የሕይወት እንጀራ

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

This entry is part 38 of 197 in the series በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች (FAQs)

በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች (FAQs)

አማላጅነት፦ ትርጉሙ፣ የክርስቶስ ዘላለማዊ ምልጃ እና የአማኞች ድርሻ

መጽሐፍ ቅዱስ፦ መለኮታዊ መነሻው፣ መዋቅሩና በአማኝ ሕይወት ውስጥ ያለው ኃይል

ቅዱሳን፦ ትርጉሙ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱና የቅድስና ሕይወት

ዲያብሎስ፦ ማንነቱ፣ ውድቀቱና በመስቀል ላይ የተሸነፈበት መለኮታዊ ድል

መላእክት፦ ማንነታቸው፣ ተግባራቸውና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓታቸው

ኢየሱስ ክርስቶስ፦ ማንነቱ፣ መለኮታዊ ሥራውና የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

እምነት፦ ትርጉሙ፣ ምንጩና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኃይሉ

አማኑኤል፦ ትርጉሙ፣ ትንቢታዊ መሠረቱና መለኮታዊ ምስጢሩ

ወንጌል፦ ትርጉሙ፣ ማዕከላዊ ሐሳቡና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኃይሉ

እግዚአብሔር፦ ማንነቱ፣ መለኮታዊ ባሕርያቱና የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

ጸጋ፦ ትርጉሙ፣ መገለጫዎቹና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ንስሐ፦ መንፈሳዊ ትርጉሙ፣ አስፈላጊነቱና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ጸሎት፦ መንፈሳዊ ትርጉሙ፣ አስፈላጊነቱና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ጾም፦ መንፈሳዊ ትርጉሙ፣ ዓላማውና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ድነት፦ ትርጉሙ፣ አስፈላጊነቱና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

የክርስቶስ ደም፦ ሥነ-መለኮታዊ ትርጉምና የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

ቅድስና 

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

እምነት 

የመዳኛ መንገድ፡- ንስሐ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ 

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች 

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

ሕፃናት በእርግጥ ኃጢአትን ለመሥራት ከደረሱበት ጊዜ በፊት የኃጢአት በደለኞች ይባላሉ? 

የደኅንነት አስፈላጊነት- ሰዎች ኃጢአተኛ በሆነ ባሕርይ ተወለዱ ማለት ምን ማለት ነው?

ኃጢአት ከየት መጣ? 

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

የደኅንነት ትርጉም፡- ከኃጢአትና ከኃጢአት ውጤቶች ሁሉ መዳን 

ኃጢአት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ 

ሁሉም ሰው የኃጢአት ተግባርን ፈጽሟል 

ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት በደልን ወርሰናል

የኃጢአት ውጤት፡- ሞት 

የደኅንነት አስፈላጊነት – ኃጢአት ምንድን ነው? ክፍል አንድ 

ክርስቶስ እንደ መካከለኛና እንደ አማላጅ 

ኢየሱስ አሁን ያለው ባሕሪና አገልግሎቱ

የኢየሱስ ዕርገት (ከፍ ከፍ ማለት) 

የክርስቶስ ከፍ ከፍ ማለት (ዕርገት)

የኢየሱስ ሞት 

ኢየሱስ እና የእግዚአብሔር መንግሥት

ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ምሳሌያችን 

የክርስቶስ መቀባት

ኢየሱስ እንደ ጌታ 

በጳውሎስና በዮሐንስ መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መገለጹ 

የእግዚአብሔር ልጅ መለኮታዊ ነው። 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለ መሆኑ በብሉይና በወንጌላት ውስጥ 

ኢየሱስ የሰው ልጅ 

መሢሑ እንደ መድኅን 

መሢሑ እንደ ነቢይ 

መሢሑ እንደ ካህን 

መሢሑ እንደ ንጉሥ 

መሢሑ ኢየሱስ

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

በብሉይ ኪዳን የክርስቶስ ተምሳሌቶች

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሲገለጥ (ቅድመ-ተሠገዎ)

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የያህዌ መልአክ (ቅድመ- ተሠገዎ የክርስቶስ መገለጥ)

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተገለጠባቸው መልኮችና ምሳሌዎች

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን 

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2 

ከተስፋቢስነትህ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠሃል?

መጽሐፍ ቅዱስ በውትድርና ሙያ ስለሚያገለግል ክርስቲያን ምን ይላል?

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

መግቢያ

ጌታን እራት ለሚያስፈጽሙ መሪዎች አስተያየት

ክርስቲያኖች በጌታ እራት ላይ ያላቸው የግንዛቤ ልዩነት

አላግባብ የጌታን እራት ስለመውሰድ የተሰጡ ማስጠንቀቂያዎች

ቅዱስ ቁርባን (የጌታ እራት) ማለት ምን ማለት ነው?

የጌታ እራት ሥረ መሠረት

ስለ ጌታ እራት ኢየሱስ የሰጣቸውን በርካታ መመሪያዎች መገንዘብ አስፈላጊ ነው።

የጌታ እራት ሥርዓት እንዴት እንደ ተጀመረ?

«ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት»

የቤተ ክርስቲያን ንጥቀት ገለጣ (ዮሐ. 14፡1-3፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡51-57፣ 1ኛ ተሰ. 4፡13-18)

መንግሥተ ሰማያትና የቅጣት ስፍራ

ትንሣኤዎች

የወደፊቱ ፍርድ

የዘመኑ መጨረሻ

የሺህ ዓመት ግዛት

የፍዳው ዘመን [Tribulation]

ስለ ወደፊቱ ጊዜ ያሉ መሠረታዊ አመለካከቶች

ቤተ ክርስቲያን መቼ ተጀመረች?

ዓለም-አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን

ጥምቀት

የጌታ እራት

የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን በሚለው ፅንሰ አሳብ ውስጥ የሚካተተው ምንድነው?

የድነት (የደኅንነት) ቃላት

የአማኙ ዋስትና

በክርስቶስ ሞት የተገኙ አንዳንድ ጥቅሞች

የክርስቶስ ሞት

ምርጫ ምንን ያካትታል?

የሰው ኃጢአት

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3)

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ

ስለ አጋንንት ትምህርት

ስለ ለይጣን ትምህርት

ስለ መላእክት ትምህርት

አንዳንድ ሰዎች ይቅርታ የማይደረግበት አንድ ኃጢአት አለ ብለው ይፈራሉ። ስለዚህ ይህን ኃጢአት ብናደርግ ደኅንነትን እናጣለን፥ ይቅርታም አይደረግልንም ብለው ይጨነቃሉ። ታዲያ ይህ «ይቅርታ የማይደረግለት ኃጢአት» ተብዬው ምንድን ነው? 

ጥያቄ፡- ማቴ. 2፡22-32 አንብብ። ሀ) ፈሪሳዊያን ኢየሱስን በሰይጣን ኃይል አጋንንትን ያወጣል ማለታቸው በምን ምክንያት ሞኝነት ሆኖ ተቀጠረባቸው? (ቁ 26) ለ) ኢየሱስ አጋንንትን በእግዚአብሔር ኃይል የሚያወጣ ከሆነ፥ ይህ ምንን ያረጋግጣል? (ቁ 28) 

በማቴ. 12፡22-32 ውስጥ ኢየሱስ ጋኔን ያደረበት ዓይነ ሥውርና ዱላ ሰው መፈወሱ ተጽፎአል (ቁ 22)። ይህን ተአምር የተመለከቱ ሰዎች ድርጊቱ መሢሐዊ ድርጊት መሆኑን ወዲያውኑ አስተዋሉ (ቁ 23)። እንደ መዝ (146)፡8፤ ኢሳ. 29፡18፤ 38፡5-6 ካሉት የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች በመነሣት መሢሑ እንዲህ ያሉ ተአምራትን ይፈጽማል ብለው ይጠባበቁ እንደ ነበር ተጽፎአል። ስለዚህ «ይህ ሰው ኢየሱስ በእውነት መሢሑ የዳዊት ልጅ ይሆንን?» ሲሉ በአድናቆት ጠየቁ። ፈሪሳውያን ግን ስለ ኢየሱስ ኃይል ሌላ የሚሉት ነገር ነበራቸው። በብዔል ዜቡል ኃይል ይጠቀማል ሲሉ ከሰሱት፥ ብዔል ዜቡል የሰይጣን ሌላ ስሙ ነው (ቁ 24)። 

ኢየሱስ ግን ፈሪሳውያን የመሠረቱበትን ክስ በሦስት መንገዶች መለሰ። በመጀመሪያ፥ ሰይጣን የራሱን ሥራ የሚያበላሽ ሞኝ አይደለም በማለት ትክክለኛ ያልሆነ ክሳቸውን ውድቅ አደረገው። ሰይጣን የሰውን ሕይወት በውስጡ በሚኖረው አጋንንት የሚያጠፋ ከሆነ አጋንንቱ ከሰውዬው እንዲወጣና ሰውዬውም ሕይወቱ ዳግም ታድሶ ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት እንዲኖረው ፈጽሞ አያደርግም። ይህ ደግሞ በሰውዬው ሕይወት ውስጥ የሚፈጽመውን ክፉ ሥራ የሚገታና መንግሥቱን የሚያፈርስበት ነው። ሰይጣን ደግሞ የራሱ የሆነ አጋንንትን አባሮ በማውጣት በፍጹም መንግሥቱን አያፈርስም አላቸው (ቁ 25-26)። ኢየሱስ በመጀመሪያ ለፈሪሳውያን የመለሰላቸው መልስ ሰይጣን ራሱን ስለማያጠፋ ክሳቸው ሐሰት መሆኑን የሚያመለክት ነው። 

የኢየሱስ ሁለተኛው መልስ እርሱ አጋንንትን ያወጣበት የኃይሉ ታላቅነት፥ ያደረገው ታምራት ከእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ ከሰይጣን አለመሆኑን በማረጋገጥ ክሳቸው ከእውነት የራቀ መሆኑን የሚያሳይ ነበር። እርሱ አጋንንትን ያወጣበትን ኃይል፥ እንዳንድ አይሁዳውያን ከሚፈጽሙት አጋንንትን የማስወጣት ሙከራ ጋር አመዛዝኖታል (ቁ. 27)፡፡ እነዚህ አጋንንትን እናስወጣለን የሚሉ አይሁዳውያን እንደተጠቀሱት የአስቄዋ ሰባት ልጆች ዓይነት ነበሩ (በሐዋ. 19፡13-16)። እነዚህ ሰዎች አጋንንትን በማውጣት ረገድ በመጠኑም ቢሆን የተሳካላቸው ይመስል ነበር። ግን ውጤታቸው የተወሰነና ጊዜያዊ ነበር። ይህ ሊሆን የቻለው እውነተኛ የሆነ መንፈሳዊ ኃይል ስላልነበረባቸው ነው። ከአይሁዶች ይልቅ የኢየሱስ አጋንንት አወጣጥ የሰይጣን መንግሥት በማፈራረስ ረገድ የበረታ ነበር። ታዲያ ፈሪሳውያንና ሕዝቡ የእነርሱ ወገን የሆኑ አጋንንትን እናወጣለን ሲሉ በሰይጣን ኃይል ትጠቀማላችሁ ብለው አይከስሱም ነበር። ግን ተአምራቶቹ በኃይል የተሞሉና የሰይጣንን መንግሥት ደምሳሽ የሆነ ኢየሱስ በሰይጣን ኃይል ትጠቀማለህ ብለው መከሰሳቸው እንዴት ሞኝነት ነበር? ለነገሩ ኢየሱስ አጋንንትን ያወጣ የነበረው በእግዚአብሔር ኃይል ነበር። 

ፈሪሳውያን ተአምራቶቹን ከሰይጣን ኃይል ጋር ማያያዛቸው እንዴት ጅልነት (ሞኝነት) እንደ ነበረ የኢየሱስ የመጀመሪያዎቹ ሁለት መልሶች አረጋግጠዋል። በቁጥር 28 ውስጥ በሚገኘው በሦስተኛው መልሱ ፈሪሳውያን ተአምሩን ካዩ በኋላ ወደ ምን ዓይነት ድምዳሜ መድረስ እንደ ነበረባቸው አሳይቷቸዋል። እርሱ በተለየ ሁኔታ በመንፈስ ቅዱስ የተቀባ መሆኑን ተረድተው፥ «የእግዚአብሔር መንግሥት» እንደ መጣላቸው መቀበል ነበረባቸው። ማለት እርሱ የእስራኤል መሢሕ መሆኑን መገንዘብ ይገባቸው ነበር። ፈሪሳውያን ይህንን ማወቅ ለምን ነበረባቸው? ኢሳ 11፡1-5፤ 42፡1 እና 61፡1፤ እነዚህ ክፍሎች ሁሉ መሢሑ በልዩ ሁኔታ በእግዚአብሔር መንፈስ የተቀባ መሆኑን ይገልጻሉ። ኢየሱስ አጋንንትን የማስወጣት ከፍተኛ ኃይሉ፥ ይህን ልዩ ቅባት ለመቀባቱ ምስክር መሆኑን ተናግሮአል። በሌላ አነጋገር፥ አጋንንትን ሲያስወጣ፥ እርሱም መሢሑ፥ የእግዚአብሔር ንጉሥና የእግዚአብሔርን መንግሥት ወደ ምድር የሚያመጣ መሆኑን ማስመስከሩ በቁጥር 29 ውስጥ፥ አጋንንትን ማውጣቱ የመሢሕነቱ ማረጋገጫ ለመሆኑ ምሳሌ ያቀርባል። 

አንድ ሌባ ወደ ኃይለኛ ሰው ቤት ገብቶ ንብረቱን ለመዝረፍ ያለው ብቸኛ መንገድ አስቀድሞ ኃይለኛውን ሰው ማሰር ነው ይላል። ኢየሱስ ያን ሲል ሰይጣንን በኃይለኛው ሰው ማስመሰሉ ነው። የሰይጣን አጋንንት ተሸነፉ 

ማለት ሰይጣን ራሱ ተሸንፎ ታሰረ፥ ስለታሠረም አጋንንቱን ሊረዳቸው አይችልም ማለት ነው። ሰይጣን በኢየሱስ ከተሸነፈ፥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መሢሕ መሆኑ ነው። ለፈሪሳውያን የሰጠው ሦስተኛው የኢየሱስ መልስ አጋንንትን ያወጣበት ልዩ የሆነ የኃይል አጠቃቀም ሁኔታ እርሱ እግዚአብሔር ተስፋ የሰጠበት መሢሕ መሆኑን እንደሚመሰክር ነበር። 

እነዚህ ፈሪሳውያን የእግዚአብሔርን መሢሕና የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚጠባበቁ መሆናቸውን የሚናገሩ ሰዎች ነበሩ። መሢሑ ሊመጣ እንደሚቀበሉት ያወሱ ነበር። ነገር ግን ስማቴ. 12፡25-29 ውስጥ እንደተጻፈው ኢየሱስ «እኔ መሢሕ መሆኔን በልባችሁ ታውቃላችሁ ይላቸው ነበር። የብሉይ ኪዳንንም ትንቢቶች ታውቃላችሁ። ግልጽ ምስክር ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችንም በዓይናችሁ አይታችኋል። በአእምሮአችሁም እኔ መሢሕ መሆኔን አውቃችሁ ደምድማችኋል። ነገር ግን ይህን ሁሉ እያወቃችሁ አልተቀበላችሁኝም። እኔ መሢሕ መሆኔን እያወቃችሁ አልተቀበላችሁኝም፥ ሥራዩንም የሰይጣን ሥራ አደረጋችሁት» አላቸው። በዚሁ ምዕራፍ ከቁጥር 30-32 ባሉት ቁጥሮች ኢየሱስ ንግግሩን ያጠቃልላል። በልቡ ኢየሱስ ማን እንደሆነ እያወቀ የማይቀበለው የእርሱ ጠላት ነው (ቁ. 30)። ኢየሱስ መሢሕ መሆኑን በግልጽ የሚያረጋግጡ ሥራዎች መንፈስ ቅዱስ በሕይወቱ ውስጥ ሲፈጽም እነዚህ ሥራዎቹም መሢሕ መሆኑን እንደሚመሰክሩ የተረዳ፥ ነገር ግን አሁንም እርሱን በመሢሕነቱ የማይቀበል፥ እርሱ ይቅር አይባልም (ቁ 31)። እናም ኢየሱስ መሢሕ መሆኑን እያወቀ፥ እርሱ ከሰይጣን ነው ብሎ የሚከስውም ይቅርታ ውጭ ነው (ቁ 32)። እንዲህ ያለው ሰው ልቡን ያደነደነ ሰው በመሆኑ ወደ ክርስቶስ መጥቶ እንደ መሢሕ፣ እንደ መድኅንና ጌታ አድርጎ ሊቀበለው አይችልም። 

ስለዚህ በማቴ. 12፡31 ውስጥ፥ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል የተናገረ ይቅር አይባልም የተባለው ምን ማለት ነው? ይህ እንግዲህ መንፈስ ቅዱስን መሳደብ ብቻ አይደለም። እግዚአብሔርን መናቅም ብቻ አይደለም። ወንጌልንም ሰምቶ ክርስቶስን አለመቀበልም ብቻ አይደለም። እነዚህ ሁሉ የከፉ ተግባራት ስለሆኑ እግዚአብሔር ይቀጣቸዋል። ነገር ግን ማቴዎስ በምዕራፍ 12፡31 መንፈስ ቅዱስን ስለ መሳደብ ሲናገር ስለ እነዚህ ጥፋቶች መናገሩ አይደለም። ከጥቅሱ ጭብጥ እንደምንረዳው መንፈስ ቅዱስን መሳደብ ማለት ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ በልዩ ሁኔታ የተቀባ መሢሕና አዳኝ መሆኑን እያወቁ ነገር ግን ልብን አደንድኖ ሆን ብሎ እርሱን አለመቀበልና ሥራውንም መቃወም ነው። ፈሪሳውያን ይህን ባደረጉ ጊዜ፥ ኢየሱስን ላለመቀበል ልባቸውን አጠነከሩ። ስለዚህም የእርሱን ይቅርታ ሳይቀበሉ ቀሩ። 

ዛሬስ ቢሆን አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስን በመሳደብ ይህንኑ ኃጢአት ሊሠራ ይችላል? መልሱ አዎን እና አይደለምም ይሆናል። ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሠራቸውን ታምራት ማንም ሰው ዛሬ በትክክል በግንባር እንደነበረው ሁኔታ ሊያይ አይችልም። ስለሆነም ማንም ሰው ይህን ፈሪሳውያን የሠሩትን ኃጢአት ራሱን መልሶ መሥራት አይችልም። በሌላ በኩል ግን የማያምኑ ሰዎች አሁንም ቢሆን በጣም ተመሳሳይ ኃጢአትን ሊፈጽሙ ይችላሉ። ዛሬም ቢሆን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ስለመሆኑና የዓለም መድኃኒት ስለመሆኑ ብዙ ምልክቶችን ያሳያል። አሁንም የእርሱ መንፈስ በመጽሐፍ ቅዱስ በተሰበከው ቃል፥ በአማኞች ሕይወትና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተደረጉ ታምራት አማካይነት እየሠራ ነው። የማያምን ሰው እነዚህን የኢየሱስ ሥራዎች ተመልክቶ እርሱ በእውነት ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣ ክርስቶስ የዓለም አዳኝ መሆኑን አውቆ ነገር ግን ችላ ቢለውና ባይቀበለው፥ ይህ ሰው ወደ ክርስቶስ ዘንድ በሚያድን እምነት ሊመጣ እስከማይችል ልቡን ያደነድናል። 

እንግዲህ በማቴዎስ ምዕራፍ 12 ውስጥ መንፈስ ቅዱስን በመሳደብ ምክንያት ይቅር የማይባለው ኃጢአት፥ በዚህ ረገድ በማያምኑ ሰዎች የሚፈጸም ኃጢአት ነው እንጂ በእውነት ዳግም በተወለዱ ክርስቲያኖች የሚፈጸም በደል አይደለም። ስለሆነም ኢየሱስ ማን እንደሆነ እያወቁ በአንጻሩ እርሱን ያለመቀበል ኃጢአት ነው። ይቅርታ የማይደረግለት ኃጢአት ነው የተባለበት ምክንያት አንድ ሰው ክርስቶስ ማን እንደሆነ ካወቀ በኋላ ችላ ቢል፥ ልቡን ፍጹም ስለሚያደነድን እርሱን እንደ አዳኙ ለመቀበል በምንም ዓይነት አይመርጥም ማለት ነው። አንድ ሰው ሌላው ሰው ይህን ኃጢአት መፈጸሙን ሊያውቅ ይችላል? ኢየሱስ ፈሪሳውያን ይህን ኃጢአት መፈጸማቸውን አውቆ ነበር። ነገር ግን ዛሬ አንድ ሰው ሌላው ሰው ይህን ኃጢአት ለመፈጸሙ እርግጠኛ ሊሆን አይችልም። በሰብአዊና በውስን ግንዛቤአችን የሌላውን ሰው ልብና አእምሮ ማወቅ አንችልም። አንድ ሰው የክርስቶስን ማንነት ፍጹም ተገንዝቦ ሲያበቃ፥ ነገር ግን ከናካቴው ችላ በማለት ሳይቀበለው መቅረቱን ጠንቅቀን ማወቅ ፈጽሞ ያዳግተናል። ስለዚህ አንድ ወዳጃችን የሆነ ሰው ወይም ቤተሰብ ክርስቶስን ባለመቀበሉ ተስፋ መቁረጥ አይገባንም። በቃላችንና በተቀደሰ ሕይወት መመስከራችንን መቀጠልና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ወደ እራሱ መልሶ እንዲያመጣቸው ጸሎታችንን አለማቋረጥ ያስፈልገናል። በመሆኑም ማንም በእውነት ዳግም የተወለደ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስን ስለ ተሳደብኩ ይቅር የማይባል ኃጢአት ሠርቻለሁ ብሎ ሊፈራና ሊጨነቅ አይገባም።

ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች (FAQs)

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች  አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading