Site icon

ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሥልጣን አለው 

ጥያቄ፡– ማርቆስ 2፡23-27 አንብቡ። ሀ) በዚህ ክፍለ ምንባብ ውስጥ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ የሃይማኖት መሪዎችን ያስቀየመ ምን ተግባር ፈጸሙ? ለ) ይህ በምን ምክንያት የሃይማኖት መሪዎችን እስከፋ? ሐ) ኢየሱስ በቁጥር 28 ላይ ስለ 

ምን ሥልጣን ተናገረ? 

በማርቆስ 2፡23-27 ድረስ እንደተነገረው፥ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በመጓዝ ላይ ሳሉ እንደ አገሩ ባሕል በመንገድ ዳር ካገኙት እሸት ጥቂት ወስደው በሉ። ሆኖም ይህን ያደረጉበት ቀን ሰንበት ነበር። በኢየሱስ ዘመን የነበሩ የሃይማኖት መሪዎች ደግሞ በሰንበት ቀን እሸት ተቀጥፎ መበላት የለበትም ባይ ነበሩ። ስለዚህ ይህ እንዳይደረግ ከልክለዋል። ኢየሱስ ግን ደቀ 

መዛሙርቱ ከእሸቱ ወስደው እንዲበሉ ፈቀደላቸው። በዚህ ምክንያት ፈሪሳውያን ሕግ አፍርሷል ብለው በከሰሱት ጊዜ ኢየሱስ ስለ ሰንበት የሚናገረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የመተርጎም ሥልጣኑን ተጠቀመ። የሰንበት ሕግ የተሰጠው በእግዚአብሔር በራሱ ነው (ዘፀአት 20፡8-10። ኢየሱስ ሕጉን ተረጎመ ማለት እርሱ ከሃይማኖት መሪዎች ባላይ ነው እንደ ማለት ነው። ስለዚህ በሰንበት ቀን ምን መሠራት እንዳለበት ሊናገር፥ 

መለኮታዊ ሥልጣኑን መግለጹ ነበር። እርሱ የሚናገረው ሥልጣን ምን እንደሆነ በእርግጥ ይነዘቡ ዘንድ በቁጥር 28 ላይ፥ «የሰው ልጅ ለሰንበት ጌታዋ ነው» አለ። ኢየሱስ ራሱን «የሰው ልጅ ብሎ ሲጠራ ምን ማለቱ እንደሆነ በሌላ ክፍለ ትምህርት እናጠናለን። ይህ የኢየሱስ የተለመደ መጠሪያ ነው። በዚህ አገላለጹ ስለ እራሱ እንደሚናገር ገባቸው። እዚህ ላይ ኢየሱስ፤ «የሰው ልጅ ለሰንበት ጌታዋ ነው» በማለት እግዚአብሔር ስለ መሠረታት ሰንበት ሊናገር፥ ከእግዚአብሔር ጋር እኩል ስለሆነው ሥልጣኑ ማስረዳቱ ነበር። 

28ኛ ጥያቄ፡- ሀ) ማቴዎስ 5፡21-22፥ 27-28፥ 31-32፥ 33-34፥ 38-39፥ 43-44 ያሉትን ክፍሎች አንብቡ፡ በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ተረጋግመው የተነሡ ሐረጎች የትኞቹ ናቸው? ለ) ኢየሱስ በእነዚህ ሁለት ሐረጎች ደጋግሞ ሲጠቀም ምን ለማለት የፈለገ ይመስላችኋል? 

ማቴዎስ 5-7 ያለው ክፍል ኢየሱስ በተራራ ላይ ስላሰማው ስብከት ይዘግባል። ወደዚህ ስብከት መጀመሪያ አካባቢ ኢየሱስ ሁለት ሐረጎች ስድስት ጊዜ ደጋግሞ ይጠቅሳል። የመጀመሪያው ሐረ፥ «እንደተባለ ሰምታችኋል” የሚል ነው። ኢየሱስ እነዚህን ሐረጎች በተጠቀመ ቁጥር ከብሉይ ኪዳን ሕግ ይጠቅስ ነበር። አንዳንድ ጊዜም ባሕላዊውን የሕግ ትርጉም ያክልበት ነበር። ሁለተኛው የሚደጋግመው ሐረግ ደግሞ፥ «እኔ ቀን እላችኋለሁ” የሚለው ነው። ኢየሱስ በዚህ ሐረግ በሚጠቀምበት ጊዜ፥ ለብሉይ ኪዳን ሕግ የጠለቀ ትርጉም ይጨምርበት ነበር። ለምሳሌ ያህል፥ በማቴዎስ 5፡21-22 እንዲህ ይላል፥ «አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ እኔ ገን እላችኋለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል።» ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ስለ መግደል የተነገረው ማንም ሰው ሌላውን እንዳይጠላው የሚል መሆኑን በሥልጣን ያስገነዝባል። በዚህ ምዕራፍ ውስጥ በተደጋጋሚ፥ ኢየሱስ፥ «እንደ ተባለ ሰምታችኋል እኔ ግን እላችኋለሁ።» ሲል የእርሱ ትምህርት ልክ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ሁሉ የሚታመን መሆኑን መግለጹ ነበር። እንደዚሁም ኢየሱስ የእርሱ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቃል ጋር እኩል መሆኑን ያስረዳል። ኢየሱስ በተራራ ስብከቱ ላይ ትምህርቱን ከእግዚአብሔር ቃል ጋር እኩል በማድረግ፥ በተዘዋዋሪ መንገድ እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን ይገልጻል። 

ከፍ ብለን ኢየሱስ ኃጢአትን ይቅር በማለትና ቃሉ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካለው የእግዚአብሔር ቃል ጋር እኩል እንደሆነ በማሳወቅ በተዘዋዋሪ መንገድ እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን እንደ ገለጻ ተከታትለናል። እንደዚሁም፥ እርሱ ከእግዚአብሔር አብ ጋር አለኝ ባለው ልዩ ግንኙነት በተዘዋዋሪ መንገድ ራሱ እግዚአብሔር መሆኑን ገልጾአል። ጌታ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር አብ ጋር ግንኙነት እንዳለው ሲናገር፥ ከእግዚአብሔር አብ ጋር አንድ ዓይነት የተፈጥሮ ባሕርይ እንዳለው ማስገንዘቡ ነው።

ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

Exit mobile version