የሕይወት እንጀራ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- ሀ) መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ እንዴት ትመልሰዋለህ? ለ) መንፈሳዊ ስጦታ ከተፈጥሮአዊ ችሎታ የሚለየው እንዴት ነው? 

ዛሬ በቤተ ክርስቲያን በመንፈሳዊ ስጦታ ምንነት ላይ በርካታ የተላያዩና የተምታቱ አሳቦች አሉ። አንዳንዶች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጥሩ ዘማሪ ይሰውና የመዘመር መንፈሳዊ ስጦታ አለው ይላሉ። የመዘመር ችሎታ ስጦታ ሲሆን ይህን ስጦታ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎችን ለማገልገል ልንጠቀምበት እንችላለን። ነገር ግን ክርስቲያን ያልሆኑ በርካታ ሰዎች የማከም ችሎታ አላቸው። ብዙ ጊዜ ጌታን የማያከብር ዜማ ያዜማሉ። ስለዚህ ዜማ ከእግዚአብሔር የሚገኝ ስጦታ ቢሆንም ለክርስቲያኖችና ክርስቲያን ላልሆኑም የሚሰጥ ተፈጥሮአዊ ችሎታ ነው። ስለዚህ የመዘመር ችሎታ በራሱ መንፈሳዊ ስጦታ አይደለም። ሌሎች ደግሞ አንዳንድ ሰዎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያደርጉትን እንደ ተአምራትና ፈውስ የመሳሰሉ አስደናቂ ሁኔታዎችን ብቻ መንፈሳዊ ስጦታዎች ናቸው ብለው ያስባሉ። ሆኖም ቀን ብዙ ጊዜ መንፈሳዊ ስጦታዎች ሌሎችን እንደ መርዳት ሳሉ ቀላል ነገሮች የሚገለጡም ናቸው (ሮሜ 12፡6-8)። 

አንድ ሰው መንፈሳዊ ስጦታ «የክርስቶስን አካል የምናገለግልበት የጸጋ ስጦታ ነው» ብሏል። መንፈሳዊ ስጦታ፥ «ቤተ ክርስቲያንን ማለትም የክርስቶስን እካላ እንዲያገለግልበት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን የሚያድላው ነፃ ስጦታ» ሲሆን አገልጋዩ የክርስቶስ አካል ለሆነችው ለቤተ ክርስቲያን ሰዎችን በማዝ አገልግሎቱን ይሰጥ ዘንድ የሚያስችላውን ሁኔታ የሚፈጥር ነፃ ስጦታ ነው። 

ይኸውም፡- 

የቤተ ክርስቲያን ጌታ የሆነውን ክርስቶስን ማምልከ እንዲችሉ፥ 

ክርስቶስን ወክለው ለቤተ ክርስቲያን ይናገሩ ዘንድ፥ 

ክርስቶስን እየመሰሉ ያድጉ ዘንድ ሌሎችን እንዲረዱ፥ 

ክርስቶስን ወክለው የሌሎችንም ክርስቲያኖች ፍላጎት እንዲያገለግሉ። 

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በዓለም ፊት እንዲወክሉ የሚያስችልበት መንገድ ነው። 

ቀጥሎ መንፈሳዊ ስጦታዎችን በተመለከተ ዋና የሚባሉ ትምህርቶችን በአጭሩ እንመለከታለን። 

1 እግዚአብሔር ለክርስቲያኖች እንደ ስጦታ የሚሰጣቸው ነገር ነው። ከእግዚአብሔር ጸጋ የሚመጣ ስለሆነ ሠርተን ወይም በጣም መንፈሳዊ በመሆናችን የምናገኘው አይደለም። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከራሱ ፍላጐት በነፃ ለክርስቲያኖች የሚሰጠው ነገር ነው። 

2. የሚሰጠው ለክርስቲያኖች ብቻ እንጂ ክርስቲያን ላልሆኑት አይደለም። ስለዚህ አንድ ሰው ከመዳኑ በፊት ሳይሆን ከዳነ በኋላ ብቻ የሚያገኘው ነው። ይህ ማለት ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች በራሳቸው መንፈሳዊ ስጦታ ፧ አይደሉም ማለት ነው። ከተፈጥሮ ችሎታ ጋር ሊያያዙ ቢችሉም እንኳ መንፈሳዊ ስጦታዎች ከእግዚአብሔር የሚሰጡ ልዩ ስጦታ ስለሆኑ ከተፈጥር ችሎታ የላቁ ናቸው። 

3. የመንፈሳዊ ስጦታዎች ዓላማ ኢየሱስን ወክሎ ሌሎችን ማገልገል ነው (ኤፌ. 4፡1-13፤ 1ኛ ጴጥ. 4፡10-11፤ 1ኛ ቆሮ. 12፡7፥ 21-26፥ 14፡26፤ ሮሜ 12፡4-5)። ስለዚህ ትኩረቱ የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ናት። ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን ይናገር ዘንድ ይረዳል። ሰዎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ኢየሱስን እየመሰሉ እንዲያድጉ ይረዳል። ቤተ ክርስቲያን በውስጧ ያሉት ሰዎች እርስ በርሳቸውም ሆነ በዓለም ያሉትን ያገላሉ ዘንድ ይረዳቸዋል። የእግዚአብሔርን ጸጋ ለሌሎች የምናገለግልበት መንገድ ነው (1ኛ ጴጥ. 4፡10)። 

4 መንፈሳዊ ስጦታዎች በርካታ ዓይነት ናቸው። እያንዳንዱ ክርስቲያን ቢያንስ አንድ ስጦታ ማለትም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያገለግልበት አንድ ችሎታ አለው (1ኛ ቆሮ. 12፡7፥1፥ 27፤ ሮሜ 12፡6)። ስጦታዎችን በሙሉ አጠቃሎ የያዘ ክርስቲያን የለም (ሮሜ 12፡4-5፤ 1ኛ ቆሮ. 12፡29-30)። 

በዚህ ክፍል የተዘረዘሩት ስጦታዎች ስጦታዎችን በሙሉ ያጠቃለሉ እንደሆነ አናውቅም። ሁሉም ዝርዝሮች የተላያዩ መሆናቸው የሚያሳየው፥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱት ስጦታዎች ናሙናዎች መሆናቸውንና ሌሎችም መንፈሳዊ ስጦታዎች ተብለው መጠቀስ የሚችሉ ነገሮች መኖራቸውንም ይመስላል። ስለዚህ በአዲስ ኪዳን ከተጠቀሱት ከአሥራ ሰባት ወይም ከአሥራ ስምንት የሚበልጡ መንፈሳዊ ስጦታዎች እንዳሉ ማመን የበለጠ ትክክለኛ ነው። 

5. መንፈሳዊ ስጦታ የአገልግሎት ቦታ አይደለም። አንድ ሰው የማስተማር ስጦታ ሳይኖረው ‹መምህር› ተብሎ ሊጠራ ይችላል። መንፈሳዊ ስጦታ የሚለካው አንድ ሰው በአገልግሎቱ በሚያስገኘው ፍሬ እንጂ ለሥራው በመቀጠሩ አይደለም። 

6. መንፈሳዊ ስጦታን በማግኘትና በመንፈሳዊ ሕይወት በመብሰል መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት የለም። በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ያልበሰሉ ክርስቲያኖች ሁሉ እንኳ መንፈሳዊ ስጦታ አላቸው። አንድ ክርስቲያን መንፈሳዊ ስጦታዎችን በሚገባ እየተጠቀመ (ለምሳሌ በልሳን ሊናገር ይችላል) መንፈሳዊነት ግን ላይኖረው ይችላል። የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በመካከላቸው በነበረው መከፋፈልና የሥነ ምግባር ጉድለት የተነሣ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮ. 3፡1-4 ቤተ ክርስቲያናቸውን ዓለማዊ ብሎ ጠርቷታል (1ኛ ቆሮ. 3፡5)። ነገር ግን መንፈሳዊ ስጦታዎች በሙሉ እንደነበራቸው ደግሞ ተናግሯል (1ኛ ቆሮ. 1፡7)። እነዚህ ክርስቲያኖች ስልሳናት እየተናገሩ በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ቁጥጥር ሥር ግን አይኖሩም ነበር። 

7. ማንም ሰው መንፈሳዊ ስጦታዎችን በሥራው ሊያገኛቸው ባይችልም ከእግዚአብሔር መጠየቅ እንደሚቻል ቀን ተጽፏል (1ኛ ቆሮ. 12፡31፤ 14፡1። መንፈሳዊ ስጦታዎቻችንን ቶል ብለን ልንተዋቸው ወይም በልምምድና በሥልጠና ልናነሣሣቸው እንደምንችል የሚያመለክቱ ማስረጃ ዎች አሉ። በአዲስ ኪዳን ውስጥ የእግዚአብሔር ሰዎች የሆኑ መሪዎች በመንፈስ ቅዱስ መሪነት መንፈሳዊ ስጦታዎችን ለሌሎች ክርስቲያኖች ለማስተላለፍ እንደቻሉ በበርካታ ስፍራዎች እንመለከታለን (1ኛ ጢሞ. 4፡14፤ 2ኛ ጢሞ. 16)። 

ጥያቄ፡- ከላይ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች በአጭሩ የተመለከትነው አሳብ የምታውቃቸው በርካታ ክርስቲያኖች ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች ካላቸው አመለካከት ጋር የሚነጻጸሩት እንዴት ነው? 

በአዲስ ኪዳን ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች የሚነግሩን አራት ክፍሎች አሉ። ሮሜ. 12፡1-8፤ 1ኛ ቆሮ. 12-14፤ ኤፌ. 4፡7-13፤ 1ኛ ጴጥ. 4፡7-11። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች የሚያስተምራቸውን ነገሮች በግልጽ ለመረዳት እነዚህን ክፍሎች በጥንቃቄ መመርመር አለብን። በመጀመሪያ አግግርቹን ክፍሎች እናጠናና ቀጥሎ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች ክሚያስተምሩት ክፍሎች ዋነኛው የሆነውን 1ኛ ቆሮ. 12-14 እናጠናለን።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

1 thought on “መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?”

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading