም በማመን ያለው ጽድቅ ማለት በእምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ጽድቅ እንጂ ከሕግ ለእኔ ያለው ጽድቅ ሳይሆንልኝ፣ በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጕድፍ እቈጥራለሁ፤ እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፣ በመከራውም እንድካፈል፣ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፣ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።

ጠቃሚ ምክሮች

በጽሑፎቹ መካከል በብራኬት [ ] የገቡ ማብራሪያዎች የተርጓሚው ተጨማሪ አሳቦች ሲሆኑ፣ ከቁርአን በተወሰዱት አንቀጾች (አያት) መካከል የሚታዩ ቅንፎች ( ) ግን በቀጥታ ከቁርአኑ የተወሰዱ ናቸው፡፡

ከቁርአን የተወሰዱ የእንግሊዘኛው አንቀጾች (አያት) ከአማርኛው ትርጉም ጋር አብረው እንዲቀርቡ የተደረገበት ምክንያት አማርኛው ትርጉም ውስጥ የሚስተዋሉ ብዥታዎችን ግልጽ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡

ሁሉም የቁርአን እንግሊዘኛ ጥቅሶች የተወሰዱት – The Holly Qur’an: Translation and Commentary by A. Yusuf Ali © 1977፣ Amana Corporation – ላይ ሲሆን የአማርኛ ጥቅሶቹ ደግሞ፡- ከቅዱስ ቁርአን 1961 ዓ.ም. እትም ላይ የተወሰዱ ናቸው፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶቹ የተወሰዱት ደግሞ ከአማርኛ የመጽሐፍ ቅዱስ 1948 ዓ.ም. እትም ላይ ነው፡፡

ለሙስሊም ወዳጆቻችን ጥያቄዎች የተሰጠ ምላሽ

ማውጫ

አጠቃላይ ምልከታ ስለእስልምና (በተርጓሚው)
ለሙስሊም ወዳጆቻችን ጥያቄዎች የተሰጠ ምላሽ፣ መግቢያ

አስተያየት፣ ጥያቄና ሃሳብ ካሎት ከዚህ በታች ባለው ፎርም ቢልኩልን በደስታ እናስተናግዳለን።

%d bloggers like this: