የሕይወት እንጀራ

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኖስቲካዊነት

This entry is part 24 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ምንድን ነው? 

የክርስቶስ አስተምህሮ አስፈላጊነትና ድነት (ደኅንነት) 

የክርስቶስ መለኮታዊነት 

ኢየሱስ ሁሉን ቻይ እና ሁሉን የሚገዛ ነው

ኢየሱስ ሁሉን አዋቂ ነው 

ኢየሱስ በሁሉም ቦታ ይገኛል 

የኢየሱስ ባሕርይ አይለዋወጥም 

ኢየሱስ ሕይወትን ይሰጣል 

ኢየሱስ ተሰግዶለታል

ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ገልጾአል ፤ ኢየሱስ ይቅርታን መስጠት ይችላል 

ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሥልጣን አለው 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ዓይነት ባሕርይ እንዳለው ገለጸ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ተቀብሏል 

የክርስቶስ አምላክነት በቆላስይስ 1፡15-20 

የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብአዊነት 

ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን እንዴት እናውቃለን? 

የኢየሱስ ሰብአዊ ስሜቶች 

ኃጢአት አልባው የኢየሱስ ሰብአዊነት 

የኢየሱስ ከድንግል መወለድ 

ተሠገዎ በዮሐንስ 1 

ስለ ተሠገዎ በፊልጵስዩስ ምዕራፍ 2 

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኖስቲካዊነት

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ አርዮሳዊነት 

ተሠገዎ፥ ክፍል 2 

ክርስቶስ «አንድ ባሕርይ» አለው የሚለው አስተምህሮ በኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስለ ክርስቶስ ተሠገዎ ያላት ምሥጢረ እምነት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ስለ ክርስቶስ ባሕርይና አካል ያላቸው እምነት

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተገለጠባቸው መልኮችና ምሳሌዎች

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የያህዌ መልአክ (ቅድመ- ተሠገዎ የክርስቶስ መገለጥ)

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሲገለጥ (ቅድመ-ተሠገዎ)

በብሉይ ኪዳን የክርስቶስ ተምሳሌቶች

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

መሢሑ ኢየሱስ

መሢሑ እንደ ንጉሥ 

መሢሑ እንደ ካህን 

መሢሑ እንደ ነቢይ 

መሢሑ እንደ መድኅን 

ኢየሱስ የሰው ልጅ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለ መሆኑ በብሉይና በወንጌላት ውስጥ 

የእግዚአብሔር ልጅ መለኮታዊ ነው። 

በጳውሎስና በዮሐንስ መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መገለጹ 

ኢየሱስ እንደ ጌታ 

የክርስቶስ መቀባት

ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ምሳሌያችን 

ኢየሱስ እና የእግዚአብሔር መንግሥት

የኢየሱስ ሞት 

የክርስቶስ ከፍ ከፍ ማለት (ዕርገት)

የኢየሱስ ዕርገት (ከፍ ከፍ ማለት) 

ኢየሱስ አሁን ያለው ባሕሪና አገልግሎቱ

ክርስቶስ እንደ መካከለኛና እንደ አማላጅ 

የደኅንነት አስፈላጊነት- ሰዎች ኃጢአተኛ በሆነ ባሕርይ ተወለዱ ማለት ምን ማለት ነው?

ኃጢአት ከየት መጣ? 

የኃጢአት ውጤት፡- ሞት 

ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት በደልን ወርሰናል

ሁሉም ሰው የኃጢአት ተግባርን ፈጽሟል 

ኃጢአት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ 

ሕፃናት በእርግጥ ኃጢአትን ለመሥራት ከደረሱበት ጊዜ በፊት የኃጢአት በደለኞች ይባላሉ? 

አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

የደኅንነት ትርጉም፡- ከኃጢአትና ከኃጢአት ውጤቶች ሁሉ መዳን 

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች 

የመዳኛ መንገድ፡- ንስሐ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ 

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

ቅድስና 

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

ኢቢዮናውያን ተነሥተው ኢየሱስ ሰው ብቻ ነበር ብለው ባስተማሩበት በዚያው ጊዜ ከኢቢዮናውያን ለየት ያለ ትምህርት ይዘው የተነሡት ደግሞ ኖስቲካውያን ነበሩ። እነዚህ ኖስቲካውያን በትምህርታቸው ውስጥ በተፈጥሮ የተገኘውና ማንኛውም አካላዊ ነገር ሁሉ ክፉ ነው ብለው። ያምኑ ነበር። ማንኛውም ተፈጥሮአዊ ነገር ወይም ቁስ አካል ክፉ በመሆኑ ምክንያት ኢየሱስ ሰው መሆኑ እውነት ሊሆን አይችልም ብለው ያስተምሩ ነበር። መንፈስ ብቻ መልካም ነው ብለው ያምኑ ነበር። ስለዚህ ኢየሱስ እውነተኛ የሰው አካል ያለው እውነተኛ ሰው ሳይሆን እውነተኛ የሰው አካል ያለው መስሎ የተገለጠ ነው ይሉ ነበር። በእርግጥ ኢየሱስን ድንግል ማርያም አላረገዘችውም፥ ነገር ግን በውስጧ ብቻ አለፈ ብለው ያምኑ ነበር። እንደዚሁም ኖስቲካውያን ወደ ደኅንነት ሊደረስ የሚቻለው በእውቀት ነው ብለው የሚያምኑ ነበሩ። ሰው የበለጠ መንፈሳዊ ምሥጢራትን ባወቀ መጠን ክፉ ከሆነው ከቁስ አካላዊ ዓለም ይርቅና መልካም ወደሆነው መንፈሳዊ ዓለም ይቀርባል ባይ ናቸው። የጥንት ቤተ ክርስቲያን መሪዎች በእነዚህ በኖስቲካውያን ትምህርት ውስጥ ብዙ ጉድለቶችን ሊመለከቱ ችለዋል። – በመጀመሪያ፥ ኢየሱስ በድንግል ማርያም ተፀንሶ የተወለደ፥ እውነተኛ ሰው መሆኑን ይክዳሉ። ሁለተኛ፥ ቁስ አካላዊው ዓለም በራሱና ከራሱ ክፉ ነው ይላሉ። በመጨረሻም፥ ደኅንነት በመሠረቱ የሚገኘው ጥልቅ በሆነ መንፈሳዊ እውቀት ነው ይሉ ነበር። ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ኖስቲካውያንን በዚህ ሐሳዊ ትምህርታቸው የተነሣ አውግዛቸዋለች፤ ነገር ግን ትምህርታቸው ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን የበለጠ መርምራ ወደ ትክክለኛው ግንዛቤ እንድትደርስ በማድረግ ረገድ ረድቷታል። በመጀመሪያ፥ ኢየሱስ በሰው ተመስሎ ብቻ አልታየም፤ ኃጢአት አላደረገም እንጂ በማንኛውም ሁኔታ እርግጠኛ ሰው ነበር። ሁለተኛ፥ ቁስ አካላዊው ዓለም በራሱ ክፉ ኣይደለም። እግዚአብሔር መልካም አድርጎ ፈጥሮታል። ቁስ አካላዊውም ሆነ መንፈሳዊው ዓለም ከኃጢኣት የተነሣ ክፉዎች ናቸው። ሰዎች ኃጢአትን ወደ ቁስ አካላዊው ዓለም ሲያመጡ ብቻ ክፉ ይሆናል። በመጨረሻም፥ ደኅንነት መንፈሳዊ ምሥጢርን ከመገንዘብ በላይ ነው። ስለሆነም ደኅንነት ማለት በክርስቶስ አምኖ በልብ መለወጥ ነው። ደኅንነት ክርስቶስ በመስቀል ላይ በፈጸመልን ተግባር ላይና ፈቃዳችንን ለእግዚአብሔር አሳልፈን በመስጠታችን ላይ የተመሠረተ ነው። 

ጥያቄ፡- ሀ) ኖስቲካውያን ስለ ኢየሱስ ማንነት የሚያምኑት ምን ነበር? ለ) ኖስቲካውያን ስለዚህ ስለተፈጠረው ቁሳዊ ዓለም ምን ያምኑ ነበር? ሐ) ኖስቲካውያን ሰው በምን መንገድ ደኅንነትን ያገኛል ይላሉ? መ) ኖስቲካውያን ከአቢዮናውያን እንዴት ይለያሉ? ሠ) ከእነርሱ የሐሰት ትምህርት የተነሣ ስለ ኢየሱስ ምን ግንዛቤ እየጠራ ግልጽ እየሆነ ሄደ? 

ጥያቄ፡- ሀ) ከኃጢአት በስተቀር፥ ኢየሱስ ሙሉ በሙሉ ሰው ነው የሚለውን እውነታ በመቀበል ረገድ ችግር ያለባቸው የምታውቃቸው ሰዎች ኣሉ? ለ) ስለ እነርሱ የምታውቁትን ጻፉ። ሐህ ክርስቶስ በእውነት ሰው መሆኑን የሚያስተምሩ የትኞቹን ክፍለ ምንባቦች አቅርባችሁ አብራችኋቸው ትወያያላችሁ? 

ጥያቄ፡- ሀ) በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ውስጥ ከሁሉ የበለጠው ነገር መንፈሳዊ ምሥጢራትን መገንዘብ ነው ብለው የሚያምኑ፥ የምታውቁዋቸው ሰዎች አሉ? ለ) ስለ እነዚህ ሰዎች የምታውቁትን ጻፉ። ሐ) በዓለም ያለው ቁስ አካል ሁሉ ክፉ ነው ብለው የሚያምኑ የምታውቋቸው ሰዎች አሉ? ስለ እነዚህ ስዎች ያላችሁን ተሞክሮ ጻፉ። 

ኖስቲካውያን ይህ ቁሳዊ ዓለም ክፉ በመሆኑ ኢየሱስ እውነተኛ ሰው ሊሆን አይችልም ብለው አመኑ። እንደዚሁም ወደ ደኅንነት የሚያደርሰው መንገድ በመንፈሳዊ ምሥጢራት ግንዛቤ ነው አሉ። ዛሬም በኅብረተሰቦቻችን ውስጥ የዚህ ዓይነት ተመሳሳይ እምነት ያላቸው ሰዎች ኣሉ። እንዳንድ ክርስቲያኖች መሆናቸውን እየተናገሩ ኢየሱስ እውነተኛ ስብእና እንዳለው አያምኑም። እነዚህ ወገኖች ኢየሱስ ሥጋ የለበሰ ኣምላክ ነወ ቢሉም፥ እንደ እኛ ሰው እንደ ነበረና ሰብአዊ ነፍስና ሰብአዊ መንፈስ እንደ ነበረው ይክዳሉ። ነገር ግን በዮሐንስ ምዕራፍ 1፥ በፊልጵስዩስ ምዕራፍ 2፥ እንደዚሁም በዕብራውያን ምዕራፍ 2 እና በሌሎችም ክፍለ ምንባቦች ላይ እንደተነዘብነው ኢየሱስ ከኃጢአት በስተቀር እንደ እኛው ሰው መሆኑን ተምረናል። እኛን ለማዳን ሲል ሰው መሆን እንዳስፈለገውም ተመልክተናል። ራሳቸውን ክርስቲያኖች ብለው የሚበሩ በኅብረተሰቦቻችን መካከል የሚገኙ አንዳንድ ሰዎች ጥልቅ የመንፈሳዊ ምሥጢራት ግንዛቤ ካላቸውና መንፈሳዊ ቃላትንም ካወቁ መንፈሳዊ ኃይልና ደኅንነትን የሚያገኙ ይመስላቸዋል። ነገር ግን በሚቀጥለው ትምህርታችን ላይ ደኅንነት በዕውቀት ወይም በልዩ ግንዛቤ የሚገኝ አለመሆኑን እንማራለን። ደኅንነት ፈቃድንና ልብን በመለወጥ ይመጣል።

ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን  በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት 

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading