የሕይወት እንጀራ

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- ያዕ. 5፡14–15 አንብብ። ሀ) በዚህ ክፍል በምታገኘው መሠረት የፈውስን ቅደም ተከተሎች አስፍር። ለ) ይህ የፈውስ አሠራር ለመፈወስ ኃይል እንዳላቸው ከሚናገሩት ሰዎች አሠራር ጋር እንዴት ይሄዳል? 

እግዚአብሔር አሁንም ይፈውሳልን? አዎን። እግዚአብሔር በቀደሙት ዘመናት ተአምራትን እንዳደረገ ዛሬም ፈውስን የሚያካትቱ ተአምራትን ያደርጋል። እግዚአብሔር የፈውስ ሥራውን አቁሟል ማለት ስሕተት ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ ይፈውሳል ማለትም ስሕተት ነው። ኢየሱስ በከነዓን የነበሩትን በሙሉ እንዳልፈወሰና ደቀ መዛሙርትም በአገልግሎታቸው የፈወሱት ያገኙትን ሰው ሁሉ እንዳልሆነ ዛሬም እግዚአብሔር ሰውን ሁሉ እንደሚፈውስ ማስረጃ ማቅረብ እንችልም። 

ታዲያ እግዚአብሔር ዛሬ ፈውስን የሚያደርግበት ተለምዶአዊ መንገድ ምንድን ነው? ስንታመም ወይም የምንወደው ሰው ሲታመም ወይም በቤተ ክርስቲያን ያለ አንድ ሰው ሲታመም ምን ማድረግ አለብን? አዲስ ኪዳን የሚከተሉትን ነገሮች ያስተምራል። 

1. በመጀመሪያ ስትታመም እግዚአብሔር ይፈውስህ ዘንድ ጸልይ። እግዚአብሔር እየቀጣህ ያለው ያልተናዘዝኸው ኃጢአት እንዳለ እራስህን መርምር። ፈውስን እስኪሰጥህ ድረስ በትዕግሥት በመጠበቅ እግዚአብሔር በዚህ በሽታ ውስጥ ሊያስተምርህ የሚፈልገው ነገር ምን እንደሆነ ጠይቀው። በሽታ ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር ልጆቹን ለማስተማር የሚጠቀምበት መሣሪያ ነው። 

2. ወደ ሐኪም ወይም በሕክምና ሙያ ወደ ሠለጠነ ሰው በመሄድ ምርመራ አድርግ። እግዚአብሔር ያለ ምንም መድኃኒት ሊፈውሰን ቢችልም እንኳ አእምሮአችንን በመጠቀም ውሳኔ ልናደርግና ተገቢውን የሕክምና እርዳታ ሊሰጠን ወደሚችል ሰው ልንሄድ ይገባናል። ለሕክምና ባለሙያዎች ችሎታንና ሥልጣናን የሰጠ እግዚአብሔር መሆኑን አስታውስ። እግዚአብሔር ፈውስን ለማምጣት መሣሪያው አድርጐ ሊጠቀምባቸው ይችላል። ነገር ግን እምነታችን በመድኃኒት ወይም በሰዎች ሳይሆን ፈውስን ለማምጣት በሰዎች በሚሠራ በእግዚአብሔር እንደሆነ መረዳት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ 

3. የሕክምና እርዳታ ፈውስን ሊያመጣ ካልቻላ ስያዕ. 5 ላይ ያለውን መመሪያ ተከተል። የመፈወስ ስጦታ አለን ወደሚሉ ሰዎች አትሂድ። በምንታመምበት ወቅት እግዚእብሔር በቀጥታ ያላመለከተውን መንገድ ከመከተል መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን መከተል ይሻላል። 

ሀ. የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ጥራ። 

ለ. ከሽማግሌዎች ጋር በመሆን በእግዚአብሔር ፊት ንጹሕ ትሆን ዘንድ ራስህን መርምር። ብዙ በሽታዎች በቀጥታ የኃጢአት ውጤት ባይሆኑም እግዚአብሔር ያለመታዘዛችንን ለመቅጣት በሽታዎችን አንዳንድ ጊዜ ወደ ሕይወታችን ያመጣል። ኃጢአትን ካደረግን እግዚአብሔር ይፈውሰን ዘንድ ከመጠየቃችን በፊት ተናዝዘን ንስሐ መግባት አለብን። 

(ማስታወሻ፡–በሽታ ሁሉ የኃጢአት ውጤት ነው ከማለት እጅግ ተጠንቀቅ። ብዙ ጊዜ አይደለም። እግዚአብሔር ክፉዎችን የሚቀጣበት ጊዜ ቢኖርም እንኳ ብዙ ጊዜ እስከ መጨረሻው የፍርድ ቀን ድረስ ሳይቀጡ ይቆያሉ። ደግሞም እግዚአብሔር ኃጢአትን የሚያደርጉ ክርስቲያኖች አንዳንድ ጊዜ ቢቀጣም እንኳ ሁልጊዜ አይቀጣም (መዝ. [73]፡1-17)። እግዚአብሔር ልዩ በሆነ መገለጥ ችግሩን ካልጠቆመ በስተቀር በሰው ሕይወት ውስጥ ንስሐ ያልተገባበት ኃጢአት እንዳለ የሚያውቁት ግለሰቡና እግዚአብሔር ብቻ ናቸው። 

ሐ. ኃጢአትህን ከተናዘዝክ ወይም ሽማግሌዎች ነፃ መሆንህን ካረጋገጡልህ በኋላ ሽማግሌዎች ዘይት ቀብተው ይጸልዩልህ። ለምን ዘይት መቀባት አስፈለገ? ብዙ ክርስቲያኖች በዘይት ውስጥ የተለየ ነገር እንዳለ ስለሚያስቡ ዘይት መኖር አለበት፤ በዘይቱና እርሱ በሚወክለው ነገር አማካኝነት ፈውስ ያመጣል ያላሉ። ይህ ግን ሊሆን የሚችል ነገር አይደለም። በጥንት ጊዜያት ከሁሉ የተሻለና የታወቀ መድኃኒት ዘይት ነበር። በመዝ 23 ላይ እግዚአብሔር ራሳችንን በዘይት የሚቀባ እረኛ መሆኑ የተነገረው ለዚህ ነው። መቀባቱ ፈውስን ለማምጣት የታለመ ነበር። ዘይት መጠቀም ስሕተት ባይሆንም እንኳ ያዕቆብ የሚናገረው ጸሎትን ለበሽታው ተስማሚ ከሆነ መድኃኒት ጋር የማቀናጀት ጉዳይ እንደሆነ አምናለሁ። 

መ. ሽማግሌዎች ዘይት ከመቀባት ጋር ሊጸልዩልህ ይገባል። ጸሎት ከመድኃኒት ወይም ከዘይት ጋር ሲቀናጅ እግዚአብሔር ይፈውሳል። ነገር ግን የሚፈውሰው ምንድን ነው? ፈውስን የሚያመጣው ዘይቱ ወይም መድኃኒቱ ብቻ ሳይሆን ጸሎቱም ጭምር ነው። ፈውስን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው። 

ሠ. እግዚአብሔር እንደሚያደርግልህ ማመን አለብህ። የእምነት ጉድለት እግዚአብሔር እንዳይነካህና ፈውስን እንዳታገኝ ሊያደርግ ይችላል። 

እግዚአብሔር ልዕለ-ተፈጥሮአዊ ፈውስ የሚሰጥበት መንገድ በቤተ ክርስቲያን ጸሎትና ለታመመው ሰው በሚሰጠው መድኃኒት ነው። 

4. አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ለአንዳንድ ሰዎች የታመመ ሰው መፈወሱን የሚያውጁበት ወይም የሚያሳውቁበት ችሎታ ይሰጣቸዋል። ይህ የፈውስ መንፈሳዊ ስጦታ በመባል ተገልጿል። 

በ1ኛ ቆሮ. 12፡9-10 ጳውሎስ ሁለት ተአምራዊ የሆኑ መንፈሳዊ ስጦታዎችን ጠቅሷል። የመጀመሪያው ተአምራት የማድረግ ሌላው ደግሞ የፈውስ ስጦታ ነበር። ከሌሎች መንፈሳዊ ስጦታዎች በተለየ ሁኔታ ለእነዚህ ሁለት ስጦታዎች ጳውሎስ የተጠቀመው የብዙ ቁጥር ማለትዎ የፈውሶችና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች እያለ ነው። እንዲህ ያደረገው ለምን ነበር? እነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች በሚሰጠው ሰው ላይ በተደጋጋሚ የመስጠቱንና እንደገና ተመልሶ የመወሰዱን ጉዳይ የሚያመለክት ይመስላል። አትኩሮቱ ሰው ላይ አይደለም። ይህ ስጦታዎች ተብሎ በብዙ የመጠቀሱ ጉዳይ የሚያመለክተው እግዚአብሔር አንድን ሰው ለመፈወስ ሲፈልግ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ላለ ሰው ያንን የታመመ ሰው ለመፈወስ ፈቃዱ እንደሆነ በመግለጥ የታመመው ሰው እንደሚፈወስ እንዲናገር ማድረጉን ነው። ይህ ስጦታ የተሰጠው ሰው ከተናገረ በኋላ ሰውዬው ይፈወሳል። ይህ የፈውስ ስጦታ ግን ከሰውዬው ሊወሰድ ይችላል። በሌላ ሰው ላይ ፈውስ እንዲያውጅ እግዚአብሔር እንደሚናገረው እስኪሰማው ድረስ ጊዜ ሊወስድ ይችላል። 

በቤተ ክርስቲያን ያሉ የታመሙ ሰዎች ሁሉ እንደሚፈወሱ ለመናገር ችሎታ የለውም። ይልቁኑ ይህ ሰው የፈውስን ጉዳይ በተናጠል ሊመለከት ይገባዋል። በእያንዳንዱ ወቅት እግዚአብሔር አንድን ሰው እንደሚፈውስ እንዲናገር መንፈሱን ሊያነሣሣለት ይገባል። እግዚአብሔር ፈውስን ያመጣ ዘንድ በሚፈልግበት ጊዜ ሁሉ በአንድ ሰው እንደሚጠቀም ምንም ዋስትና የለም። ይህን ሊያደርግ ይችላል። ነገር ግን የፈውስ መልእክት ለማምጣት በሌላ ሰውም በቀላሉ መጠቀም ይችላል። ስጦታው የሚሰጠው ለቤተ ክርስቲያን እንጂ ለግለሰቦች አይደለም። (ማስታወሻ፡- የፈውስ መልእክት በአንድ ሰው በኩል መምጣቱ ከሰውየው ማንነት ወይም መንፈሳዊ ታላቅነት አድርገን መመልከት እንደሌለብን ማስታወስ እጅግ አስፈላጊ ግዴታ ነው። የሚፈውሰው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሰውዬው እግዚአብሔር የሚያደርገውን ለሕዝቡ ለማሳወቅ የሚጠቀምበት መሣሪያ ብቻ ነው። የመፈወስ ስጦታ ያለው ሰውዩው ነው ብለን ካሰብን እግዚአብሔርን ሳይሆን ሰውዬውን ማክበር ጀምረናል ማለት ነው። 

እግዚአብሔር ፈውስን ካልሰጠስ? እራሳችንን መርምረን የመንፈስ ቅዱስን ሥራ የሚያግድ ኃጢአት እንደሌለ ካረጋገጥን በኋላ እንኳ ፈውስ ባይመጣልንስ? እግዚአብሔር እንደሚፈውስ በልባችን ፈጽሞ እያመንን እንኳ እግዚአብሔር ካልሠራና ፈውስን ካላመጣስ? መጽሐፍ ቅዱስ እንደምንፈወስ የሚሰጠን ዋስትና የለም። አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር በተሰወረ ፈቃዱ በሽታና ሞት እንዲሆኑ ይፈቅዳል። የእግዚአብሔር ዓላማዎች ሁልጊዜ የምንረዳቸው አይደሉም። ነገር ግን ሁለት እውነቶችን እናውቃለን። በመጀመሪያ እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ ይቆጣጣራል። ስለዚህ በሽታዎች እግዚአብሔር ሳያውቅ ድንገት የሚሆኑ አይደሉም። ሁለተኛ በሽታና ሐዘን እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያስተምርባቸው ሁለት ትላልቅ መሣሪያዎች ናቸው። እግዚአብሔር ጳውሎስን የእግዚአብሔር ጸጋ በድካም ጊዜ በቂ እንደሆነ እስተምሮታል (2ኛ ቆሮ. 12፡7-10)። ስለሆነም በሽታ እግዚአብሔር እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መንፈሳዊ ትምህርቶችን ለእኛ የሚያስተምርበት መሣሪያ ነው። 

ደግሞ በጸሎት መትጋት አለብን። እግዚአብሔር ጸሎታችንን እስኪመልስ ወይም ጥያቄያችንን እንደማይመልስ ነገር ግን በዚያ ሁኔታ ውስጥ እንኖር ዘንድ ችሎታን እንደሚሰጠንና ለክብሩ እንደሚጠቀምበት ዋስትና እስክናገኝ ድረስ ጸሎታችንን መቀጠል አለብን።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading