የሕይወት እንጀራ

ከተስፋቢስነትህ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠሃል?

This entry is part 86 of 197 in the series በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች (FAQs)

በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች (FAQs)

አማላጅነት፦ ትርጉሙ፣ የክርስቶስ ዘላለማዊ ምልጃ እና የአማኞች ድርሻ

መጽሐፍ ቅዱስ፦ መለኮታዊ መነሻው፣ መዋቅሩና በአማኝ ሕይወት ውስጥ ያለው ኃይል

ቅዱሳን፦ ትርጉሙ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱና የቅድስና ሕይወት

ዲያብሎስ፦ ማንነቱ፣ ውድቀቱና በመስቀል ላይ የተሸነፈበት መለኮታዊ ድል

መላእክት፦ ማንነታቸው፣ ተግባራቸውና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓታቸው

ኢየሱስ ክርስቶስ፦ ማንነቱ፣ መለኮታዊ ሥራውና የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

እምነት፦ ትርጉሙ፣ ምንጩና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኃይሉ

አማኑኤል፦ ትርጉሙ፣ ትንቢታዊ መሠረቱና መለኮታዊ ምስጢሩ

ወንጌል፦ ትርጉሙ፣ ማዕከላዊ ሐሳቡና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኃይሉ

እግዚአብሔር፦ ማንነቱ፣ መለኮታዊ ባሕርያቱና የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

ጸጋ፦ ትርጉሙ፣ መገለጫዎቹና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ንስሐ፦ መንፈሳዊ ትርጉሙ፣ አስፈላጊነቱና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ጸሎት፦ መንፈሳዊ ትርጉሙ፣ አስፈላጊነቱና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ጾም፦ መንፈሳዊ ትርጉሙ፣ ዓላማውና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

ድነት፦ ትርጉሙ፣ አስፈላጊነቱና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቱ

የክርስቶስ ደም፦ ሥነ-መለኮታዊ ትርጉምና የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

ቅድስና 

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

እምነት 

የመዳኛ መንገድ፡- ንስሐ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ 

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች 

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

ሕፃናት በእርግጥ ኃጢአትን ለመሥራት ከደረሱበት ጊዜ በፊት የኃጢአት በደለኞች ይባላሉ? 

የደኅንነት አስፈላጊነት- ሰዎች ኃጢአተኛ በሆነ ባሕርይ ተወለዱ ማለት ምን ማለት ነው?

ኃጢአት ከየት መጣ? 

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

የደኅንነት ትርጉም፡- ከኃጢአትና ከኃጢአት ውጤቶች ሁሉ መዳን 

ኃጢአት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ 

ሁሉም ሰው የኃጢአት ተግባርን ፈጽሟል 

ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት በደልን ወርሰናል

የኃጢአት ውጤት፡- ሞት 

የደኅንነት አስፈላጊነት – ኃጢአት ምንድን ነው? ክፍል አንድ 

ክርስቶስ እንደ መካከለኛና እንደ አማላጅ 

ኢየሱስ አሁን ያለው ባሕሪና አገልግሎቱ

የኢየሱስ ዕርገት (ከፍ ከፍ ማለት) 

የክርስቶስ ከፍ ከፍ ማለት (ዕርገት)

የኢየሱስ ሞት 

ኢየሱስ እና የእግዚአብሔር መንግሥት

ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ምሳሌያችን 

የክርስቶስ መቀባት

ኢየሱስ እንደ ጌታ 

በጳውሎስና በዮሐንስ መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መገለጹ 

የእግዚአብሔር ልጅ መለኮታዊ ነው። 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለ መሆኑ በብሉይና በወንጌላት ውስጥ 

ኢየሱስ የሰው ልጅ 

መሢሑ እንደ መድኅን 

መሢሑ እንደ ነቢይ 

መሢሑ እንደ ካህን 

መሢሑ እንደ ንጉሥ 

መሢሑ ኢየሱስ

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

በብሉይ ኪዳን የክርስቶስ ተምሳሌቶች

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሲገለጥ (ቅድመ-ተሠገዎ)

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የያህዌ መልአክ (ቅድመ- ተሠገዎ የክርስቶስ መገለጥ)

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተገለጠባቸው መልኮችና ምሳሌዎች

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን 

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2 

ከተስፋቢስነትህ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠሃል?

መጽሐፍ ቅዱስ በውትድርና ሙያ ስለሚያገለግል ክርስቲያን ምን ይላል?

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

መግቢያ

ጌታን እራት ለሚያስፈጽሙ መሪዎች አስተያየት

ክርስቲያኖች በጌታ እራት ላይ ያላቸው የግንዛቤ ልዩነት

አላግባብ የጌታን እራት ስለመውሰድ የተሰጡ ማስጠንቀቂያዎች

ቅዱስ ቁርባን (የጌታ እራት) ማለት ምን ማለት ነው?

የጌታ እራት ሥረ መሠረት

ስለ ጌታ እራት ኢየሱስ የሰጣቸውን በርካታ መመሪያዎች መገንዘብ አስፈላጊ ነው።

የጌታ እራት ሥርዓት እንዴት እንደ ተጀመረ?

«ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት»

የቤተ ክርስቲያን ንጥቀት ገለጣ (ዮሐ. 14፡1-3፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡51-57፣ 1ኛ ተሰ. 4፡13-18)

መንግሥተ ሰማያትና የቅጣት ስፍራ

ትንሣኤዎች

የወደፊቱ ፍርድ

የዘመኑ መጨረሻ

የሺህ ዓመት ግዛት

የፍዳው ዘመን [Tribulation]

ስለ ወደፊቱ ጊዜ ያሉ መሠረታዊ አመለካከቶች

ቤተ ክርስቲያን መቼ ተጀመረች?

ዓለም-አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን

ጥምቀት

የጌታ እራት

የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች

አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን በሚለው ፅንሰ አሳብ ውስጥ የሚካተተው ምንድነው?

የድነት (የደኅንነት) ቃላት

የአማኙ ዋስትና

በክርስቶስ ሞት የተገኙ አንዳንድ ጥቅሞች

የክርስቶስ ሞት

ምርጫ ምንን ያካትታል?

የሰው ኃጢአት

የሰው ልጅ ውድቀትና የታሪክ መለወጥ (ዘፍጥረት 3)

የሰው ተፈጥሮ፡- የሰው ባሕርይ

ስለ አጋንንት ትምህርት

ስለ ለይጣን ትምህርት

ስለ መላእክት ትምህርት

ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በድንገት በሮሜ 7 ውስጥ በሚገኘው አይነት የሕይወት ልምድ ሲገቡ ቢያገኙም ለምን እንደገቡ ግን መገንዘብ ሲቸግራቸው ይታያል፡፡ በተስፋ እና ድል የተሞላውን የሮሜ 6 ምዕራፍ ካነበቡ በኋላ በፊታቸው በሮሜ 7 ላይ እንደተጠቀሰው አይነት የሕይወት ልምምድ ሊገጥማቸው እንደሚችል ከቶዉኑም አይጠብቁም፡፡ ይህን አስበው ብዙ ሳይቆዩ ራሳቸውን በዚህ ታሪክ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ለዚህ ክስተት ማብራሪያው ምንድን ነው?  

በመጀመሪያ፣ በሮሜ 6 ላይ የተገለፀው እና እኛ ከክርስቶስ ጋር የመሞታችን ሃቅ ላለን የኃጢአት ጥያቄዎች ሁሉ በቂ ምላሽ በመሆኑ ላይ ምንም ብዥታ ሊኖረን አይገባም፡፡ ሞታችን እና ከሞታችን ጋር ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮች በምዕራፉ በተሟላ ዝርዝር ባለመቅረቡ በምዕራፍ 7 ውስጥ ለቀረበው መንፈሳዊ እውነታ እንግዶች እንድንሆን ሊያደርገን ይችላል፡፡ ሮሜ 7 በሮሜ 6፡14 ውስጥ የተገለጸውን እውነት በጥልቀት እንድንረዳ እና በቂ ግንዛቤ እንድንይዝ የሚረዳን ምዕራፍ ነው፡፡ ጥቅሱ እንዲህ ይነበባል፡- “ኃጢአት አይገዛችሁምና፤ ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደላችሁምና።” እዚህ ላይ ያለው ትልቁ ችግር በርካታ ክርስቲያኖች ከሕግ መፈታት (ሮሜ 7፡6) ወይም አርነት መውጣት ማለት ምን ማለት እንደሆነ አለመገንዘባቸው ነው፡፡ ይህን ለመረዳት አስቀድመን የሕግን ምንንነት ማወቅ ይገባናል፡፡

ጸጋ ማለት እግዚአብሔር ለእኔ የሚያደርገው ነገር ሲሆን ሕግ ደግሞ እኔ ለእግዚአብሔር የማደርገው ነገር ነው። እግዚአብሔር እንድፈጽመው ወይም እንዳደርገው የሚጠይቀኝ ቅዱስና እና ጻድቅ ፍላጎቶች አሉት፤ እርሱም ሕግ ይባላል። ሕግ ማለት እግዚአብሔር እንድፈጽመው ከእኔ የሚጠብቀው ቅዱስ ፍላጎት ከሆነ ከሕግ አርነት ወይም ነጻነት መውጣት ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ይህን ቅዱስ ፍላጎቱን እኔ እንዳሟላ መጠበቅ ትቶ ራሱ አሟልቷል ማለት ነው፡፡ ሕግ እግዚአብሔር ለእርሱ አንድ ነገር እንዳደርግ እንደሚጥብቅ የሚገልጽ ከሆነ፤ ከሕግ ነጻ መውጣት ደግሞ ከእኔ ምንም እንደማይጠብቅ ያመለክታል። እናም በጸጋው እሱ ራሱ ያደርገዋል።  እኔ (ማለትም በሥጋዬ) የሕግን ትዕዛዝ ለመፈጸም ከቶ አልችልም (ሮሜ 7፡14)፡፡ በዚህ በሰረት በሮሜ 7 ላይ ያለው ሰው ችግር በስጋው ለእግዚአብሔር የሕግን ትዕዛዝ ለመፈጸም መታገሉ መሆኑን እንረዳለን። በእንዲህ ሁኔታ (ማለትም በሥጋህ) የሕግን ትዕዛዝ በመፈጸም እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት በምትንቀሳቀስበት ቅስበት ራስህን ከሕግ በታች ታደርጋለ፡፡ ከዛም የሮሜ 7 ሰውዬን የሕይወት ልምምድ መለማመድ ትጀምራለህ፡፡  

እዚህ ላይ አንድ ነገር በጊዜ ግልጽ መሆን አለበት፡፡ ችግሩ እኔ እንጂ ሕጉ አይደለም፡፡ “…ሕጉ ቅዱስ ነው ትእዛዚቱም ቅድስትና ጻድቅት በጎም ናት” ( ሮም 7:12 )፡፡ በሕጉ ላይ ምንም ችግር የለም፣ ችግሩ እኔ ጋር ነው። የሕግ ፍላጎቶች ጽድቅ ናቸው፤ ነገር ግን እንዲፈጽማቸው የተጠየቀው ሰው ዓመፀኛ ነው። ችግሩ፣ ሕጉ የጠየቀው ጥያቄ ተገቢ አለመሆኑ ሳይሆን ፈጻሚው አካል ሊያደርጋቸው አለመቻሉ ነው፡፡ 

“ከኃጢአት በታች ልሆን የተሸጥሁ” ሰው ነኝ (ሮሜ. 7:14)፡፡ ኃጢአት በእኔ ላይ የበላይ ነው (ይገዛኛል)። ሕግ ከእኔ የሚጠይቀው አንዳች ነገር እስከሌለ ድረስ ጤነኛ መስዬ መኖር እችላለው፤ ሕጉ እንዳደርገው የሚፈልገው ነገር በተገለጠ ጊዜ ግን የእኔም አመጻ (ሃጢአት) አብሮ ይገለጣል፡፡ የተደበቀው ማንነቴ ወደ ብርሃን ይወጣል፡፡

ደንባራ አገልጋይ ቢኖርህና ያለሥራ ተቀምጦ ቢውል ደንባራነቱ ከእርሱ ጋር ቢሆንም ማንነቱ ሳይገለጥ ይቆያል፡፡ ቀኑን ሙሉ ምንም ሳያደርግ ከተቀመጠ ምንም የጠቀመህ ነገር ባኖርም ቢያንስ ግን ሲደናበር ከሚያጠፋው ጥፋት ተጠብቀሃል፡፡ “ጊዜ አታባክን፤ ተነሳና አንድ ነገር አድርግ” ያልከው እለት ወዲያውኑ የተደበቀው ችግር መገለጥ ይጀምራል፡፡ ገና ሲነሳ ከወንበሩ ጋር እግሩ ይላተማል፣ ጥቂት እንደተራመደ በመንገዱ ላይ ካለ ነገር ጋር ይጋጫል፤ ብዙ ሳይቆይ ሲደናበር ውድ እቃህን ከእጁ ላይ ጥሎ ይሰብርብሃል፡፡ እንዲሰራ ሳትጠይቀው ቀርተህ ቢሆን ምንም እንኳ ሊጠቅምህ ባይችልም ይህን ሁሉ ችግር አይፈጸምም፡፡ እንዲያደርግልህ የጠየከው ጥያቄ ከሌለ ደንባራነቱ በጭራሽ አይታወቅም፡፡ ተነስቶ እንዲሰራ መጠየቁ ትክክል ቢሆንም የተጠየቀው ሰው ግን ጥያቄዎን በአግባቡ ለመፈጸም የማያስችል መሰረታዊ ችግር አለበት፡፡ ተቀምጦም ሆነ ሲሰራ ሰውየው ያው ደንባራ ነው፡፡ ነገር ግን ደንባራነቱን የገለጠው ትዕዛዙን ተከትሎ ነው፡፡

ሁላችንም በተፈጥሮ ኃጢአተኞች ነን። እግዚአብሔር ከእኛ ምንም ካልጠየቀ፤ እኛም ሆነ በእኛ ውስጥ ያለው ነገር ሁሉ ጥሩ መስሎ ሊኖር ይችላል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ከእኛ አንዳች ነገር በጠየቀ ጊዜ (ሕግ) ሃጢአተኛ ተፈጥሮአችን ራሱን መግለጥ ይጀምራል፡፡ በሌላ አነጋገር ሕጉ ድካማችንን በግልጽ ያሳያል። ዝም ብለህ እንድቀመጥ ከፈቀድክልኝ፣ ሁሉ ነገር ሰላም ሊመስል ይችላል፡፡ እንድሰራ ባዘዝከኝ ጊዜ ግን፣ ጥፋቴን መመልከት ትጀምራለህ፡፡ ሁለተኛ እድል ብትሰጠኝም ማጥፋቴን አልተውም፡፡ ቅዱሱን የእግዚአብሔርን ሕግ ለመፈጸም ስነሳ የሚፈጠረውm ይኸው ነው፡፡ ሕጉ በውስጤ ያለውን ማንነቴን መግለጥ ይጀምራል፡፡

እግዚአብሔር እኔ ማን እንደሆንኩ ያውቃል፡፡ ከራስ ጸጉሬ እስከ እግሬ ጥፍሬ በኃጢአት የተሞላሁ እንደሆነም  ያውቃል፡፡ ምንም ማድረግ እንደማልችል ለሱ የተሰወረ ሃቅ አይደለም፡፡ ችግሩ እኔ ይህን ሃቅ አለማወቄ ነው። እኔን ጨምሮ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ መሰረታዊ ግንዛቤ ቢኖረኝም ፍጹም ተስፋ ቢስ ሃጢአተኛ መሆኔን ግን በቀላሉ አልገነዘብም፡፡ ለአብነት፣ ራሴን ከአንዳንድ “የከፉ” ሃጢአተኞች ይልቅ የተሻልኩ አድርጌ ልመለከት እችላለው፡፡ በመሆኑም፣ እግዚአብሔር ፍጹም ተስፋ ቢስ እና ደካማ እንደሆንኩ ወደምገነዘብበት ሁኔታ ሊያመጣኝ ይፈልጋል፡፡ የሕግን ትዕዛዝ ከመፈጸም አኳያ ምን ያህል ጎስቋሎች ወይም ደካሞች እንደሆንን የምንለውን ያህል እውነታውን አናውቀውም፡፡  እናም፣ እግዚአብሔር ከዚህ መራር እውነታ ጋር እንድንፋጠጥ እና እንድንቀበል አንድ መሳሪያ አዘጋጅቷል፤ ያም መሳሪያ ሕግ ይባላል፡፡ በሕጉ ባይሆን ኖሮ ምን ያህል ደካሞች እና ተስፋ ቢሶች መሆናችንን ባላወቅን ነበር፡፡ ጳውሎስ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር። በሮሜ 7፡7 ላይ፣ “…በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና” በማለት ይህን መረዳቱን ግልጽ ያደርግልናል፡፡ ከሌሎቹ ትዕዛዛት አንጻር ጳውሎስ የነበረው የሕይወት ልምምድ ምን ይምሰል ምን፣ ማንነቱን ያውቅ ዘንድ ፊት ለፊት የተላተመው ከአሥረኛው ትእዛዝ ጋር እንደነበር ተገልጿል፡፡ በዚህ ትዕዛዝ አማካኝነት ጳውሎስ ከድካሙ እና ተስፋቢስነቱ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጠ!

አብዝተን ሕጉን ለመጠበቅ በሞከርን ቁጥር አብዝተን በመውደቅ ሕይወታችን ለሮሜ 7 ልምምድ ቅርብ መሆኑን እየተረዳን እንመጣለን፡፡ የዚህ አላማው፣ በራሳችን የሕጉን ትዕዛዛት ልንፈጽም የማንችል ተስፋ ቢሶችና ደካሞች መሆናችንን ማስገንዘብ ነው፡፡ ከላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር ይህን ማንነታችንን ጠንቅቆ ያውቀዋል፤ እኛ ግን አናውቅም፡፡ ስለዚህም እግዚአብሔር እጅግ አስቸጋሪ እና ህመም ባለባቸው ሁኔታዎች ውስጥ እንድናልፍ በመፍቀድ ከዚህ እውነታ ጋር ፊት ለፊት እንድንላተም ብሎም እውነታውን እንድንቀበል ያደርጋል፡፡ እግዚአብሔር ሕግን የሰጠን ወደዚህ እውነት እንድንደርስ ነው።

ስለዚህ በአክብሮት እና በጥንቃቄ እንዲህ ማለት እንችላለን፡- እግዚአብሔር ሕግን እንድንጠብቀው ሳይሆን እንድንጥሰው ነው የሰጠን። ሕጉን መፈጸም እንደማንችል በእርግጥ ያውቃል፡፡ ስረ-መሰረታችን እጅግ የተበላሸና እና ከእኛ አንዳች በጎ ነገር እንደማይገኝ ያውቃል (ሮሜ 7፡18)፡፡ ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ በኩል ሊጸድቅ አይችልም፡፡ ሕግ ሊያጽድቀን የተሰጠ ሳይሆን “በደል እንዲበዛ” የተሰጠ ነውና (ሮሜ 5፡20)፡፡ ሕግ የተሰጠው እንድንፈጽመው ሳይሆን ሕግ ተላላፊዎች መሆናችንን ለማስረዳት ነው፡፡  “…በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና። ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ፤ ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና። እኔም ዱሮ ያለ ሕግ ሕያው ነበርሁ፤ ትእዛዝ በመጣች ጊዜ ግን ኃጢአት ሕያው ሆነ እኔም ሞትሁ፤” (ሮሜ. 7:7-9)፡፡ ሕግ፣ እውነተኛውን ተፈጥሮአችንን ከተደበቀበት ጎሬ አውጥቶ ወደ አደባባይ ያወጣዋል፡፡ በሚያሳዝን ሁኔታ ለራሳችን ያለን ግምት የተጋነነ እና እጅግ ኩሩዎች ስለሆንን እግዚአብሔር ይህን ውሸት ገልጦ ለማሳየት እና ሃጢአተኞች እና ደካሞች መሆናችንን ለማስረዳት ሕግን ይጠቀማል፡፡ 

ሕጉ እንደምንተላላፈው እየታወቀ የተሰጠ እንጂ ይፈጽሙታል በሚል ተስፋ የተሰጠ አይደለም፡፡ ለመጠበቅ በምናደርገው ትግል ውስጥ ተላልፈነው ስናበቃ በውስጣችን ያለውን ማንነት ከገለጠ የሕግ አላማ ተሳካ ማለት ነው፡፡ ሕጉ፣ “በእምነት እንጸድቅ ዘንድ … ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን…” ነው (ገላ. 3፡24)።

አዳነው ዲሮ ዳባ

በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች (FAQs)

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2  መጽሐፍ ቅዱስ በውትድርና ሙያ ስለሚያገለግል ክርስቲያን ምን ይላል?

6 thoughts on “ከተስፋቢስነትህ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠሃል?”

  1. ተባርኮ

    On Thu, Nov 11, 2021, 10:40 PM ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት wrote:

    > tsegaewnet posted: ” ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በድንገት ወደ በሮሜ 7 ውስጥ በሚገኘው አይነት የሕይወት
    > ልምድ ሲገቡ ቢያገኙም ለምን እንደገቡ ግን መገንዘብ ሲቸግራቸው ይታያል፡፡ በተስፋ እና ድል የተሞላውን የሮሜ 6 ምዕራፍ
    > ካነበቡ በኋላ በፊታቸው በሮሜ 7 ላይ እንደተጠቀሰው አይነት የሕይወት ልምምድ ሊገጥማቸው እንደሚችል ከቶዉኑም
    > አይጠብቁም፡፡ ይህን አስበው ብዙ ሳይቆዩ ራሳቸውን በዚህ ታሪክ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ለዚህ ”
    >

  2. Thank you !
    With blessings

    On Friday, November 12, 2021, ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት wrote:

    > tsegaewnet posted: ” ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በድንገት ወደ በሮሜ 7 ውስጥ በሚገኘው አይነት የሕይወት
    > ልምድ ሲገቡ ቢያገኙም ለምን እንደገቡ ግን መገንዘብ ሲቸግራቸው ይታያል፡፡ በተስፋ እና ድል የተሞላውን የሮሜ 6 ምዕራፍ
    > ካነበቡ በኋላ በፊታቸው በሮሜ 7 ላይ እንደተጠቀሰው አይነት የሕይወት ልምምድ ሊገጥማቸው እንደሚችል ከቶዉኑም
    > አይጠብቁም፡፡ ይህን አስበው ብዙ ሳይቆዩ ራሳቸውን በዚህ ታሪክ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ለዚህ ”
    >

  3. በጣም ደስ የሚል ቃል አካፈልከን፡፡ ዉስጤ ሀሴት አደረገ፡፡ እዉነት ለመናገር በሮሜ 6 እና 7 ላይ ያለዉ ቃል ሁል ጊዜ በትክክለኛ መንገድ አልረዳዉም፡፡ ግራ ይገባኛል፡፡ ቤተክርስቲያንም ይህንን ቃል በግልጽ እና በዝርዝር ለምዕመናን አታስረዳም፡፡ ዛሬ ከአንተ የሰማሁት ትምህርት ልቤን መልሶታል፡፡ ደስ ብሎኝል፡፡ ብዥ ያለብኝን በእግዚአብሔር ቃል ፍንትዉ አድርገህ አሳይተህኝል፡፡ እግዚአብሔር ይባርክህ፡፡

  4. የጌታ ሰላም ለእናንተ ይሁን ! ወደ ጥያቄ ልግባ አገልጋይ ነኝ! መድረክ ላይ ለሎች ስያገለግሉ ውስጤ በቃሉ ይቃጠላል ።
    ከአገልጋዩ የተለየ መገለጥ ይመጣልኛል ። ነገር ግን እነ መድረክ ስወጣ በአገልግሎተ አልረካም ። እቤት መጽሐፍ ቅዱስ
    ሳነብ ሳሰላስል እረካለሁ። ነገር ግን መድረክ ላይ ለሎችን ሳገለግል እርካታውን አጣዋለሁ። ምን ይሁን ምክንያቱ??

    On Thu, Nov 11, 2021, 10:40 PM ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት wrote:

    > tsegaewnet posted: ” ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በድንገት ወደ በሮሜ 7 ውስጥ በሚገኘው አይነት የሕይወት
    > ልምድ ሲገቡ ቢያገኙም ለምን እንደገቡ ግን መገንዘብ ሲቸግራቸው ይታያል፡፡ በተስፋ እና ድል የተሞላውን የሮሜ 6 ምዕራፍ
    > ካነበቡ በኋላ በፊታቸው በሮሜ 7 ላይ እንደተጠቀሰው አይነት የሕይወት ልምምድ ሊገጥማቸው እንደሚችል ከቶዉኑም
    > አይጠብቁም፡፡ ይህን አስበው ብዙ ሳይቆዩ ራሳቸውን በዚህ ታሪክ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ለዚህ ”
    >

    1. ጌታ ይባርክህ! ይህ በብዙ ቅን አገልጋዮች ሕይወት ውስጥ የሚታይ፣ ነገር ግን ትኩረት የሚሻ መንፈሳዊ ጉዞ ነው። ለቃሉ ያለህ መቃጠልና በቤትህ የምታገኘው በረከት እጅግ መልካም ነገር ነው።
      መድረክ ላይ በምትወጣበት ጊዜ እርካታ የምታጣበት ምክንያቶች ጥቂቶቹ እነዚህ ሊሆኑ ይችላሉ፦
      የትኩረት አቅጣጫ መለወጥ (Focus Shift)፦ ቤት ውስጥ ስታጠና ትኩረትህ “ጌታና እኔ” ላይ ብቻ ነው። መድረክ ላይ ግን ባለማወቅ ትኩረትህ ወደ “ሰው” (ሰው ምን ይለኛል? እንዴት አቀርበው ይሆን? በሚገባ ተረድተውኛል?) ወደሚል ስጋት ሊቀየር ይችላል። ይህም ያንን የቅርብ ህብረት ያደበዝዘዋል።
      የመገለጥና የማድረስ (Delivery) ልዩነት፦ መገለጥን መቀበልና ያንን የተቀበሉትን መገለጥ ለሰው በሚሆን ቋንቋ አቀናጅቶ ማድረስ የተለያዩ ችሎታዎች ናቸው። የተቀበልከው ትልቅ ሆኖ ሳለ፣ በንግግር የገለጽከው ግን ትንሽ እንደሆነ ሲሰማህ “ያልረካህ” ይመስልሃል።
      ከመጠን ያለፈ ግምት (High Expectations)፦ በቤትህ የምታገኘውን ያንን ጥልቅ ሰላምና መገለጥ መድረክ ላይም ልክ በዚያው ልክ ካልደገምኩት ብለህ ራስህን ስለምታስጨንቅ፣ አገልግሎቱ አልቆ ስትወርድ “የፈለግኩትን ያህል አልነካኋቸውም” የሚል የጥላቻ ስሜት (Self-criticism) ሊመጣብህ ይችላል።
      የመድረክ ፍርሃት (Stage Anxiety)፦ ምንም እንኳ አገልጋይ ብትሆንም፣ መድረክ ላይ ያለው መንፈሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫና ውስጣዊ ነጻነትህን (Inner freedom) ሊጋርደው ይችላል።
      ምን ብታደርግ ይሻላል?
      ተቀባይነትን ከጌታ ብቻ ፈልግ፦ መድረክ ላይ ስትወጣ ሰዎችን ሳይሆን፣ ያንን በቤትህ የምታወራውን ጌታን እያየህ ለማውራት ሞክር።
      ዝግጅትህን በጸሎት አሟላ፦ መገለጡ ስላለህ ብቻ ሳይሆን፣ ያንን መገለጥ ለሰዎች እንዴት እንደምታፈሰው መንፈስ ቅዱስ እንዲረዳህ በዝግጅት ጊዜህ አብዝተህ ጸልይ።
      ውጤቱን ለጌታ ስጥ፦ አንተ መዝራት እንጂ ማብቀል አትችልም። “ያልረካሁበት” አገልግሎት እንኳ በአንድ ሰው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል እመን።
      አንተ ባልረካህበት አገልግሎት ውስጥ ጌታ የረካባቸው ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አስብ፡፡

  5. አገልግሎታችሁ የተባረከ ይሁን

    On Thu, Nov 11, 2021, 10:40 PM ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት wrote:

    > tsegaewnet posted: ” ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በድንገት ወደ በሮሜ 7 ውስጥ በሚገኘው አይነት የሕይወት
    > ልምድ ሲገቡ ቢያገኙም ለምን እንደገቡ ግን መገንዘብ ሲቸግራቸው ይታያል፡፡ በተስፋ እና ድል የተሞላውን የሮሜ 6 ምዕራፍ
    > ካነበቡ በኋላ በፊታቸው በሮሜ 7 ላይ እንደተጠቀሰው አይነት የሕይወት ልምምድ ሊገጥማቸው እንደሚችል ከቶዉኑም
    > አይጠብቁም፡፡ ይህን አስበው ብዙ ሳይቆዩ ራሳቸውን በዚህ ታሪክ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ለዚህ ”
    >

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading