ጥያቄ፡- ሀ) ማቴቃለ 26፡59-66 አንብቡ። ኢየሱስ በእርሱ ላይ ለተሰነዘሩ ለእናታቱ ክሶች የሰጠው ምላሽ ዝምታ ነበር። በመጨረሻ በተናገረ ጊዜ ለየትኛው ጥያቀ ነው መልስ የሰጠው? ለ) ኢየሱስ በመለሰው መልስ ካህኑ ለምን ተቆጣ?
ኢየሱስ ተወንጅሎ በአይሁድ ሸንጎ ፊት በቀረበ ጊዜ፥ አይሁዶች ኢየሱስን የሚከሱበትን ወንጀል ይፈልጉ ነበር። ነገር ገን ምንም ዓይነት የክለ ምክንያቶችን ለማግኘት ቢጥሩም፥ ሕግ ለማፍረሱ ምንም ማስረጃ ሊያገኙ አልቻሉም። በመጨረሻም ሊቀ ካህናቱ፥ «አንተ የእግዚአብሔር ልጅ መሢሑ ክርስቶስ ነህን?» አለው። በሚቀጥለው ትምህርት ላይ መለስ ብለን «ክርስቶስ እና የእግዚአብሔር ልጅ» የሚሉትን የማዕረግ ስያሜዎች እናጠናለን። ለአሁኑ ስለ ኢየሱስ መልስና ስለ ካህናቱ ስሜት እናጥና። ኢየሱስ በአጭሩ መልስ ሲለጥ፥ «አንተ አልህ» ነበር ያለው። ይህን ሲመልስ ምን ማለቱ ነበር? ይህ አንተ የምትለው ነው፤ ነገር ግን እውነት አይደለም ማለቱ ነው? እንዲህ ማለቱ አይደለም። ኢየሱስ ያለው፥ «አዎን፥ ልክ አንተ እንዳልኸው ነው» ነበር። በሚቀጥለው ዐረፍተ ነገር ይህን ማለቱ እንደሆነ እንገነዘባለን። ኢየሱስ ወደ ፊት በእግዚአብሔር ቀኝ እንደሚቀመጥ ከዚያም በአምላካዊ ኃይልና ሥልጣን ወደ ምድር እንደሚመለስ ተናግሯል።
ኢየሱስ ራሱ የእግዚአብሔር ሥልጣንና ባሕርይ እንዳለው ገልጾአል፡ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆኑ ከካህኑ ጋር ተስማምቷል። ነገር ግን ስለ መሢሕነቱ ከካህኑ ጋር ከመስማማትም ያልፋል፡ እንደ መሢሕነቱ ኃይል፥ ሥልጣንና ከእግዚአብሔር ከራሱ ጋር የተስተካከለ ባሕርይ እንዳለው አክሎ ገልጾአል።
ኢየሱስ ይህንን ያለው በካህናቱ ምላሽ ምክንያት እንደሆነ እንገነዘባለን ካህናቱም እርሱ ያለውን እንደ ሰሙ፥ ልብሳቸውን ቀድደው ተሳደበ በማለት ከሰሱት። እርሱ አምላክ መሆኑን በማሳወቁ እግዚአብሔርን እንደ ተሳደር አድርገው ቆጠሩ።
ከእነዚህ ክፍለ ምንባቦች በግልጽ እንደሚታየው ኢየሱስ ራሱ አምላክ መሆኑን ገልጾአል። ኢየሱስ ስለ ራሱ የሚናገረውን ተቀብሎ ሳይስማማበት ማንም ሰው እርሱን አከብራለሁ፥ እንደዚሁም እከተለዋለሁ ሊል አይችልም፡ እርሱን እንደ እግዚአብሔር ልናመልከውና ልንታዘዘው ይገባል።
ጥያቄ፡- ኢየሱስን እንደ ነቢይ ወይም እንደ ታላቅ ሰው አድርጎ የሚያከብር ነገር ግን አምላክነቱን የሚክድ ሰው አጋጥሟችሁ፥ ወይም እንዲህ ስላለ ሰዉ የተጻፈ መጽሐፍ አንብባችሁ ታውቃላችሁ?
ጥያቄ፡- ኢየሱስን እንደ እግዚአብሔር መልእክተኛ እናከብራለን ስለሚሉ ግን እርሱ ራሱ እግዚአብሔር መሆኑን ለሚክዱ ሰዎች ምን ትመልሳላችሁ መልሳችሁን በማስታወሻ ደብተራችሁ ውስጥ ጻፉ።
ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ
