የሕይወት እንጀራ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 12፡1 አንብብ። ሀ) ጳውሎስ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ቸል እንዳይሉ ወይም እንዲያውቁ ይፈልግ የነበረው ነገር ምን ነበር? ለ) ዛሬም ክርስቲያኖች በተመሳሳይ መንገድ ቸልተኛ የሆኑበት ወይም የማያውቁት ነገር አለን? መልስህን አብራራ ሐ) በቤተ ክርስቲያንህ መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሏቸውን አንዳንድ ሰዎች ጥቀስ። አንዳንድ መንፈሳዊ ስጦታዎች እንዳሏቸው እንድታምን ያደረገህ በሕይወታቸው ያየኸው ነገር ምንድን ነው? መ) አብዛኛዎቹ ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ እየተጠቀሙ ይመስልሃልን? መልስህን አብራራ። 

እግዚአብሔር በእኛ በልጆቹ ላይ በርካታ ስጦታዎችን አፍስሷል። ከድነት (ደኅንነት) ሌላ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ከተቀበልነው ሁሉ ታላቁ ነው። መንፈስ ቅዱስ በልባችን ስላሚኖር ሁሉ ነገራችን ይለወጣል። የእግዚአብሔር ጠላቶች የነበርን እኛ ልጆቹ እንሆናለን። የቀድሞ አባታችን የነበረውን ዲያብሎስን ከመምሰል አሁን አባታችን የሆነውን እግዚአብሔርን ወደ መምሰል እንለወጣለን። የእግዚአብሔር ልዩ ልጅ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንመስል ዘንድ መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን ሁልጊዜ ይሠራል። እንደ ኢየሱስ እንድንኖር፥ እንደ ኢየሱስ ተግባራችንን እንድናከናውንና እንደ ኢየሱስ እንድንሠራ ይረዳናል። በምስክርነታችን፥ በአምልኮአችንና በጸሎታችን ባለን የሕይወት ዘርፍ ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ሊረዳን ከእኛ ጋር አለ። ምን ዓይነት ወዳጅ ነው ያለን! መንፈስ ቅዱስ እጅግ በጥልቀት በሕይወታችን ከሚሠራቸው ነገሮች አንዱ የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን እናገለግል ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታዎችን መስጠቱ ነው። 

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአሳብ ልዩነት ምክንያት ከፍተኛ ክርክር ከሚካሄድባቸው ርእሶች እንዱ የመንፈሳዊ ስጦታዎች ጉዳይ ነው። በአንድ በኩል የመንፈሳዊ ስጦታዎችን ጉዳይ የሚያናንቁ ክፍሎች አሉ። ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች ሲናገሩ ወይም ሲያስተምሩ አይታዩም። ከዚህም የተነሣ፥ በቤተ ክርስቲያናቸው መንፈሳዊ ስጦታዎች በአገልግሎት ላይ አይውሉም። ስለዚህ ጥቂት ሰዎች ብቻ መሪ የሚሆኑበትና የሚያገላግሉበት፥ አብዛኞቹ ግን ተሳትፎ ሳያደርጉ ዳር ቆመው የሚያዩበት ቤተ ክርስቲያን ሆኖ ይቀራል። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት በአምልኮአቸው ወይም በአገልግሎታቸው ያለው መንፈሳዊ ኃይል አነስተኛ ነው። 

በሌላኛው ጽንፍ ደግሞ በመንፈሳዊ ስጦታዎች በተለይ በድንቃ ድንቅ የታጀቡ መንፈሳዊ ስጦታዎች የሚያስደስቷቸው ይገኛሉ። ትኩረት የሚያደርጉበት የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ይህ ብቻ ነው። ለመንፈስ ቅዱስ ህልውና ብቸኛ ማረጋገጫ የሚሆኑት መንፈሳዊ ስጦታዎች፥ በተለይም በልሳን እንደ መናገር ያሉ ትኩረት የሚስቡ ሁኔታዎች ናቸው፤ እነዚህ ነገሮች ከሌሉ መንፈስ ቅዱስ አላ ማለት አይቻልም ብለው ያስተምራሉ። 

እነዚህ ሁለቱም ክፍሎች ሚዛናዊ ስላልሆኑ ለቤተ ክርስቲያን አደገኞች ናቸው። እንደገና ማስታወስ ያለብን የክርስቲያን ሕይወት ሚዛናዊ መሆኑን ነው። መንፈሳዊ ስጦታዎችን መካድ ወይም መገደብ ስሕተት ሲሆን ይህን ስናደርግ መንፈስ ቅዱስ በክርስቶስ አካል ውስጥ የሚሠራውን የመገንባት ሥራ እናስተጓጉላላን። በመንፈሳዊ ስጦታዎች እጅግ በመፈንደቅ በመንፈስ ቅዱስ ላይም ሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለሚሰጡ ሌሎች ትምህርቶች እኩል ትኩረት አለመስጠት ስሕተት ነው። 

ጥያቄ፡ ሀ) በኢትዮጵያ በምትገኝ በዛሬይቱ ቤተ ክርስቲያን እነዚህን ሁላት ዝንባሌዎች የምታየው እንዴት ነው? ላ) ይህ ሚዛናዊነት ማጣት ምን ምን ችግሮችን ፈጠረ? 

ይህ ጉዳይ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እጅግ የሚከፋፍል ርእስ ስለሆነ በሚቀጥሉት በርካታ ሳምንታት አዲስ ኪዳን ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች የሚያስተምረውን እንመለከታለን። መንፈሳዊ ስጦታዎች ስለ ነበራቸው ሰዎች ብሉይ ኪዳን የሚጠቃቅስ ቢሆንም መንፈሳዊ ስጦታዎች ምን እንደሆኑና እንዴት ልንገለገልባቸው እንደሚገባ ብዙ አሳብ አልተሰጠም። ለዚህ ትምህርት የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች በተለይ ደግሞ ሐዋርያው ጳውሎስ ባለውላታችን ነው። 

ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ሮሜ 12፡1-8፤ ኤፌ. 4፡1-16፤ 1ኛ ጴጥ. 4፡7-11 ። እነዚህ ጥቅሶች እያንዳንዳቸው መንፈስ ቅዱስ መንፈሳዊ ስጦታዎችን በመስጠት ላላለው ሚና ምን ያስተምራሉ? 

መንፈስ ቅዱስ የመንፈሳዊ ስጦታዎች ሰጪ 

መንፈስ ቅዱስ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች እንዱ አንድ ሰው ወደ ክርስትና ሲመጣ ሰውዬውን ወደ ክርስቶስ አካል መጨመር ነው። ይህን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ (ማጥመቅ› ብለነው ነበር። አንድ ክርስቲያን በክርስቶስ አካል ከተጨመረ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ምን ያደርጋል? መልሱ ክሚከተሉት ሦስት ነገሮች አንዱን መፈጸም የሚያስችሉትን መንፈሳዊ ስጦታዎች መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን ይሰጣል የሚል ነው። 

ህ የክርስቶስ አካል አባል እንደመሆኑ መጠን ከሌሎች ጋር በኅብረት እግዚአብሔርን ማመለክ እንዲችል ይረዳዋል። 

2. በክርስቶስ አካል ውስጥ ያሉትን ሌሎችን በእምነት ለማሳደግ ያገላግል ዘንድ ይረዳዋል። 

3. ከክርስቶስ አካል ውጭ የሆኑት ወደ ክርስቶስ አካል ይመጡ ዘንድ እንዲያገለግል ይረዳዋል። በአጭሩ ክርስቲያኖች ኢየሱስን እንዲያመልኩ፥ የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተ ክርስቲያንን) እንዲያሳድጉና በኢየሱስ ስፍራ ሆነው ለዓለም አገልግሎት እንዲሰጡ ይረዳዋል። 

አዲስ ኪዳን የሚያስተምረን መንፈሳዊ ስጦታዎችን ለመስጠት ኃላፊነት ያላበት የሥላሴ አካል መንፈስ ቅዱስ መሆኑን ነው። በ1ኛ ቆሮ. 2፡1 እንደዚህ የሚል አሳብ ተነግሮናል «ይህን ሁሉ ግን (መንፈሳዊ ስጦታዎችን) ያ አንዱ መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻው እያካፈለ ያደርጋል።» በዚህ ጥቅስ የምናየው መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ መንፈሳዊ ስጦታዎችን እንዴሰጠ ነው። መንፈስ ቅዱስ በተቀዳሚ ስጦታውን ሰሚቀበለው ሰው ፍላጎት ሳይሆን በራሱ ፈቃድ መንፈሳዊ ስጦታዎችን ይሰጣል። በ1ኛ ቆሮ. 2፡7 ቀደም ብሎ እነዚህ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች «መንፈስ ቅዱስን መግለጥ» ተብለው ተጠቅሰዋል። ይህ የሆነበት ምክንያት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ህልውናውን ክሚያረጋግጥባቸው መንገዶች አንዱ ሰዎች መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን እንዲጠቀሙ ማድረግ ስለሆነ ነው። መንፈሳዊ ስጦታዎች ከሌሉ መንፈስ ቅዱስ እንደሌለ ለመጠርጠር እንችላለን። ወይም መንፈስ ቅዱስ እራሱን እንዳይገልጥ የተከላከለበት መንገድ አለ ማለት ነው።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading